ድርሳነ እራኤል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ድርሳን ሲሆን በቀድሞው የቤ/ክርስቲያኒቱ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ መንበረ ፓትርያርክነት ወቅት እንዲሁ ይሁንታ ተሰጥቶት በትንሳዔ ዘጉባዔ ማተሚያ ቤት ታትሟል።
በዚህ መፅሀፍ እየሱስ ለማርያም ነገራት ተብሎ የተቀመጠው ንግግር አስተውሎ ለተመለከተው እጅግ ግራ አጋቢ ነው። በመፅሀፉ እንደተቀመጠው በጎጃም ምድር ውስጥ ከክርስቲያኖች ውጭ ያሉ አካላት አይቀመጡም ሲል ክልከላውን ያፀድቃል። በጎጃም ምድር እጅግ ቁጥሩ የበዛ ክርስቲያን ያልሆነ ማህበረሰብ/ሙስሊም/ ይገኛል። ይህንን መሠል ንግግሮች በቀደሙት ጊዜያት በቦታው አንዳንድ አካባቢዎች "እስላም ይውደም" እየተባለ ሰልፍ ለተወጣባቸው የጥላቻ ንግግሮች/Hate Speach/ ሰበብ ከመሆን የዘለለ ምን ፋይዳ አላቸው? ከዚህ በፊት ግምገማ ተደርጎ እርምት እንደተደረገባቸው ረሱል የሚሳደቡ "የተአምረ ማርያም" አንዳንድ ክፍሎች ይህስ በሊቃውንት ለምን አይመረመርምና እርማት አይሰጠውም? መሠል ትምህርቶች ለልጆች ማወረስስ ተገቢ ነው ወይ?
No comments:
Post a Comment