Thursday 15 October 2020

በእርሱ ያመኑትን ሕሙማንን ታሞ ያድን ዘንድ እጆቹን ለሕማም ዘረጋ ( ምንጭ ቅዳሴ ሐዋርያት ) ሰፍሃ እደዊሁ ለሕማም ሐሚሞ ከመ ሕሙማነ ያድህን እለ ተወከሉ በላዕሌሁ በእርሱ ያመኑትን ሕሙማንን ታሞ ያድን ዘንድ እጆቹን ለሕማም ዘረጋ ( ምንጭ ቅዳሴ ሐዋርያት ) የመጀመርያይቱ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዛሬ ላይ ተሃድሶ የሚያስፈልጋት ቢሆንም ቀድሞ ወይንም ከዚህ በፊት የነበራት የደኅንነት እምነት አቋም ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ያመኑትን ሕሙማንን ያድን ዘንድ እጆቹን ለሕማም ዘርግቶና ሕማማችንን ፣ መርገማችንንም ጭምር ወስዶልን ሳለ ፣ የዛሬዋ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ግን ኢየሱስ ክርስቶስ ለበደልዋ ካሳ የሚሆንን ቅጣት እንዳልተቀጣላት አድርጋ በመቁጠር ፣ የኪዳኑን ደም አክፋፍታና ረግጣ ወደ ፍጡራን አምልኮና አዳኝነት ኮበለለች :: ለደኅንነታችንም የተዘረጋው የኢየሱስ እጆች ሳይሆኑ የመላዕክት ክንፎች ናቸው አለችን :: ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ? ብለን ስንጠይቃት ደግሞም ታሪኳን አያይዛና ቀጥላ መላዕክቱ ክንፎቻቸውን ወደ ሲኦል በመዘርጋት ሥፍር ቁጥር የሌላቸውን ነፍሳት አዳኑ ስትልም መጽሐፍቅዱስ ላይ ያልተጻፈ ታሪክና የአሮጊቶችን ተረት መተረት ጀመረች ፤ እንደገናም በመላዕክቱ ሳታበቃ የመንግሥተ ሰማያት የይለፍ ፈቃድ ለነተክለ ሃይማኖት እንደ ተሰጠ አድርጋ በመቁጠር ፣ የኃጥኡም ሆነ የጻድቁ ነፍስ ተክለሃይማኖት ጋር ሳይደርስ ወደ ሲኦል አይሄድም አለችን :: የመጀመርያዋ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ግን የሐዋርያት ቅዳሴ በተሰኘው መጽሐፍዋ ላይ በእርሱ ያመኑትን ሕሙማንን ታሞ ያድን ዘንድ እጆቹን ለሕማም ዘረጋ ብላ ጽፋና ከትባ ስለያዘች ለደኅንነትዋ ከተዘረጋላት ከጌታ እጅ ውጪ ሌላ ነገር ማለትም ሆነ መቀላወጥ አላማራትም ፣ ደስም አላሰኛትም :: በእርሱ ያመነውን ሕሙማንን ያድን ዘንድ እጆቹን ለሕማሜ የዘረጋልኝ የጌታዬ እጅ ለእኔ በቂዬ ነው ስለዚህ የነፍሴ አዳኝ ኢየሱስና ኢየሱስ ብቻ ነው ስትል የሐዋርያት ሥራ 4 ፥ 12 በእርሱ ላይ አርፋና ተደላድላ እኛንም አደላደለችን :: ለበለጠ መረጃ እንደገና የተለቀቀውን ቪዲዮ በማስተዋል ተከታተሉ ለሌሎች ወገኖችም ሼር አድርጉ ስል ለማበረታታት እወዳለሁ ጌታ ይባርካችሁ ወንድማችሁ ሐዋርያዊው አገልጋይ አባ ዮናስ ጌታነህ

Friday 2 October 2020

GEDION ASCHALEW "ማንነቴን ሰዋዋለው" Amazing New Ethiopian Gospel Song

#henonstudio #gedi #share ጌታ ይሻልሀል by Gedion Ascha...

 በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!

በእንተ ሰማንያ አሃዱ (ክፍል-1)
መግቢያ
የቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ምንም እንኳን ኦርቶዶክሳዊው እስቤ መጽሐፍ ቅዱስ ብቸኛው የክርስትና አስተምህሮ መመሪያና ምንጭ ነው ባይልም መጽሐፍ ቅዱስ ለቤተክርስቲያን መተኪያ የሌለው የጽሁፍ ሀብቷ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ብቸኛው የክርስትና አስተምህሮ መመሪያና ምንጭ አይደለም ያልነው ትውፊት ከመጽሐፍ ቅዱስ ጎን ለጎን አብሮ ስለሚያገለግል ነው። የጽሁፉ ሀሳብ መጽሐፍ ቅዱስን በሚመለከት ስለሆነ ትውፊትን በሚመለከት እራሱን በቻለ ርእስ እንመጣበታለን። መጽሐፍ ቅዱስ ለክርስትና አስተምህሮ መሠረት ነው የሚለው በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት ቢኖረውም በውስጡ ስላሉት የመጽሐፍት ብዛት ግን ልዩነት መኖሩ የታወቀ ነው። በተለይም ፕሮቴስታንታውያን ከሉተር የተሃድሶ እንቅስቃሴ በኃላ እንደ አዲስ የተሰራውን 66ት መጽሐፍት ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሚቀበሉ በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ያሉ (እነርሱ ጋር የሌሉትን) መጽሐፍት ሲተቹ ይታያሉ። ለአብነትም በቴዎድሮስ ደመላሽ "ሰማንያ አሃዱ በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን" የሚለውን መጽሐፍና "ኦርቶዶክስ መልስ ካላት እኛም ጥያቄ አለን" በሚል የተዘጋጀውን ቪሲዲ መጥቀስ ይቻላል። ይህንን መሠረት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስላለው በተለምዶ ሰማንያ አሃዱ ስለሚባለው መጽሐፍ ቅዱስ ከስር ከመሠረቱ በመመልከት ለጠያቂዎች ምላሽ አዘጋጅተናል።
=>>>እንደ መንደርደሪያ (አጠቃላይ ጥያቄያዊ መልእክቶች ለፕሮቴስታንታውያን)
1. መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ጊዜና ቦታ የተጻፈ መጽሐፍ እንደሆነ ይታወቃል። በተለይም የሀዲስ ኪዳን መጽሐፍት በተጻፉበት ወቅት ሌሎች ሀሰተኞች መጽሐፍት (ψευδεπγραφα/Peudepigraha) ስለነበሩ እውነተኞችን መጽሐፍት ከሀሰተኞች ለመለየት የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና (Biblical Canonization) መንገድ ተጠቅመዋል። በዚህ የቀኖና ሂደት ውስጥ የተሳተፍት የጥንቷ ቤተክርስቲያን አባቶች (Early Church Fathers) ነበሩ። እነዚህ አባቶች በክህነት የሚያምኑና እራሳቸውም እስከ ጵጵስና ደረጃ የደረሱ ነበሩ። ይህ ከሆነ ዛሬ ላይ ያሉ በመጽሐፍ ቅዱስ እናምናለን የሚሉ የተለያዩ በክርስትና ስም ያሉ የእምነት ድርጅቶች (ፕሮቴስታንታውያን፣ ጅሆቫ ዊትነስ፣ ኦንሊ ጂሰሶች) የጥንቷ ቤተክርስቲያን አባቶች ሰፍረው እና ለክተው የሰጧቸውን መጽሐፍት ነው የሚጠቀሙት ማለት ነው። እኛም የቤተክርስቲያን አባቶች በምሥጢራተ ቤተክርስቲያን፣ በነገረ ክርስቶስ፣ በምሥጢረ ሥላሴ፣ በነገረ ማርያም፣ በነገረ ድኅነት፣ በነገረ ቤተክርስቲያን ያስተማሩትን ትምህርቶች ለምን አትቀበሉም? ብለን እንጠይቃለን። እውነተኞችን መጽሐፍት ከሀሰተኞች ለይተው ቀንነው በአንድ ጥራዝ የሀይማኖት መመሪያ የሆነውን መጽሐፍ ከተቀበላቹ ሙሉ ትምህርታቸውን ለምን አትቀበሉም? ለማለት እንወዳለን።
2. ሉተር ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሲወጣ ከጀመራቸው "የብቻ ትምህርቶች" አንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ (Scripture alone) ነው። ይህ አመለካከት ዛሬ ላይ ባሉ የፕሮቴስታንት ዲኖሚኔሽኖችም ዘንድ የሚንጸባረቅ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ ምን ያህል መጽሐፍት እንዳሉት አይዘረዝርም። ጸሀፊያቸው ማን መሆኑን እንኳ የማይናገሩት የሐዲስ ኪዳን መጽሐፍት ራሳቸውን በራሳቸው አያረጋግጡም። ለምሣሌ የማቴዎስ ወንጌልን እንውሰድ። የማቴዎስ ወንጌል የተጻፈው ከ 12ቱ ሐዋርያት አንዱ በሆነው በማቴዎስ ስለ መሆኑ አንድም ቦታ ላይ እንኳ አይናገርም። እንዲያውም በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ዘመን በማቴዎስ ስም ይሰራጭ የነበረው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ብቻ አልነበረም። ማቴዎስ ወንጌላዊ ጽፎታል ተብሎ ይሰራጭ የነበረ "የተከራካሪው የቶማስ መጽሐፍ- The book of the contender" የሚባል መጽሐፍም ነበር። የማቴዎስ ወንጌልን ከዚህ አይነቱና ሌሎች መጽሐፍት ቱውፊትን ካልተጠቀሙ እንዴት መለየት ቻሉ?
3. ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ ላይ ፕሮቴስታንቶች በሚቀበሏቸው መልኩ 66ቱ መጽሐፍ ቅዱስ የተቀነነው(የተዘጋጀው) ከሉተር በኃላ ነው። ለአብነት ብንመለከት:-
=>>> ሶስቱ ሲኖዶሳውያት ቀኖና ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውኝን መጽሐፍት ይዘዋል።
1. 85 ሐዋርያውያት ቀኖናት 85ኛ ቀኖና ( Canons of the apostles)[1]:- ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን ከብሉይ ኪዳን መቃብያን መጽሐፍትን፣ ከሀዲስ ኪዳን መልእክታተ ቀለሜንጦስን አካቶ ይዟል። በአንጻሩ ደግሞ የዮሐንስ ራእይን አያካትትም።
2. ቀኖናት ዘሎዶቅያ/Council of Laodicea [2]:- የሎዶቅያ 60ኛ ቀኖና ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን መጽሐፈ ባሮክ እና ተረፈ ኤርሚያስን ይዟል በአንጻሩ ደግሞ የዮሐንስ ራእይን አያካትትም።
3. ቀኖናት ዘቅርጣግ (Codex Canonum ecclesiae africanae) [3] በመባል ይታወቃል። ይህ ቀኖና ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን መጽሐፈ ጥበብና የመቃብያን መጽሐፍትን ይዟል።
=>>>በቤተክርስቲያን አባቶች በግል ደረጃ የተቀነኑ ቀኖናዎች ስንመለከትም ዛሬ ላይ ፕሮቴስታንት እጅ ካለው የተለዩ ሆነው እናገኛቸዋለን። ለምሣሌ ቅዱስ አትናቴዎስ በ 367ዓ.ም በላከው የፋሲካ መልእክቱ 39ኛ ላይ የመጽሐፍትን ዝርዝር በቀኖና መልክ አስቀምጧል። [4]ቅዱስ አትናቴዎስ በዘረዘራቸው ውስጥ መጽሐፈ ባሮክና ተረፈ ኤርሚያስ(ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸው) ተካተው ሲገኙ መጽሐፈ አስቴር (ፕሮቴስታንቶች የሚቀበሉት) አልተካተተም።
=>>>እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ዛሬ 66ቱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው እውነተኛ፣ ሌሎች መጽሐፍት ሀሰተኞች/ተቀባይነት የሌላቸው የሚለው ሀሳብ እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል? ከየትኛው ታሪካዊ የቀኖና ሂደትስ አገኙት?በእርግጥም ከጥንት የቤተክርስቲያን አባቶች ሉተር በልጦባቸው ይህን አድርገዋል።
=>>>በቀጣይ ጽሁፍ የሰማንያ አሃዱ መጽሐፍት ምንጮችን ለመመልከት እንሞክራለን።
ማጣቀሻ
[1]Michael D. Marlowe. "The "Apostolic Canons" (about A.D. 380)" . Bible Research . Archived from the original on 29 August 2010. Retrieved 2 September 2010.
[2] Council of Laodicea at bible-researcher.com . Retrieved 2011-10-05.
[4]የሰማንያ አሃዱ መጽሐፍት ምንጮች እና ቀኖናት-ዲበኩሉ ዘውዴ ገጽ 52
ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!
©ዕቅበተ እምነት ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
No photo description available.
19
1 Comment
23 Shares
Like
Comment
Share

 በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!

በእንተ ሰማንያ አሃዱ (ክፍል-2)
[የዲዩትሮካኖን/Deuterocanonical መጻሕፍት ምንጮች]
=>>>በኦርቶዶክስና በካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ በፕሮቴስታንቶች ዘንድ የማይገኙ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ዲዩትሮካኖን(Deuterocanon) ተብለው ሲጠሩ ሁለተኛ የቀኖና መጻሕፍት ማለት ነው። በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ደግሞ ፕሮቶካኖን(Protocanon) ተብለው ሲጠሩ የመጀመሪያ ቀኖና መጻሕፍት ማለት ነው። ፕሮቶካኖን እና ዲዩትሮካኖን የሚለው ቃል ቅደም ተከተልን (Chronological Order) የሚያሳይ እንጂ በመጻሕፍቱ መካከል ለየቅል የደረጃ ልዩነት እንዳለ (Distinction in Status) የሚገልጽ አይደለም። [1] ይህም ማለት ዲዩትሮካኖኒካል የተባለቡት ዋናው መክንያት በቀኖና የተመዘገቡበትን የታሪክ ምእራፍ ለማመልከት ነው።
=>>>የመጀመሪያዎቹ የብሉይ ኪዳን ቀኖና መጻሕፍት(Protocanonical Books) በእስራኤል የመመለስ ዘመን ካህኑና ጸሀፊው ዕዝራ በሠራው ቤተ መጻሕፍት ውስጥ አስቀምጧቸዋል። በዚህ ወቅት የተሰበሰቡት መጻሕፍት በአይሁድ እጅ የተገኙት ብቻ ነበሩ። በሳምራውያን እና በኤሴያውያን እጅ የነበሩ መጻሕፍት በወቅቱ አልተሰበሰቡም። [2] በሁለተኛ መቃብያን እንደ ተጻፈው ነህምያ ቤተ መጻሕፍት ባቋቋመ ጊዜ የነገሥታትንና የነብያትን መጻሕፍት የዳዊት መዝሙራትና የነገሥታትን ደብዳቤዎች አሰባስቧል። ዕዝራና ነህምያ በሌሎች የአይሁድ ክፍሎች (ሳምራውያንና ኤሴያውያን) እጅ የነበሩትንና ከእነርሱ በኃላ የተጻፉትን መጽሐፍት አላሰባሰቧቸውም።
=>>>ሁለተኛዎቹ የብሉይ ኪዳን የቀኖና መጻሕፍት (Deuterocanonical Books) ከእዝራና ከነህምያ በኃላ የተጻፉ ወይም ቀድመው ቢጻፉም በኃላ ተሰባስበው ወደ ቀኖና የገቡ መጻሕፍት ናቸው። እስራኤላውያን በግብጽ በባቢሎንና በፋርስ በተደጋጋሚ በደረሰባቸው ስደት የተነሳ መጽሐፍት ተበታትነው ይገኙ ነበር። በተለይም ከ 2ኛው ክ/ዘመን በኃላ ወደ ቁምራን ዋሻ (ሙት ባሕር አካባቢ) መሰባሰብ የጀመሩት ኤሴያውያን የያዙዋቸው መጻሕፍት ለብዙ ዘመናት ተጠብቀው ቆይተዋል። ከዚያ በኃላ የተነሱ የአይሁድም የክርስቲያንም ሊቃውንት እየተፈለጉ ሲገኙ ለቀኖና በመብቃታቸው ሁለተኛ የቀኖና መጻሕፍት ለመባል ችለዋል። [3]
=>>>የዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ምንጮች እና ቀኖናዊ ማረጋገጫዎች:-
፩. መጽሐፍ ቅዱስ:- የሀዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጸሀፊዎች ከዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት እየጠቀሱ ጽፈዋል። ይኸውም መጻሕፍቱ ተአማኒነት እንዳላቸው የሚያረጋግጥ ነው። ለአብነት የሚከተሉትን ጥቅሶች መመለከት ይቻላል።
1. ይሁዳ ጌታን በሠላሳ ብር ከሸጠው በኃላ ተጸጽቶ ሠላሳውን ብር ለካህናት አለቆች መልሶላቸዋል። እነርሱም የሸክላ ሠሪን መሬት ገዝተውበታል። ይህ አስቀድሞ በነብዩ ኤርሚያስ የተነገረ ትንቢት ነው። ይህ ትንቢት አስቀድሞ ከዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት አንዱ በሆነው በተረፈ ኤርያስ ተጽፏል።
"በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው። ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥
ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት። የሚል ተፈጸመ።" ማቴ27÷9-10
"የእስራኤል ልጆች የተስማሙበት የክርስቶስን ዋጋ ሠላሳውን ብር ይቀበሉታል። ያንንም ብር ለሸክላ ሠሪ ቦታ ዋጋ አድርገው ይሰጡታል" ተረፈ ኤርሚያስ 7÷3 (1980 እትም)
2. አይሁድ ጌታችንን መከራ እንዳደረሱበት፣ እንደ ዘለፉት እና ለሞት አሳልፈው እንደሰጡት በመጽሐፈ ጥበብ በትንቢት የተቀመጠውን እና በወንጌላት የተጻፈውን በማነጻጸር ማየት ይቻላል።
ትንቢት:- "የእግዚአብሔር እውነተኛ ልጅ እንደሆነ ያድነው ከሚቃወሙትም ሰዎች እጅ ያድነው" ጥበብ2÷18
ፍጻሜ:- " በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።"
ማቴ 27:43
ትንቢት:- "ቅንነቱን እናውቅ ዘንድ እየሰደብን በመከራ እንመርምረው እንደ ቃሉ ረዳት ይሆነው እንደሆነ የከፋ የተዋረደ ሞትን እንፍረድበት አሉ" ጥበብ2÷19-20
ፍጻሜ:- "ኢየሱስንም የያዙት ሰዎች ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤ ሸፍነውም ፊቱን ይመቱት ነበርና። በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገር እያሉ ይጠይቁት ነበር።ሌላም ብዙ ነገር እየተሳደቡ በእርሱ ላይ ይናገሩ ነበር።" ሉቃ22÷63-65
3. በወንጌል ላይ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመፈተን የቀረቡ ትንሳኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን እንደ ነበሩ ተጽፏል።
"ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት....ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች? ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። ከመጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።" ማቴ22÷24-28
ሰዱቃውያ ይህን ታሪክ ከመጽሐፈ ጦቢት ነው የወሰዱት። እነርሱ እሱን ለመፈተን ታሪኩን ቢጠቅሱትም መጻሕፍትን አታውቁምና ትስታላቹ ብሎ መልስ ሰጥቷቸዋል።
"እንሆ ሰባት ሰዎች አገቡሽ ባሎችሽ እየታነቁ እንዲሞቱ አታውቂምን? አሏት። ከነርሳቸው አንዱ እንኳን አልቀረሽም። እነርሳቸውም ሞተዋልና..." ጣቢት3÷8
4. ከጌታ ሐዋርያት ከሆኑት አንዱ ይሁዳ ሄኖክ ስለ ተናገረው ትንቢት ጽፏል። የሄኖክ ትንቢት በመጽሐፈ ሄኖክ ላይ ተጽፎ ይገኛል።
" ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ። እነሆ፥ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ... ሁሉ እንዲወቅስ ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቶአል ብሎ ለእነዚህ ደግሞ ትንቢት ተናገረ።"
ይሁ 1:14-15
"ለወዳጆቹ ይፈርድላቸው ዘንድ እንሆ ከብዙ መላእክት ጋራ ይመጣል። ሕገ እግዚአብሔርንም የዘነጉ ሰዎች ያጠፋቸዋል።"
መጽሐፈ ሄኖክ 1÷9
5. ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንቶስ መልእክቱ ከመጽሐፈ መቃብያን ጠቅሶ ጽፏል።
" ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።"
1ኛቆሮ 2:9
"ለደጋግ ሰዎች የተዘጋጀች ደስ የምታሰኝ ዓይን ያለየውን ጆሮም ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን እግዚአብሔር ደስ ላሰኙት ያዘጋጀውን..." 1ኛመቃ14÷20
6. ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱም ከመጽሐፈ መቃብያን ጠቅሶ አስተምሯል።
" ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤"
(ወደ ዕብራውያን 11:35)
ይህ ታሪክ በቀጥታ ከመጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ከምእራፍ 3 የተወሰደ ታሪክ ነው። 1ኛመቃ3÷1-38 ይመልከቱ።
7. በትንቢተ ኤርሚያስ ላይ የኤርሚያስ ደቀ መዝሙር የነበረው ባሮክ ጸሀፊ እንደ ነበር ተጽፏል። ደግሞም ከኤርሚያስ የሚሰማቸውን ነገሮች ይጽፍ እንደ ነበር ተጽፏል።
"ኤርሚያስም ሌላ ክርታስ ወሰደ ለኔርያም ልጅ ለጸሐፊው ለባሮክ ሰጠው እርሱም የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም በእሳት ያቃጠለውን የመጽሐፍ ቃል ሁሉ ከኤርሚያስ አፍ ጻፈበት ደግሞም እንደ ቀድሞ ያለ ቃል ብዙ ቃል ተጨመረበት" ኤር36÷32
ይህ ሀሳብ ለመጽሐፈ ባሮክ ፍንጭ የሚሰጥ ነው። ባሮክ ጸሀፊ ከነበረ ባሮክ የጻፋቸው መጽሐፍት ወዴት አሉ? የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል።
በቀጣይ ክፍል የዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ሌሎች ምንጮችን እንመለከታለን።
ማጣቀሻ
[1] Catholic Encyclopedia, Canonof the Old Testament
[2]The Bible through the Ages p-127
[3]Pope Shenouda lll CD, Coptic Orthodox Church, Australia, 1988
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
©ዕቅበተ እምነት ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
No photo description available.
9
17 Shares
Like
Comment
Share

 ዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!

በእንተ ሰማንያ አሃዱ (ክፍል-3)
የዲዩትሮካኖኒካል(Deuterocanonical) መጽሐፍት ምንጮች
=>>>በክፍል-2 ጽሁፍ የዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ምንጮች መካከል ዋነኛው መጽሐፍ ቅዱስ እንደሆነ ተመልከተን የሀዲስ ኪዳን መጽሐፍት ፀሀፊዎች ከመጻሕፍቱ እየጠቀሱ መጻፋቸውን ተመልክተናል። በዚህ ጽሁፍ የቀሩትን ሌሎች ምንጮች ለማየት እንሞክራለን።
፪. ግሪክ ሰባ ሊቃናት (Septuagint/LXX) ትርጉምና ስብስብ
የሰባው ሊቃውንት ትርጉም በባቢሎን ምርኮ ጊዜም ሆነ ከምርኮው በኃላ በተፈጠሩ ችግሮች ወደ ግብጽ ተሰደው በዚያ በመሰረቱት የእስክንድርያ አይሁድ በበጥሊሞስ 2ኛ ፒላደልዩስ/Ptolemy II Philadelphus (285-247 ቅ.ል.ክ) ትእዛዝ ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የተተረጎመ ነው። ይህ የሰባ ሉቃውንት ትርጉምና ስብስብ በግሪክ አናጊግሶስኮመና
(anagignoskomena) ወይም ዲዩትሮካኖኒካል (deuterocanonical) መጽሐፍትን ይዘዋል። ይሄን በሚያጠናክር ሁኔታ በግሪክ ቋንቋ የተጻፉ ቀደምት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዞች(codices) መሆናቸው በሚታመነው የቫቲካን ጥራዝ (Codex Vaticans)፣ የሲናይ ጥራዝ(Codex Sinaiticus እና የአሌክሳንደርያ ጥራዝ (Codex Alexanderinus) ውስጥ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ከሌሎት አሥራው መጻሕፍት ጋር አብረው ይገኛሉ። [Meade, John D. (2018-03-23). "Was there a "Septuagint Canon"?" . Didaktikos: Journal of Theological Education. Retrieved
8 October 2019.]
=>>>Septuagint vs Masoretic Text
=>>>አይሁድ ከክርስቶስ ልደት በፊት የታወቀ እና የተወሰነ የመጽሐፍት ብዛት የላቸውም። ለመጀመሪያ ጊዜ ከክርስቶስ በኃላ በ 90ዓ.ም በጃሚና ጉባኤ(Council of Jamina) የተሰበሰቡት ሊቃውንት ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሏቸውን የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ላለመቀበል ወሰኑ። በመቀጠልም ማሶሬቲክስ( Masoretic Text/MT) በመባል የሚታወቀውን የአይሁድ የብሉይ ኪዳን 39 መጽሐፍት ያሉትን ከ600ዓ.ም ጀምሮ ፈሪሳውያን አይሁዶች በገሊላ በጥብርያዶስ ባህር አጠገብ ተሰብስበው ማዘጋጀት ጀመሩ። በጃሚና የተሰበሰቡ አይሁድ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍትን ያልተቀበሉበት ሁለት ዋና መክንያቶችን ማንሳት ይቻላል። [Canon of the Old Testament" .
Catholic Encyclopedia .]
1. የመጀመሪያው አይሁድ የራሳቸውን መጽሐፍ እየጠቀሱ መልስ ላሳጧቸው የክርስቲያን ሊቃውንት መልስ ለመስጠት ትኩረት የሰጡበት ጊዜ ነበር። የአይሁድ ጉባኤ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ስለ መሲሁ መምጣት፣ አለምን ለማዳን ስለ መሰቀሉ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በግልጽ ይመሰክራሉ። ይህ ደግሞ አይሁድ ለክርስቶስ ከነበራቸው አመለካከት ጋር ይጋጫል። ለራሳቸው አመለካከት ሲሉ መጽሐፍቱን ላለመቀበል ወስነዋል። ስለ መሲሁ በግልጥ የሚናገሩ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ለአብነት ያህል የቀረቡ:-
መጽሐፈ ጥበብ:-
"እግዚአብሔርንም ማወቅ በእኔ አለ ይላል ራሱንም የእግዚአብሔር ልጅ ያደርጋል" ጥበብ2÷13
መጽሐፈ ባሮክ
"እርሱን የሚመስል ሌላ የለምና ወደ አንተ መጣን ይላሉ።የጥበብን ሥራ ሁሉ እርሱ አገኛት ለባለሟሉ ለያእቆብ ለወዳጁም ለእስራኤል ሰጠው። ከዚህ በኃላ በምድር ተገለጠ እንደ ሰውም ሆነ።" ባሮክ3÷38
2. የአይሁድ ዳግማዊ የነጻነት እንቅስቃሴ 70ዓ.ም ከፈነዳ በኃላ የብሔራዊነት ስሜት ያየለበት ጊዜ ነበር። ይህ በመሆኑ በ 90 ዓ.ም በጃሚና ጉባኤ የመጽሐፍትን ቀኖና ለመወሰን የተሰበሰቡ አይሁድ በነበራቸው ፀረ ግሪካዊ አቋም በግሪክ ቋንቋ ብቻ ይገኙ የነበሩትን መጽሐፍት ላለመቀበል ወስነዋል።
[ለምን የሰባ ሊቃውንት ትርጉምና ስብስብ ለዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ምንጭነት ተጠቀሰ?]
=>>>ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከነበረበት የቤተክርስቲያን ምሥረታ ጀምሮ በቤተክርስቲያን አባቶች ዘንድ (Early Church Fathers) ተቀባይነት የነበረው የሰባ ሊቃናት ትርጉም ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት እንደ ሚናገሩት አብዛኛዎቹ በሀዲስ ኪዳን መጽሐፍት የተጠቀሱት የብሉይ ኪዳን ጥቅሶች ከሳባ ሊቃውንት ትርጉም የተወሰዱ ናቸው።በተጨማሪም በጥንቷ ቤተክርስቲያን በአብዛኛው ለትርጉም ምንጭነት እና ለማሥተማሪያነት ያገለገለው የሰባው ሊቃውንት ትርጉም ነው። የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍትን አካቶ የያዘው የሰባ ሊቃውንት ትርጉምና ስብስብ በመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን ዘንድ እውቅና ያለው መሆኑ ለመጽሐፍቱ ተአማኒነት ማረጋገጫ የሚሰጥ ነው። [Nicole, Roger, New Testament Use of the Old Testament Revelation and the Bible , ed. Carl. F.H. Henry (Grand Rapids: Baker, 1958), pp. 137–51.]
[የአይሁድ ውሳኔ እና ፕሮቴስታንቶች]
=>>>አይሁድ መጽሐፍቱን ያልተቀበሉባቸው የራሳቸው መክንያት ያላቸው ሲሆን ፕሮቴስታንቶችም እነርሱ ካልተቀበሉ እኛም አንቀበለም ብለው አውጥተዋቸዋል። ይህ የስህተት ሀሳብ ነው።
1. ከክርስቶስ መምጣት በኃላ አይሁድነት በቀድሞው ማንነት የሚታወቅ አይደለም። አሁን በክርስትና ዘመን አይሁድ ስንል የይሁዳ ነገዶች ወይም የያእቆብ ዘሮች ወይም የአብርሃም የቃልኪዳን ልጆች ማለት አይደለም። ከክርስቶስ እርገት በኃላ ያለው አይሁድነት እውነተኛ ሳይሆን ሐሰተኞች የክርስቶስ ተቃዋሚ (Anti-Christ) እና የሰይጣን ማህበር መሆናቸውን ቅዱስ መጽሐፍ አስቀምጦታል።
" መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ፥ ነገር ግን ባለ ጠጋ ነህ፤ የሰይጣንም ማኅበር ናቸው እንጂ አይሁድ ሳይሆኑ። አይሁድ ነን የሚሉት የሚሳደቡትን ስድብ አውቃለሁ።"
(የዮሐንስ ራእይ 2:9)
አይሁዶች እኛ ከአማኞች ወገን ነን ቢሉም የሚታመኑበት መንገድ ግን በጌታ በክርስቶስ ከሆነው የመዳን መንገድ የተለየ በመሆኑ የሰይጣን ማህበር ተብለዋል። ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ እንዲህ ይላል:-
"በግልጥ አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ አይደለምና፥ በግልጥ በሥጋ የሚደረግ መገረዝም መገረዝ አይደለምና ዳሩ ግን በስውር አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ ነው፥ መገረዝም በመንፈስ የሚደረግ የልብ መገረዝ ነው እንጂ በመጽሐፍ አይደለም።" ሮሜ2÷28-29
=>>>የጥንቷ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ከሐዋርያት በተማሩት መሰረት ይህንን የቅዱስ ጳውሎስ ጥቅስ አብራርተውታል። የሁሉም አረዳድ ከክርስቶስ መወለድ በኃላ ያሉት የአይሁድ ማህበር ሀሰተኛ እንደሆነና እና በፊደል ሳይሆን በመንፈስ የሚመላለሱ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ሕግ የሚፈጽሙ በስሙም የተሾሙ እስራኤል ዘነፍስ እነርሱም የክርስቲያኖች ማህበር የሆነችው ቤተክርስቲያን ባለ ሙሉ ስልጣን እንደሆነች ነው። ለዚህም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (St. John Chrysostom)፣ ሊቁ አርጌንስ (Origen the Scholar)፣ ቅዱስ ጎርጎሪዮስ( St. Gregory the Theologian) ተጠቃሽ ናቸው። [The Epistle of St Paul to the Romans. Based on the interpretation & Meditations of the Early Fathers by:- Fr Tadros, Yacoub Malaty. Page 52-54] በተጨማሪም ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበሩት አይሁዶች ወጥ የሆነ የመጽሐፍት ብዛት አልነበራቸውም። ፈሪሳውያን አይሁድ፣ ሰዱቃውያን አይሁድ፣ ኤስንያን አይሁድ፣ ሳምራውያን እና ቤተ እሥራኤል በሚጠቀሙት ቅዱሳት መጽሐፍት ይለያያሉ። በሀዲስ ኪዳን ባለ ሙሉ ስልጣን የሆነችው ቤተክርስቲያን እንጂ የሀሰተኞች ማህበር የሆነው የአይሁድ ስብስብ አይደለም። ይህ በሆነበት ሁኔታ ከመሲሁ መገለጥ በኃላ የተወሰነን የአይሁድ ውሳኔ ትክክል ነው ብሎ የቤተክርስቲያን መጽሐፍትን አለመቀበል የአይሁድ ፀረ ክርስቶሳዊ ሀሳብ መደገፍ ነው። ለዚህ ነው መጽሐፍ እንዲህ ሲል ያስጠነቀቀን:-
" ኢየሱስም። ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁ አላቸው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 16:6)
2. ፕሮቴስታንቶች የአይሁድ ውሳኔ ትክክል ነው ብለው መቀበላቸው ራሳቸውን ችግር ውስጥ ይከታቸዋል። መክንያቱም አይሁድ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍትን አንቀበልም ብለው ያበቁ ሳይሆን በ 66ቱ ውስጥ ከሚገኙት 39ኙ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍትም ብዙ ነገር ሰርዘዋል። ለአብነት የሚከተሉትን መመልከት ይቻላል:-
፩. " እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 1:23)
ይህ ትንቢት ከትንቢተ ኢሳይያስ 7÷14 የተወሰደ ነው። በአይሁድ Masoretic መጽሐፍ ድንግል የሚለውን ወጣት ሴት young woman ይለዋል።
፪. " ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ። መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤"
(ወደ ዕብራውያን 10:5) ይህ የትንቢት ቃል የተወሰደው ከመዝሙር 40÷6 ነው። በአይሁድ Masoretic ስጋን አዘጋጀህልኝ የሚለው የለም።
=>>>ከዚህ የምንረዳው አይሁድ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍትን አለመቀበል ብቻ ሳይሆን ከፕሮቶካኖኒካል መጽሐፍትም ብዙ ለውጥ ማድረጋቸውን ነው።
[መጽሐፈ ሄኖክና መጽሐፈ ኩፋሌ]
አንዳንድ ሰዎች መጽሐፈ ሄኖክና መጽሐፈ ኩፋሌ በኢትዮጵያ ብቻ ስለሚታወቁ ተቀባይነት የላቸውም ይላሉ። ይህ ግን የስህተት ሀሳብ ነው።
=>>>መጽሐፈ ሄኖክ(Book of Enoch) በሀዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ በሐዋርያው ይሁዳ ተጠቅሷል። ይሁዳ1÷14 እና ሄኖክ 1÷9 ተመልከቱ። በኢትዮጵያ ብቻ ይታወቃል የሚለውን ሀሳብ የሚያፈርስ አዲስ ግኝት ተገኝቷል። ይኸውም የሙት ባህር ጥቅል (Dead See Scrolls) በመባል የሚታወቁት በቁምራን ዋሻ ውስጥ የተገኙት የቅዱሳት መጻሕፍት ስብስብ ነው። መጽሐፈ በአርማይክ (Aramaic)፣ በኩይኔ ግሪክ( Koine Greek) እና በላቲን (Latin) ቋንቋዎች የተጻፉ የመጽሐፈ ሄኖክ ቁርጥራጮች ተገኝተዋል። በዚህም መጽሐፉ አስቀድሞ በአይሁድ ዘንድ የታወቀ እንደሆነ ማረጋገጫ የሰጠ ነው። በተጨማሪም በተለያዩ የ 1ኛና የ2ተኛ ክ/ዘመን ደራሲዎች እንደተጠቀሰ ይታወቃል። [Cheyne and Black, Encyclopaedia Biblica (1899), "Apocalyptic Literature" (column 220)]
ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት መጽሐፉን ስላላገኙት በቀኖና ውስጥ ባይከቱትም ኢትዮጵያ መጽሐፉ በእጇ ስላለ እና በራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት ያለው ብሎም ከሌሎች ቅዱሳት መጽሐፍት ጋር የሚስማማ ስለሆነ በቀኖና ውስጥ ከታዋለች።
=>>> መጽሐፈ ኩፋሌ (Book of Jubilees) :- የዚህ መጽሐፍ ጸሀፊ ሙሴ እንደሆነ ይታመናል። ይህንንም በመጽሐፉ ይዘት ማረጋገጥ ይቻላል። ይህም መጽሐፍ ልክ እንደ መጽሐፈ ሄኖክ በሙት ባህር ጥቅሎች (Dead see scrolls) ተገኝቷል። ይህም ልክ እንደ መጽሐፈ ሄኖክ አስቀድሞ ይታወቅ እንደ ነበር የሚያሳይ ነው። በተጨማሪም በቀደምት የቤተክርስቲያን አባቶች ለማስተማሪያነት እንደ ተጠቀሰ ይነገራል። ለአብነትም ኤጲፋኔዎስ (Epiphanius) ፣ ጀስቲን (Justin Martyr), አርጌንስ(Origen) , የታርሱሱ ዲዮዶሮስ(Diodorus of Tarsus) ይጠቀሳሉ። [Charles, R. H. (1902). The book of Jubilees or the Little Genesis . London: Adam and Charles Black. pp. lxxvii–lxxxvi.]
=>>>በተጨማሪም በሙሴ ኦሪት መጻሕፍት የማይገኙ ግን በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሱ ጥቅሶች አሉ። ለምሣሌ:-
" ሙሴም። እጅግ እፈራለሁ እንቀጠቀጥማለሁ እስኪል ድረስ የሚታየው እጅግ የሚያስፈራ ነበር፤" (ወደ ዕብራውያን 12:21) መመልከት ይቻላል። ይህ በሆነበት ሁኔታ ከአምስቱ የሙሴ መጽሐፍት ውጪ የሆነ ተቀባይነት የለውም ብሎ መደምደም አይቻልም። ቅድስት ቤተክርስቲያን በትውፊት በደረሳት መሠረት መጽሐፉን በቀኖና ውስጥ ከታ ትጠቀምበታለች።
=>>>በተጨማሪም በ Dead See Scrolls መጽሐፈ ሲራክ፣ ተረፈ ኤርሚያስ ያሉ የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ተገኝተዋል።
=>>በቀጣይ ጽሁፍ ተጨማሪ ሌሎች የዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ምንጮችን እንመለከታለን።
ስብሐት ለእግዚአብሔር!
©ዕቅበተ እምነት ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ!
No photo description available.
8
1 Comment
15 Shares
Like
Comment
Share