Wednesday 30 August 2017

ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ክፍል አስራ አምስት ( ቊጥር 1 ) ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ክፍል አስራ አምስት ( ቊጥር 1 ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዛሬውን ትምህርት ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው በሚል አርዕስት ጀምረናል ኢየሱስ ሰባ ስምንት ጊዜ ያህል ራሱን የሰው ልጅ በሚል ታይትል ጠርቷል በዚህ ውስጥ ደቀመዛሙርቱን የእርሱን አይደንቲቲ ጠየቀ የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 13 ኢየሱስ የሰው ልጅ የሆነበትን ጉዳይ ስንመለከት ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን እንመለከታለን ኢየሱስ እግዚአብሔር ሆኖ ሳለ ፍጹም ሰው ሆኖ የኖረበትን ሕይወት እናያለን ኢየሱስ የሰው ልጅ የሆነበት ትልቁ ምክንያት የሙሴን ሕግ ለመፈጸምና ለመጠበቅ ነው ለምን ስንል የአዳም ዘር የሆነ ሁሉ የሙሴን ሕግ መጠበቅ ስለማይችል ነው የሰው ልጅ የሚለው ታይትሉ ወይንም የተሰጠው ስያሜ ከምድራዊ ሕይወቱ ጋር የተያያዘ ነው የማርቆስ ወንጌል 2 ፥ 10 ከዚህ የተነሣ ለሰንበት እንኳ ሳይቀር ጌታዋ ነው የማርቆስ ወንጌል 2 ፥ 28 እንደገናም ኢየሱስ ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይ ወፎችም መሣፈርያ አላቸው ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው ይለናል የማቴዎስ ወንጌል 8 ፥ 20 የትምህርቱ ጠቅላላ ሃሳብ ይህ ነው ቪዲዮውን ስትሰሙት ደግሞ በተብራራ መልኩ የቀረበ ስለሆነ በብዙ ትጠቀማላችሁ ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment