Friday 18 August 2017

ወቅታዊና አስፈላጊ የጊዜው መልዕክት





የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ




የስድባችንን ፍርድ የሚፈርድልን ክፋቱንም በራሱ ላይ የሚመልስልን ስላለ በሰነፎች በባለጌዎችና በተሳዳቢዎች የምትበሳጩ የምትናደዱ አትበሳጩ አትናደዱ ( 1 ሳሙኤል 25 39 ሮሜ 12 19 )

Image result for nabal







ወቅታዊና አስፈላጊ የጊዜው መልዕክት















የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ





የስድባችንን ፍርድ የሚፈርድልን ክፋቱንም በራሱ ላይ የሚመልስልን ስላለ በሰነፎች በባለጌዎችና በተሳዳቢዎች 

የምትበሳጩ የምትናደዱ አትበሳጩ አትናደዱ ( 1 ሳሙኤል 25 39 ሮሜ 12 19 )


ተሰምቶ የማይጠገብ ድንቅ መዝሙር ስሙትና ተባረኩበት

ፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶ ዝማሬ መላዕክት ያሰማህ ዘመንህን 

እግዚአብሔር ይባርከው 








አልተቀጣምና እርሱ ይሞታል፤ በስንፍናውም ብዛት ይስታል ( መጽሐፈ ምሳሌ 5 23 )

ብልህ ሁሉ በእውቀት ይሠራል፤ ሰነፍ ግን ስንፍናውን ይገልጣል ( መጽሐፈ ምሳሌ 13 16 )

ለትግሥተኛ ሰው ብዙ ማስተዋል አለው፤ ቍጡ ግን ስንፍናውን ከፍ ከፍ ያደርጋል ( መጽሐፈ ምሳሌ 14 : 29 )

ሰነፍን በስንፍናው ከመገናኘት ልጆችዋ የተነጠቁባትን ድብ መገናኘት ይሻላል ( መጽሐፈ ምሳሌ 17 : 12 )

አንተ ደግሞ እርሱን እንዳትመስል ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት ( መጽሐፈ ምሳሌ 26 : 4 )

ለራሱ ጠቢብ የሆነ እንዳይመስለው ለሰነፍ እንደ ስንፍናው መልስለት ( መጽሐፈ ምሳሌ 26 : 5 )

ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ ውሻ ስንፍናውን የሚደግም ሰው እንዲሁ ነው ( መጽሐፈ ምሳሌ 26 : 11 )

ሰነፍን በሙቀጫ ውስጥ ከእህል ጋር በዘነዘና ብትወቅጠው፥ ስንፍናው ከእርሱ አይርቅም ( መጽሐፈ ምሳሌ 27 : 22

Related image

         




 የተወደዳችሁ ወገኖች ዛሬ በዚህ ሃሳብ ላይ ጥቂት የጻፍኩት ነገር አለና ተከታተሉኝ ሰነፎች ስንሆን 

ባለጌዎች እንሆናለን ባለጌዎች ስንሆን ደግሞ ተሳዳቢዎች እንሆናለን እነዚህ ነገሮች ተያያዥነት ስላላቸው 

በአንድ ሰው ሕይወት ውስጥ ሲገለጡ ተያይዘውና ተከታትለው ነው የሚገለጡት ስንፍናም ሆነ ባለጌነት ደግሞ 

ሰው አይመርጥም በዕድሜ ለጋ ሕጻን ወጣት ጎልማሳ በመካከለኛ የዕድሜ ክልል ያለ ሙሉ ሰው ሽማግሌ አሮጊት 

አይልም እንደገናም ሃብታም ደሃ የተማረ ያልተማረ ሥልጣን ያለው ሥልጣን የሌለው ጥቁር ቀይ ነጭ ጠይም 

መልከ መልካም መልኩ የማያምር ረጅም አጭር ቀጭን ወፍራምና የመሳሰሉትን አይልም እነደየ ሰዉ ያለማደግ 

ሕይወትና የአስተሳሰብ ዝቅጠት ልክ ከፍ ብሎ ይታያል ተጎልጉሎም ይወጣል ይገለጣል ስንፍናም ሆነ ብልግና 

ከሰዎች ሕይወት ውስጥ ሊወገድ የሚችለው ሰዎች ከላይ እንደዘረዘርኩት ሃብታም ደሃ የተማሩ ያልተማሩ 


ሥልጣን ያላቸው ሥልጣን የሌላቸው እና የመሳሰሉትን ሲሆኑ ብቻ ሳይሆን በአስተሳሰብ ሲለወጡና ከፍ ብለው 


ሲገኙ ነው መጽሐፍ እንደሚነግረን ሰዎች ማለት አስተሳሰባቸው ማለት ናቸውና ምሳሌ 23 7 አስተሳሰባቸው 


ሲለወጥ ስንፍናቸውና ብልግናቸውም ያኔ ከእነርሱ ይሄዳል በሕይወታቸውም ሆነ በአመለካከታቸው ከፍ ብለው 


ይገኛሉ በሰዎች ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ የሚያመጣው ደግሞ የተገለጠው የእግዚአብሔር ቃል እውነት ነው 


ትንቢተ ኢሳይያስ 55 6 _ 12 የሉቃስ ወንጌል 7 29 _ 35 ከዚያ ውጪ እንደተባለውና በእግዚአብሔርም ቃል 


እንደተጻፈው ሰነፍን በሙቀጫ ውስጥ ከእህል ጋር በዘነዘና ብትወቅጠው፥ ስንፍናው ከእርሱ አይርቅም ይላልና 


መጽሐፈ ምሳሌ 27 22 ስንፍናው በማይለቀው በሰነፍ ሰው ባሕርይ መናደድም ሆነ መበሳጨት ፍጹም ሞኝነት 


ነው ለዚህም ነው እንግዲህ አንተ ደግሞ እርሱን እንዳትመስል ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት ሲል በዚሁ



በምሳሌ መጽሐፍ ላይ የእግዚአብሔር ቃል የነገረን ምሳሌ 26 4 ዳዊት ለናባል የነበረው ግምት የተለየ ስለነበረ 


ከባለሟሎቹ ጋር ሆኖ መንጋው በናባል እረኞች ሲጠበቅ ዳዊትና ባለሟሎቹ በቀንና በሌሊት አጥር ሆነውላቸው 


እንደነበር የእግዚአብሔር ቃል በግልጥነት ይነግረናል የናባል የመንጋው እረኞችም ከነዳዊት ጋር በነበሩበት ጊዜ 


ሁሉ አልተበደሉም ነበር በቀርሜሎስም በተቀመጡበት ዘመን ሁሉ ከመንጋው አንዳች አልጎደለባቸውም ነበር 


ነገር ግን ዳዊት ለናባል ያለው ይሄ ሁሉ ግምት የተበላሸው ናባል ያለውን ነገር ለዳዊት አላካፍልም ሲል 


የእምቢተኝነት አቋም በመያዙ ሳይሆን ከዚያ መልስ መጽሐፍ እንደሚነግረን እነሆ ዳዊት በምድረ በዳ ሳለ 


ጌታችንን ሊባርኩ መልዕክተኞችን ላከ እርሱ ግን ሰደባቸው ይለናል አያይዞም መጽሐፉ እነዚህ ሰዎች ግን በእኛ 


ዘንድ እጅግ መልካም ነበሩ አልበደሉንምም አለን 1 ሳሙኤል 25 በሙሉ ያንብቡት እንደገናም ቊጥር 14 _ 


17 የተጻፈውን ይመልከቱ ታድያ እጅግ መልካም ለነበሩና የስድብ ቃል ለማይገባቸው ለእነዚህ የተባረኩ ሰዎች 


የሀገር ሀብታም የሆነው አጅሬው ናባል ተራ የሆነ የስድብ ቃል ከአፉ አውጥቶ በመሳደብ ዳዊትን አሳዘነ 


የተወደዳችሁ ወገኖቼ መጽሐፉ ለምሳሌነትና እንድንማርበትም የባለጸጋውን ሰው የናባልን ቅሌት ይጠቁመን 


እንጂ ዛሬም በዘመናችን ናባልን የመሰሉ በሀብትና በባለጸግነት ብዛት በመንፈሳዊ የአገልግሎት ሥልጣንና 


ስምም ጭምር ተሸፍነው አንቱ የተባሉ ሰዎች ስማቸውም ሆነ ተግባራቸው እንዲሁም የሚያሳዩትና የሚያሰሙት 


ነገር በሙሉ ተዳምሮ ካሉበት ሁኔታ ጋር አብሮ የማይሄድ በመሆኑ ዛሬም ድረስ ባለጌ ናባሎች በከተማችንም ሆነ 


ባዓለማችን እንዲሁም በቤተክርስቲያን መድረክ ሳይቀር ያሉ ሁሉ ብዙዎች ናቸው ዳዊትን ያስቆጣውና ለበቀልም 


ያነሳሳው ነገር አንድና አንድ እንግዲህ ይሄ ነው የጠበቀው ቀርቶ ያልጠበቀውን መልስ ከናባል አንደበት ሰማ 


ዛሬም ታድያ በዓለማችንም ሆነ በምድራችን እንዲሁም በቤተክርስቲያን በሥልጣንና በገንዘብ በክብር በተሸፈነ 


ማንነት ውስጥ ሆነው ጤነኛና አዋቂ ከመሰሉ በሳሎችም ነን ሲሉ ራሳቸውን ካቀረቡ ናባሎች ዛሬም እንደዳዊት 


የጠበቅነው ቀርቶ ያልጠበቅነውን አሳፋሪ ነገር እንሰማለን እንደገናም ጆሮአችንን ሳይቀር እስኪሰቀጥጠን 


የሰማውንም ጆሮአችንን እስኪከብደውና የሰማው ጆሮዬ ነው ወይስ ሌላ ብለን እስክንጠራጠር ድረስ በጣም 


አሳፋሪ የሆነን ነገር ሰምተናል አይተናል ለወደፊቱም በብዙ እንሰማለን እናያለን ብዙ ናባሎች ከነብልግናቸውና 


ከነስድባቸውም ጭምር ከዚህም ሌላ ከሥልጣናቸውና ከሃብታቸው ከገንዘባቸውም ጋር አይነኬ ሆነው 


ተቀምጠዋል ለዚህም ነው መጽሐፍ ቅዱስ ናባልን ሰውየው ግን ባለጌ ነበረ ግብሩም ክፉ ነበረ እንዳለው 


እነዚህም ሰዎች ሃብትና ንብረት ሥልጣንም ጭምር እላያቸው ላይ ያለ ቢሆንም እንኳ እንደዚሁ እንደናባል 


የፋነኑ ሆነው በመገኘታቸው ክፉ ነገር ከሰው ሳይሆን ከባለቤቱ ከእግዚአብሔር እንዲመጣባቸው የተቆረጠ 


በመሆኑ ማንም ሊናገራቸው የማይችል ምናምንቴዎች ባለጌዎችና ክፉዎች ናቸው መጽሐፍቅዱስ 2 ነገሥት 


ምዕራፍ 5 1 ላይ ስለ ሶርያው ንጉሥ ስለ ንዕማን ሲናገር የሶርያ ንጉሥ ሠራዊት አለቃ ንዕማን እግዚአብሔር 


በእርሱ እጅ ለሶርያ ደኅንነትን ስለሰጠ በጌታው ዘንድ ታላቅ ክቡር ሰው ነበረ ደግሞም ጽኑዕ ኃያል ነበረ ነገር ግን 


ለምጻም ነበረ ይለናል ታድያ የንዕማንን ይሄን የመሰለ የታላቅነት የክቡርነት የጀግንነት ጽናትና ኃያልነት 


ያጠፋው በላዩ ላይ እየታየ ያለው ለምጻምነት ነው መጽሐፍቅዱስ አሁንም ንዕማንን ለምጻም ነበረ ይለናል ታድያ 


ንዕማን ይህንን በላዩ ላይ የተጣበቀውን ጸያፉን ለምጽ አውቆ ነው ነቢዩ ኤልሳዕን ፍለጋ ዮርዳኖስ ድረስ 


የወረደው ወርዶም አልቀረ ለነቢዩ ቃል ታዞና እሺ ብሎ ወደ ወንዙ ውስጥ በገባ ጊዜ ገላው እንደ ሕጻን ልጅ ገላ 


ሆኖና ተመልሶ ተፈወሰ 2 ነገሥት ምዕራፍ 5 በሙሉ ይመልከቱ ይሄ ፈውስ ታድያ በንዕማን ሳያበቃ ዛሬም ላይ 


በሥልጣን በገንዘብና በክብር ተሸፍነን አንቱ ለተባልን ስንገለጥ ደግሞ ከስንፍናችን ጋር ናባሎች ሆነንና ፈጠን 


ለተገኘን ሁሉ የማያዳግም ፈውስ ሆኖ በሕይወታችን እንዲመጣ የሁልጊዘም ጸሎቴ ነው ባለሥልጣኑ ንዕማን 


ገንዘቡ ሳያኮራው ሥልጣኑም ልቡን ሳይደፍነው ዮርዳኖስ ወንዝ ድረስ እንደሄደና ከነቢዩ አፍ በወጣው ቃል ታዞ 


ብቅ ትልቅ በማለት እንደተፈወሰ ሁሉ እኛም በሥልጣንና በገንዘብ የተሸፈነውን ማንነታችንን እና ሰዎችም 


የማያውቁትን እኛነታችንን ይዘን ሰዎች እኔን የበተክርስቲያን መሪና መጋቢ ሐዋርያና ነቢይ ሽማግሌና 


የመሣሠሉትን ይሉኛል የሚለውን በይሉኝታ የተያዘ የማዕረግ ከበሬታና እንዲሁም የኑሮ ከፍታ ሁሉ ወደ ጐን 


በማድረግ ከዮርዳኖስ ውሃ በሚበልጠውና ውጪያዊ ለምጽን ብቻ ሳይሆን የውስጥን ለምጽ ጭምር በሚያነጻው 


በክርስቶስ ደም ለመታጠብ ራሳችንን ብንሰጥ መጥተንም በክርስቶስ ደም ብንታጠብ ከዚህ ሁሉ ችግር 


እንላቀቃለን እግዚአብሔርን የሚያከብረው ነገር ገንዘባችን ሥልጣናችንና የአገልግሎት ስማችን ስመ ጥር 


የሆነውም እኛነታችንና አንቱታችን ሳይሆን የተፈወሰው ሕይወታችን ነው ይህ የተፈወሰው ሕይወታችን ደግሞ 


ለእግዚአብሔር ክብር የሚውል ብቻ ሳይሆን ለሰዎች ጥቅምም የሚሆን ነው ከዚያ ውጪ ግን በሕይወት ፈውስ 


እግዚአብሔር እንደ ንዕማን ሳይገናኘን እንዲሁ ከሀብታችንና ከስልጣናችን እንዲሁም ከተሰጠን የአገልግሎት 


ስማችን ጋር ተጎዝጉዘንና ተነስንሰን አንቱ ብቻ ተብለንም የምንከርም ከሆነ ግን አንድ ቀን የናባል ዕጣ ፈንታ 


የእኛም ይሆናል እንደገናም በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የምያስፈራ ነውና ዕብራውያን 10 26 _ 31 


እኛም እንደ ናባል ከእግዚአብሔር በሆነው በድንገተኛው ሞት ልንወሰድ እንችላለን 1 ሳሙኤል 25 38  


መዝሙር 72 ( 73 ) በሙሉ ምሳሌ 29 1 ምሳሌ 28 13 1 ዮሐንስ 1 5 _ 10 እግዚአብሔር ከዚህ ዓይነቱ 


አስከፊ ሞት ይጠብቀን ለንስሐም ሕይወት ያብቃን
Related imageImage result for 2 king 5





ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry

ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ

God bless u all





yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment