Monday 29 October 2018

Zemary hawaz newest song MECHE NEW መቼ ነው መቼ ነው ያለቅድመ ሁኔታ መቼ ነው በእምነት የምሰብክህ ጌታ መቼ ነው የዙርያዬን ረስቼው መቼ ነው ስለ እውነት የማደላው ዘማሪ ሐዋዝ ተገኔን እግዚአብሔር ይባርከው ወገኞቼስ ለእኛስ መቼ ነው ያለቅድመ ሁኔታ ጌታን የምንሰብከው ዘመኑ እኮ አጭር ነው የትኩረት አድማሶቻችንን ከሳበው ከንቱና ተራ ከሆነው ነገር ወጥተን እባካችሁ ይህንን ጌታን እንስበከው ኢየሱስ ያድናል እግዚአብሔር እንዴት ተቀበለን ? I - እግዚአብሔር ፍቅሩን በኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶ ተቀበለን በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠ የእግዚአብሔር ፍቅር  1ኛ ) በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና ( የዮሐንስ ወንጌል  3 : 16 ) 2ኛ ) ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል ( ሮሜ 5 ፥ 8 ) 3ኛ ) ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን ፥ በጸጋ ድናችኋልና ፥ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን ( ወደ ኤፌሶን ሰዎች  2 : 4 - 7 ) 4ኛ ) በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል ( 1ኛ የዮሐንስ መልእክት  4 9 - 11 ) II - ሰዎች ሊለማመዱት ፣ ሊገልጹትና ሊያሳዩት ያልቻሉት የእግዚአብሔር ፍቅር የማቴዎስ ወንጌል 18 ፥ 23 _ 35   አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment