Thursday 25 October 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 1 ) እግዚአብሔር እንዴት ተቀበለን ? ስለ ወደደን ተቀበለን :: ሀ ) መወደድ ( ትንቢተ ሚልክያስ 1 ፥ 2 ፤ ትንቢተ ዘካርያስ 10 ፥ 6 ) የዛሬው ትምህርት ትኩረት ሰጥቶ የሚናገረው ስለ መወደድ ነው በማስተዋል ተከታተሉ :: መወደዱ የገባው ሰው ደግሞ በቅዱስ አጠራሩ ጠርቶ ያዳነውን ጌታ ይጠራል እንጂ 2ኛ ጢሞቴዎስ 1 : 9 እንደገና ወደኋላ ተመልሶና የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ መውደድ ረስቶ ወይንም በእግዚአብሔር እንዳልተወደደ አድርጎ ራሱን በመቊጠር ነይ ነይ እምዬ ማርያም ፣ ናና ሚካኤል ፣ ናና ገብርኤል ፣ ናና ኡራኤል እና የመሣሠሉትን እያለ ሲጣራ አይገኝም :: ነይ ነይ እምዬ ማርያም ፣ ናና ሚካኤል እና ሌሎችንም ቅዱሳን መላዕክትንም ሆነ ቅዱሳንን ሰዎች አለመጥራት እነርሱን መጥላትና እነርሱንም አለመፈለግ እንዳልሆነ ሕዝባችን ሊረዳ ይገባዋል :: እኛ አምላክ ያለን እና አምላካችንም ልጆቹ አድርጎ የተቀበለን ሕዝቦቹ ስለሆንን ( 2ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 16 _ 18 ) ማርያምን ቅዱሳን ሰዎችንና ቅዱሳን መላዕክትን ሁሉ ስማቸውን አድሬስ በማድረግ እየተጣራን ወደ ማርያም ወደ ፍጡራን ሰዎችና ወደ መላዕክቱም ጭምር እንድንጸልይ መጽሐፍቅዱስ አያስተምረንም ተባረኩ :: ወስብሐት ለእግዚአብሔር ዘእንበለ ወላዲቱ ድንግል ወዘእንበለ መስቀሉ ክቡር ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment