Monday 29 October 2018

ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አዕምሮ ትርጉም ፦ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን ( ምንጭ ከቅዳሴ እግዚእ የተወሰደ)ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አዕምሮ ትርጉም ፦ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን ( ምንጭ ከቅዳሴ እግዚእ የተወሰደ) የቀደመችዋ ኦርቶዶክስ የያዘቻቸውን መጽሐፍቅዱሳዊ እውነቶች ለማሳየት ቅዳሴ ለኢየሱስ በሚል አርዕስት ከወንድማችን አባ ተክለማርያም ጋር በየሳምንቱ ቅዳሜ ባለን ፕሮግራም ጀምረን ቅዳሴ ሐዋርያትን በማጠናቀቅ ቅዳሴ እግዚእ ላይ ደርሰናል በዛሬው ዕለት የለቀቅነው ቪዲዮ ደግሞ በጣም አስደናቂና በውስጡም ትልቅ መልዕክት ያለው በመሆኑ ሰምታችሁ እንድትባረኩበት እነሆ ብለናል ትምህርቱ በየሳምንቱ ሳይቋረጥ ይቀጥላል ተባረኩ ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አዕምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን ዘወትር አንተን ያዩ ዘንድ ጆሮዎቻችንም ያንተን ብቻ ቃል ይሰሙ ዘንድ ( ምንጭ ከቅዳሴ እግዚእ የተወሰደ) በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው የሉቃስ ወንጌል 24: 45 ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1 : 18 - 19 አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment