Friday 5 October 2018

*⛪#በእንባቸው #ቤተክርስትያን #አደራ ይላሉ*��ብፁዕ አቡነ #ቀውስጦስ*��ማኅበረ ቅዱሳን ባዘጋጀው መናፍቃን ...ብጹዕ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ኢየሱስ በሰማይ ሆኖ ዛሬም ይማልዳል የሚለው ሃሳብ በጣም ስለከበዳቸው እኔ ግን ይጨንቀኛል ልጆቼ እንዳትሠረቁ ራሳችሁን ጠብቁ ሲሉ ለተጨነቁበትና ላለቀሱበት ጥብቅ የሆነ አደራቸውንም ላስተላለፉበት ቃለ ምዕዳን የተዘጋጀ መጽሐፍቅዱሳዊ ምላሽ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ፣ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናንና የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች በሙሉ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን እያልን ብጹዕ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ እኔ ግን ይጨንቀኛል ልጆቼ እንዳትሠረቁ ራሳችሁን ጠብቁ ሲሉ ለተጨነቁበትና ላለቀሱበት የኢየሱስ ክርስቶስ የማማለድ ሥራ ትክክለኛውን መልስ ልንሰጣቸውና ከጭንቀታቸውም ሆነ ከልቅሶአቸው ልንታደጋቸው እንዲሁም ሰራቂው እንደገናም ሌባው ማን እንደሆነ በቃሉ መሠረት ልናመለክታቸው ጊዜው በመሆኑ ምላሹን ለመስማት በሰዓታችሁ እንድትገኙ ከወዲሁ ጋብዘናችኋል እኛም ይህንን ምላሽ በሰዓታችን ተገኝተን ወደ እናንተ እስክናደርስ ድረስ ብጹዕ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ እንዲህ ተጨንቀው ያለቀሱበትን ቪዲዮ እናንተም በአግባቡ እንድትመለከቱትና ከምንሰጠውም ምላሽ ጋር በማገናዘብ ትክክለኛ የሆነውን አባቶችም ጭምር በእምነት መግለጫቸው ላይ የዘገቡትን እውነት እኛም እናሰማለን ከዚህም ሌላ ይህቺው የመጀመርያይቱ ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የቃሉን እውነት መነሻ አድርጋ በመጻሕፍቶችዋ ከዘገበቻቸው ሃሳቦች ጋር በጣምራነት አያይዘን ምላሻችንን ይዘን የምንቀርብ በመሆናችን ይህንን በመረጃ የተደገፈ ትምህርት ለመስማት በሰዓታችሁ እንድትገኙ ከወዲሁ ለማሳሰብ እንወዳለን ወይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment