Monday 29 October 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 2 ) እግዚአብሔር እንዴት ተቀበለን ? I - እግዚአብሔር ፍቅሩን በኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶ ተቀበለን በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠ የእግዚአብሔር ፍቅር 1ኛ ) በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና ( የዮሐንስ ወንጌል 3 : 16 ) 2ኛ ) ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል ( ሮሜ 5 ፥ 8 ) 3ኛ ) ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን ፥ በጸጋ ድናችኋልና ፥ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን ( ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 : 4 - 7 ) 4ኛ ) በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል ( 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4 9 - 11 ) II - ሰዎች ሊለማመዱት ፣ ሊገልጹትና ሊያሳዩት ያልቻሉት የእግዚአብሔር ፍቅር የማቴዎስ ወንጌል 18 ፥ 23 _ 35 አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አዕምሮ ትርጉም ፦ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን ( ምንጭ ከቅዳሴ እግዚእ የተወሰደ)ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አዕምሮ ትርጉም ፦ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን ( ምንጭ ከቅዳሴ እግዚእ የተወሰደ) የቀደመችዋ ኦርቶዶክስ የያዘቻቸውን መጽሐፍቅዱሳዊ እውነቶች ለማሳየት ቅዳሴ ለኢየሱስ በሚል አርዕስት ከወንድማችን አባ ተክለማርያም ጋር በየሳምንቱ ቅዳሜ ባለን ፕሮግራም ጀምረን ቅዳሴ ሐዋርያትን በማጠናቀቅ ቅዳሴ እግዚእ ላይ ደርሰናል በዛሬው ዕለት የለቀቅነው ቪዲዮ ደግሞ በጣም አስደናቂና በውስጡም ትልቅ መልዕክት ያለው በመሆኑ ሰምታችሁ እንድትባረኩበት እነሆ ብለናል ትምህርቱ በየሳምንቱ ሳይቋረጥ ይቀጥላል ተባረኩ ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አዕምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን ዘወትር አንተን ያዩ ዘንድ ጆሮዎቻችንም ያንተን ብቻ ቃል ይሰሙ ዘንድ ( ምንጭ ከቅዳሴ እግዚእ የተወሰደ) በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው የሉቃስ ወንጌል 24: 45 ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1 : 18 - 19 አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

Zemary hawaz newest song MECHE NEW መቼ ነው መቼ ነው ያለቅድመ ሁኔታ መቼ ነው በእምነት የምሰብክህ ጌታ መቼ ነው የዙርያዬን ረስቼው መቼ ነው ስለ እውነት የማደላው ዘማሪ ሐዋዝ ተገኔን እግዚአብሔር ይባርከው ወገኞቼስ ለእኛስ መቼ ነው ያለቅድመ ሁኔታ ጌታን የምንሰብከው ዘመኑ እኮ አጭር ነው የትኩረት አድማሶቻችንን ከሳበው ከንቱና ተራ ከሆነው ነገር ወጥተን እባካችሁ ይህንን ጌታን እንስበከው ኢየሱስ ያድናል እግዚአብሔር እንዴት ተቀበለን ? I - እግዚአብሔር ፍቅሩን በኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶ ተቀበለን በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠ የእግዚአብሔር ፍቅር  1ኛ ) በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና ( የዮሐንስ ወንጌል  3 : 16 ) 2ኛ ) ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል ( ሮሜ 5 ፥ 8 ) 3ኛ ) ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን ፥ በጸጋ ድናችኋልና ፥ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን ( ወደ ኤፌሶን ሰዎች  2 : 4 - 7 ) 4ኛ ) በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል ( 1ኛ የዮሐንስ መልእክት  4 9 - 11 ) II - ሰዎች ሊለማመዱት ፣ ሊገልጹትና ሊያሳዩት ያልቻሉት የእግዚአብሔር ፍቅር የማቴዎስ ወንጌል 18 ፥ 23 _ 35   አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

እግዚአብሔር እንዴት ተቀበለን ?


I - እግዚአብሔር ፍቅሩን በኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶ ተቀበለን



በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠ የእግዚአብሔር ፍቅር



handGod.jpg
1 ) በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና 


                               ( የዮሐንስ ወንጌል  3 : 16 )



2 ) ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል 

                                       ( ሮሜ 5 8 )


3 ) ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን በጸጋ ድናችኋልና በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን ( ወደ ኤፌሶን ሰዎች  2 : 4 - 7 ) 


4 ) በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል 


                            ( 1 የዮሐንስ መልእክት  4 9 - 11 )




II - ሰዎች ሊለማመዱት ሊገልጹትና ሊያሳዩት ያልቻሉት የእግዚአብሔር ፍቅር 

የማቴዎስ ወንጌል 18 23 _ 35 



slide_2.jpg
Screen-Shot-2018-03-19-at-9.00.33-PM.png



አባ ዮናስ ጌታነህ 


ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት 

Saturday 27 October 2018

አጠር ያለ የግጥም መነባንብ :- የተክለ ሃይማኖት ወዮታ የተክለ ሃይማኖት ወዮታ የገድሉን ሐሰተኝነት በሚያጋልጥ መልኩ ከተክለሐይማኖት ገድል ተውጣጥቶ እና በወንጌሉ እውነት ተቃኝቶ የቀረበ የግጥም መነባንብ መልካም የንባብ ጊዜ ይሁንልዎት!!! ወዮልኝ ወዮታ አለብኝ ለሰዎች ብርሃን ያበራሁኝ መስሎኝ በጨለማ ኖሬ ለራሴ ጨለምኩኝ ከንቱ ግብዝነት ይዞኝ ስንቀባረር ክህነቴን በሰማይ አድርጌው ለመኖር ክንፎችን ገጥሜ በግራና በቀኝ የሰማይ ካህን ነው ራሴን አስባልኩኝ ነገር ግን ክንፎቹ የውሸት ነበሩ ለይምሰል ተስለው ተሰክተው የቀሩ እንደ ዶሮ ላባ ድንገት ሲነቀሉ በወንጌሉ እውነት ዳግም ላያበቅሉ እኔም ተሳቅቄ ወዮልኝም አልኩኝ ሥራዬን ገልጠውት ከሹመት ሲሽሩኝ የሰዎችን ኃጢአት ይቅርም ለማስባል የሚንበረከክ ነው ሲጸልይ የሚውል ማንም ያልሰራውን ሰርተኸዋል ሲሉኝ ተብዬ ስወደስ ሰዎች ሲያሞካሹኝ በጌቴሴማኒ የተንበረከከው ሥርየት ለማሰጠት ደሙን ያፈሰሰው ደም ሳይፈስ ሥርየት ፍጹም አይገኝም በመንበርከክ ጸሎት ማንም አያመጣም ብሎ ተናገረኝ ውሸታም ነህ ብሎ ሥራዬን አጋልጦ ተንኮሌን ፈንቅሎ ላሞች ባልዋሉበት የኩበት ለቀማ ራሴን ሰቅዬ በጸሎቱ ማማ እግሬ የተቆረጠው ስጸልይ ነው አልኩኝ በገድል በድርሣኑ ራሴን ከመርኩኝ እውነቱ ሲነገር ታሪክ ሌላ ሆነ እኔም ተጋለጥኩኝ ስሜም ተኮነነ መንግሥትን ከላስታ ወደ ሸዋ ምድር ለማዞር ፈልጌ ስዶልት ስመክር ገድለህ ንገሥ ብዬ ንጉሡን ሳሳብር የዶሮውን ጩኸት ትርጉሙን አውቃለሁ እያልኩ ስቀሰቅስ ሳዳምቅ እያለሁ ድንገት በጦርነት እግሬ ተሰበረ የጸሎት ሰው ሲሉኝ ስሜም የከበረ ዛሬስ ተዋረድኩኝ ገበናዬም ወጣ ብዬ አለቀስኩኝ ባመጣሁት ጣጣ የመጨረሻዬ የተቅማጥ በሽታ የመጨረሻዬ የወባ በሽታ ከዚህ ምድር ይዞኝ ሊወስደኝ በአንድ አፍታ እስቲ ስሜን ላድስ በፍጻሜው ሰዓት በዚህ በተቅማጡ ከመሞቴ በፊት ብዬ አሰብኩና ኪዳኑን በሰማይ ከኢየሱስ ደም ጋራ ላያይዘው በላይ መዋሸት ጀመርኩኝ ዳግመኛ ሳላፍር እንደ ስቅለቱ ደም ተቅማጤን ላስቆጥር በገዳም የሞተ በወባ በሽታ ይድናል አይጠፋም ይኖራል በደስታ በመላዕክት ዓለም በሆታ በእልልታ በመንግሥተ ሰማይ በላይኛው ጌታ ነገር ግን አንዳንዱ አቃሎት ነገሬን ከሰማኝ በኋላ የባልቴት ተረቴን በያደባባዩ ደግሞ ሊያሳፍረኝ መደበቅያ ሥፍራ ቦታም አሳጥቶኝ በወንጌሉ እውነት በርብሮ ገለጠኝ የመቀበርያዬም ጊዜያቱ ደረሰ ሳልፈልገው በግድ ጉድጓዴ ተማሰ እኔም ከዚህ ወዲያ ይበቃኛል አልኩኝ ዳግም ላልተነፍስ መቃብር ወረድኩኝ እፎይ ያለው ትውልድ ይኸው ተቀስቅሶአል የወንጌል ደመራው ችቦው ተለኩሶአል ጆሮ ያለው ይስማ ኢየሱስ ያድናል ወስብሐት ለእግዚአብሔር ዘእንበለ ወላዲቱ ድንግል ወዘእንበለ መስቀሉ ክቡር ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት ለግጥሞቹ የተጠቀምኩበት መረጃዎች የሚከተሉት ናቸው ያንብቡአቸው ዕብራውያን 12 ፥ 24 , ቅዳሴ ሐዋርያት ገጽ 122 ፥ 106 , የተክለ ሐይማኖት ስብሐተ ፍቁር ገጽ 214 , የተክለ ሐይማኖት ስብሐተ ፍቁር ገጽ 2116 , ዕብራውያን 10 ፥ 29 - 31 , በ13ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ በላስታ ያለውን የዛጉዬን መንግሥት ወደ ሸዋ ለመመለስ ባካሄደው መፈንቅለ መንግሥት , ገድለተክለሐይማኖት ምዕራፍ 27 ፥ 15 ፣ 17 , 1ኛ ቆሮንቶስ 1 ፥ 7 ፣ ኤፌሶን 1 ፥ 7 , ኅዳር 24 ፥ ገጽ 78 , ዕብራውያን 9 ፥ 22 ፣ ኤፌሶን 1 ፥ 7 ፣ ሮሜ 5 ፥ 6 _ 10 , ገድለ ተክለሐይማኖት ምዕራፍ 57 , ገድለ ተክለሐይማኖት ትንሣኤ የመጻሕፍት አሳታሚ ድርጅት ሦስተኛ እትም 1973 የታተመ ምዕራፍ 56 ቊጥር 1 - 3 ገጽ 175 ,

Thursday 25 October 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 1 ) እግዚአብሔር እንዴት ተቀበለን ? ስለ ወደደን ተቀበለን :: ሀ ) መወደድ ( ትንቢተ ሚልክያስ 1 ፥ 2 ፤ ትንቢተ ዘካርያስ 10 ፥ 6 ) የዛሬው ትምህርት ትኩረት ሰጥቶ የሚናገረው ስለ መወደድ ነው በማስተዋል ተከታተሉ :: መወደዱ የገባው ሰው ደግሞ በቅዱስ አጠራሩ ጠርቶ ያዳነውን ጌታ ይጠራል እንጂ 2ኛ ጢሞቴዎስ 1 : 9 እንደገና ወደኋላ ተመልሶና የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ መውደድ ረስቶ ወይንም በእግዚአብሔር እንዳልተወደደ አድርጎ ራሱን በመቊጠር ነይ ነይ እምዬ ማርያም ፣ ናና ሚካኤል ፣ ናና ገብርኤል ፣ ናና ኡራኤል እና የመሣሠሉትን እያለ ሲጣራ አይገኝም :: ነይ ነይ እምዬ ማርያም ፣ ናና ሚካኤል እና ሌሎችንም ቅዱሳን መላዕክትንም ሆነ ቅዱሳንን ሰዎች አለመጥራት እነርሱን መጥላትና እነርሱንም አለመፈለግ እንዳልሆነ ሕዝባችን ሊረዳ ይገባዋል :: እኛ አምላክ ያለን እና አምላካችንም ልጆቹ አድርጎ የተቀበለን ሕዝቦቹ ስለሆንን ( 2ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 16 _ 18 ) ማርያምን ቅዱሳን ሰዎችንና ቅዱሳን መላዕክትን ሁሉ ስማቸውን አድሬስ በማድረግ እየተጣራን ወደ ማርያም ወደ ፍጡራን ሰዎችና ወደ መላዕክቱም ጭምር እንድንጸልይ መጽሐፍቅዱስ አያስተምረንም ተባረኩ :: ወስብሐት ለእግዚአብሔር ዘእንበለ ወላዲቱ ድንግል ወዘእንበለ መስቀሉ ክቡር ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

Sunday 14 October 2018

የተክለ ሃይማኖት ወዮታ 


የገድሉን ሐሰተኝነት በሚያጋልጥ መልኩ ከተክለሐይማኖት ገድል ተውጣጥቶ እና በወንጌሉ እውነት ተቃኝቶ  የቀረበ የግጥም መነባንብ 



መልካም የንባብ ጊዜ ይሁንልዎት!!!




ወዮልኝ 

ወዮታ አለብኝ 

ለሰዎች ብርሃን ያበራሁኝ መስሎኝ 

በጨለማ ኖሬ ለራሴ ጨለምኩኝ 

ከንቱ ግብዝነት ይዞኝ ስንቀባረር 

ክህነቴን በሰማይ አድርጌው ለመኖር 

ክንፎችን ገጥሜ በግራና በቀኝ 

የሰማይ ካህን ነው ራሴን አስባልኩኝ 

ነገር ግን ክንፎቹ የውሸት ነበሩ 

ለይምሰል ተስለው ተሰክተው የቀሩ 

እንደ ዶሮ ላባ ድንገት ሲነቀሉ 

በወንጌሉ እውነት ዳግም ላያበቅሉ 

እኔም ተሳቅቄ ወዮልኝም አልኩኝ 

ሥራዬን ገልጠውት ከሹመት ሲሽሩኝ 

የሰዎችን ኃጢአት ይቅርም ለማስባል 

የሚንበረከክ ነው ሲጸልይ የሚውል 

ማንም ያልሰራውን ሰርተኸዋል ሲሉኝ 

ተብዬ ስወደስ ሰዎች ሲያሞካሹኝ

በጌቴሴማኒ የተንበረከከው 

ሥርየት ለማሰጠት ደሙን ያፈሰሰው 

ደም ሳይፈስ ሥርየት ፍጹም አይገኝም 

በመንበርከክ ጸሎት ማንም አያመጣም 

ብሎ ተናገረኝ ውሸታም ነህ ብሎ

 ሥራዬን አጋልጦ ተንኮሌን ፈንቅሎ 

ላሞች ባልዋሉበት የኩበት ለቀማ

ራሴን ሰቅዬ በጸሎቱ ማማ 

እግሬ የተቆረጠው ስጸልይ ነው አልኩኝ 

በገድል በድርሣኑ ራሴን ከመርኩኝ 

እውነቱ ሲነገር ታሪክ ሌላ ሆነ 

እኔም ተጋለጥኩኝ ስሜም ተኮነነ

መንግሥትን ከላስታ ወደ ሸዋ ምድር 

ለማዞር ፈልጌ ስዶልት ስመክር 

ገድለህ ንገሥ ብዬ ንጉሡን ሳሳብር 

የዶሮውን ጩኸት ትርጉሙን አውቃለሁ 

እያልኩ ስቀሰቅስ ሳዳምቅ እያለሁ 

ድንገት በጦርነት እግሬ ተሰበረ 

የጸሎት ሰው ሲሉኝ ስሜም የከበረ 

ዛሬስ ተዋረድኩኝ ገበናዬም ወጣ 

ብዬ አለቀስኩኝ ባመጣሁት ጣጣ 

የመጨረሻዬ የተቅማጥ በሽታ 

የመጨረሻዬ የወባ በሽታ 

ከዚህ ምድር ይዞኝ ሊወስደኝ በአንድ አፍታ 

እስቲ ስሜን ላድስ በፍጻሜው ሰዓት 

በዚህ በተቅማጡ ከመሞቴ በፊት 

ብዬ አሰብኩና ኪዳኑን በሰማይ 

ከኢየሱስ ደም ጋራ ላያይዘው በላይ 

መዋሸት ጀመርኩኝ ዳግመኛ ሳላፍር 

እንደ ስቅለቱ ደም ተቅማጤን ላስቆጥር 

በገዳም የሞተ በወባ በሽታ 

ይድናል አይጠፋም ይኖራል በደስታ 

በመላዕክት ዓለም በሆታ በደስታ 

በመንግሥተ ሰማይ በላይኛው ጌታ 

ነገር ግን አንዳንዱ አቃሎት ነገሬን 

ከሰማኝ በኋላ የባልቴት ተረቴን 

በያደባባዩ ደግሞ ሊያሳፍረኝ 

መደበቅያ ሥፍራ ቦታም አሳጥቶኝ 

በወንጌሉ እውነት በርብሮ ገለጠኝ 

የመቀበርያዬም ጊዜያቱ ደረሰ 

ሳልፈልገው በግድ ጉድጓዴ ተማሰ 

እኔም ከዚህ ወዲያ ይበቃኛል አልኩኝ 

ዳግም ላልተነፍስ መቃብር ወረድኩኝ 

እፎይ ያለው  ትውልድ ይኸው ተቀስቅሶአል 

የወንጌል ደመራው ችቦው ተለኩሶአል 

ጆሮ ያለው ይስማ ኢየሱስ ያድናል  


ወስብሐት ለእግዚአብሔር 
ዘእንበለ ወላዲቱ ድንግል 
ወዘእንበለ መስቀሉ ክቡር 

ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ 


ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት 

Monday 8 October 2018

የመልዕክት ርዕስ ፦———— ክፍል አንድ መልዕክት ፦ ልጄ ሆይ ለእሥራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥየመልዕክት ርዕስ ፦———— ክፍል አንድ መልዕክት ፦ ልጄ ሆይ ለእሥራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ ኢያሱም አካንን ልጄ ሆይ ለእሥራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ ለእርሱም ተናዘዝ ያደረግኸውንም ንገረኝ አትሸሽገኝ አለው የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላምለእናንተ ይሁን በእነዚህ በሁለት ቀናት ማለትም ዛሬ ሰኞና ሐሙስ የምንመለከታቸው ሃሳቦች 1ኛ ) ክፍል አንድ መልዕክት ፦ ልጄ ሆይ ለእሥራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ 2ኛ ) ክፍል ሁለት መልዕክት ፦ ለእርሱም ተናዘዝ ያደረግኸውንም ንገረኝ አትሸሽገኝ የሚሉ ናቸው የክፍሉም ምንባብ በአጭሩ እንዲህ የሚል ነው ኢያሱም አካንን ልጄ ሆይ ለእሥራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ ለእርሱም ተናዘዝ ያደረግኸውንም ንገረኝ አትሸሽገኝ አለው ( ኢያሱ 7 ፥ 19 ፣ ያዕቆብ 5 ፥ 16 ) የሃሳቡን ሙሉ ክፍል ለማግኘት ኢያሱ ምዕራፍ 7 ን በሙሉ አንብቡት በዛሬው ዕለት ግን የተመለከትነው ልጄ ሆይ ለእሥራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ የሚል ነው :: ይሁን እንጂ ታድያ ለእግዚአብሔር ክብር መስጠት ብዙ ዓይነት ሲሆን አካን በኢያሱ አማካኝነት ለእግዚአብሔር ክብር ስጥ የተባለበት እውነት ግን ከሁሉ የሚበልጥ መሆኑን ፣ በዚህ ውስጥ ሆኖ ለእግዚአብሔር ክብር መስጠት ማለት ደግሞ መሸነፍም ሆነ መዋረድ አለመሆኑን ፣ ከዚህም ሌላ ሁሉም ነገር ከዚህ የሚጀምር መሆኑን ፣ በዚህም ጉዳይ ታድያ አሁንም ክብር የምንሰጠው እንደ አካንም ሆነ እንደ ዳዊት ክብር ስጡ ተብለንና ተወትውተን ፣ ግዴታም መጥቶብን ሳይሆን እራሳችን ገብቶንና ፈቅደን አውቀንም ክብር ስንሰጥ እግዚአብሔር ራሱ በአደባባይ እንደሚያከብረን ነው የተማማርነው :: ለዚህ መልዕክት አጋዥ የሚሆን ሰሙኑን የተለቀቀ ቪዲዮ አለ ሊንኩን ከመልዕክቴ ጋር አያይዤ ልኬላችኋለሁ ተመልከቱት ብዙ ትማሩበታላችሁ UNBELIEVABLE!! A FIGHT breaks out in AMI - Accurate Prophecy with Alph LUKAU https://youtu.be/0g20ezp91S0 ለቀጣዩ የትምህርት ክፍለ ጊዜ እስከምንገናኝ ሰላም ሁኑልኝ ተባረኩ በማለት የምሰናበታችሁ ወንድማችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ ነኝ ከጸአተ ግብጽ አኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

Friday 5 October 2018

*⛪#በእንባቸው #ቤተክርስትያን #አደራ ይላሉ*��ብፁዕ አቡነ #ቀውስጦስ*��ማኅበረ ቅዱሳን ባዘጋጀው መናፍቃን ...ብጹዕ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ኢየሱስ በሰማይ ሆኖ ዛሬም ይማልዳል የሚለው ሃሳብ በጣም ስለከበዳቸው እኔ ግን ይጨንቀኛል ልጆቼ እንዳትሠረቁ ራሳችሁን ጠብቁ ሲሉ ለተጨነቁበትና ላለቀሱበት ጥብቅ የሆነ አደራቸውንም ላስተላለፉበት ቃለ ምዕዳን የተዘጋጀ መጽሐፍቅዱሳዊ ምላሽ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ፣ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናንና የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች በሙሉ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን እያልን ብጹዕ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ እኔ ግን ይጨንቀኛል ልጆቼ እንዳትሠረቁ ራሳችሁን ጠብቁ ሲሉ ለተጨነቁበትና ላለቀሱበት የኢየሱስ ክርስቶስ የማማለድ ሥራ ትክክለኛውን መልስ ልንሰጣቸውና ከጭንቀታቸውም ሆነ ከልቅሶአቸው ልንታደጋቸው እንዲሁም ሰራቂው እንደገናም ሌባው ማን እንደሆነ በቃሉ መሠረት ልናመለክታቸው ጊዜው በመሆኑ ምላሹን ለመስማት በሰዓታችሁ እንድትገኙ ከወዲሁ ጋብዘናችኋል እኛም ይህንን ምላሽ በሰዓታችን ተገኝተን ወደ እናንተ እስክናደርስ ድረስ ብጹዕ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ እንዲህ ተጨንቀው ያለቀሱበትን ቪዲዮ እናንተም በአግባቡ እንድትመለከቱትና ከምንሰጠውም ምላሽ ጋር በማገናዘብ ትክክለኛ የሆነውን አባቶችም ጭምር በእምነት መግለጫቸው ላይ የዘገቡትን እውነት እኛም እናሰማለን ከዚህም ሌላ ይህቺው የመጀመርያይቱ ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የቃሉን እውነት መነሻ አድርጋ በመጻሕፍቶችዋ ከዘገበቻቸው ሃሳቦች ጋር በጣምራነት አያይዘን ምላሻችንን ይዘን የምንቀርብ በመሆናችን ይህንን በመረጃ የተደገፈ ትምህርት ለመስማት በሰዓታችሁ እንድትገኙ ከወዲሁ ለማሳሰብ እንወዳለን ወይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ

Wednesday 3 October 2018

Hail Gebrselassie vs. Paul Tergat Sydney 2000 ሀይሌ በ ፖል ቴርጋት ሲገፋ የመልዕክት ርዕስ : — የሚያስቀሩ የመሰሉ ሰዎች አያስቀሩህም 1ኛ ሳሙኤል 17 ፥ 1 — 58 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቅዱሳን ሰላም ለእናንተ ይሁን :: ይህንን መልዕክት በፌስቡክ ላይቭ ላይ ሰርቼ ለቅቄዋለሁ ፣ በዩቲዩብ ፔጄም ላይ ተቀምጦላችኋልና መመልከት ትችላላችሁ :: ይሁን እንጂ መልዕክቱ ጠቀሜታነት ያለው ስለሆነ አሁንም በጽሑፌ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ :: ብዙ ጊዜ ሰዎችን በማስቀረት የሚታወቁ ሰዎች ከድልና ከማሸነፍ የቀሩ ፣ የማሸነፉም ሆነ የድሉ ተስፋ ያመለጣቸውና ሊሆንላቸውም ያልቻሉ ሰዎች ናቸው :: በዚህ ትምህርቴ ላይ የአትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴና የኬንያዊውን ሯጭ ፖልቴርጋትን ውዽድር አስመልክቶ ባለቀ ሰዓት ኃይሌ ኬንያዊውን ሯጭ አልፎት ሊያሸንፈው በሮጠ ጊዜ የደረሰበትን ቡጢ አስመልክቶ በዩቲዩብ የተለቀቀውን ቪዲዮ ለትምህርታችን እንዲሆን እነሆ ብያለሁ :: ለተጨማሪ መረጃ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴን መጠየቅ ይቻላል :: ታድያ እንግዲህ ከሩጫው ፍጻሜ መልስ ያለውን የኃይሌና የኬንያዊውን ሯጭ ግንኙነት ባላውቅም ፣ አንዳንዶች እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች በስንፍናቸው ምክንያት ካመለጣቸው ተደጋጋሚ ድል የተነሳ ሕይወታቸው በቊጭትና በንዴት ሳይቀር የተሞላ በመሆኑ ቀደመ ብለው ያሰቡትን ወንድማቸውን አይደለም ክርክር ፣ ጥል ፣ ድብድብ ጌታ አይፈቅድላቸውም እንጂ በሞት እንኳ ሳይቀር ሊያስቀሩ ወደኋላ የማይሉ ናቸው :: ይህንን ያልኩበትን ምክንያት ከመጽሐፍቅዱስ አስረጂ አቀርባለሁና ተከታተሉኝ :: ከክፍሉ ምንባብ እንደምንመለከተው ዳዊትን ታላቅ ወንድሙ ኤልያብ ከድሉ ሠፈር በጥል ነበር ሊያስቀረው የተነሳው :: ቊጣው በዳዊት ላይ ነዶ ለምን ወደዚህ ወረድህ ?እነዚያንስ ጥቂት በጎች በምድረ በዳ ለማን ተውሃቸው ? እኔ ኲራትህንና የልብህን ክፋት አውቃለሁና ሰልፉን ለማየት መጥተሃል አለው ይለናል :: ዳዊት ግን የነገሩን መንስዔ ወንድሙም ኤልያብ ይህንን የነደደ ቊጣ በላዩ ላይ ያወረደበትን መነሾ በትክክል የተረዳ በመሆኑ እኔ ምን አደረግሁ ይህ ታላቅ ነገር አይደለምን ? በማለት ከእርሱ ወደ ሌላ ዘወር አለ :: እንደዚህም ያለ ነገር ተናገረ :: ሕዝቡም እንደ ቀድሞ ያለ ነገር መለሱለት ይለናል :: ዳዊትስ በነደደበት ቊጣ ምክንያት በወንድሙ በኩል የመደመጥ ዕድሉን ባያገኝም ዘወር ብሎ ግን ሊሰሙትም ሆነ ሊያዳምጡት ከሚችሉ ጋር ተነጋገረ :: አንዳንድ ጊዜ እኮ ዘወር ልበል ቢባል እንኳ የማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ ይገባል :: የሁለቱ ወንድማማቾች የያዕቆብና የኤሳው ሕይወት የሚያስተምረን ይህንን እውነት ነው :: ኤሳው ከቊጣና ከጥል ባለፈ ሁኔታ ያዕቆብን አባቱ ስለባረከው ብቻ በያዕቆብ ላይ ቂም ያዘበት :: ዔሳውም በልቡ አለ ለአባቴ የልቅሶ ቀን ቀርቦአል :: ከዚያም በኋላ ወንድሜን ያዕቆብን እገድለዋለሁ አለ :: ታድያ ሁለቱ ወንድማማቾች ያዕቆብና ኤሳው በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉ ነው ለርብቃም ይህ የታላቁ ልጅዋ የዔሳው ቃል የደረሰላት :: ቃሉ እንደሚነግረን ታናሹን ልጅዋን ያዕቆብንም አስጠርታ አስመጣችው ፣ አለችውም :: እነሆም ወንድምህ ዔሳው ሊገድልህ ይፈቅዳል አሁንም ልጄ ሆይ ቃሌን ስማ ፣ ተነሣና ወደ ካራን ምድር ወደ ወንድሜ ወደ ላባ ሂድ ፣ በእርሱ ዘንድ ጥቂት ቀን ተቀመጥ ፣ የወንድምህ ቊጣ እስኪበርድ ድረስ ፣ የወንድምህ ቊጣ ከአንተ እስኪመለስ ድረስ ፣ ያደረግህበትንም እስኪረሳው ድረስ ከዚያም ልኬ አስመጣሃለሁ :: በአንድ ቀን ሁለታችሁን ለምን አጣለሁ ? በማለት ታናሹ ልጁዋን ስትማጸነው እንመለከታለን ዘፍጥረት 27 ፥ 41 _ 46 :: ውድ ወገኖቼ ሆይ ከዚህ ምንባብ እንደተመለከትነው ማስቀረትን በተመለከተ በተለይም በአንዳንዶች ዘንድ በአጭሩ ልንገታው አንችልም መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት ካልመጣ በስተቀር እውነተኛ ፍቅር ፣ እውነተኛ እርቅና ስምምነት ጭምር አይመጣምና ፣ እውነተኛ ፍቅርና እውነተኛ እርቅ ትክክለኛም ስምምነት እናምጣ በማለት አንለውጠውም :: ከዚህ የተነሳ የሚያስቀሩ ሰዎች አይነኬ በመሆናቸው በልባቸው ከፍ ብለውና ቃላቸውንም አስረዝመው የሚናገሩ ናቸውና ወንድሞቻቸውን እስከመግደል ደርሰው በሞት ሊያስቀሩ የሚችሉበትን ሁኔታ ይፈጥራሉ :: ነገር ግን አሁንም መቅደም ያለባቸው ሰዎች መቅደም ያለባቸው ሆነው ከተገኙና ከእግዚአብሔር ከሆኑ በሞት ጥላ መካከል እንኳ ቢሄዱ አልፈው ይቀድማሉ እንጂ የትኛውም ኃይል አቅም አግኝቶ እነርሱን የሚስቀራቸው አይሆንም :: የሐማና የመርዶክዮስ ታሪክም የሚያስታውሰን አሁንም ይህንኑ እውነት ነው :: ሐማም መርዶክዮስ እንዳልተደፋለት እንዳልሰገደለትም ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጣ ፣ የመርዶክዮስንም ወገን ነግረውት ነበርና በመርዶክዮስ ብቻ እጁን ይጭን ዘንድ በዓይኑ ተናቀ :: ሐማም በአርጤክሲስ መንግሥት ሁሉ የነበሩትን የመርዶክዮስን ሕዝብ አይሁድን ሊያጠፋ ፈለገ ይለናል ( አስቴር 3 ፥ 1 — 7 ) ይህ ብቻ አይደለም ከዚህም ሌላ ሐማ መርዶክዮስን መናቁ ሳያንሰው ፣ በዓይኑ እንኳ ሊያየው የማይፈልገውና የጠላው መሆኑን ለመናገር ፈልጎ አስቴር ለግብዣ የጠራችው መሆንዋን ለዘመዶቹ በኩራት ሆኖ በማውሳት ፣ ንግሥቲቱ አስቴር ወዳዘጋጀችው ግብዣ ከእኔ በቀር ከንጉሡ ጋር ማንንም አልጠራችም ፤ ደግሞ ነገ ከንጉሡ ጋር ወደ እርስዋ ተጠርቻለሁ ፣ ነገር ግን አይሁዳዊው መርዶክዮስ በንጉሡ በር ተቀምጦ ካየሁ ይህ ሁሉ ለእኔ ምንም አይጠቅምም ሲል ተናገረ :: ሚስቱም ዞሳራና ወዳጆቹ ሁሉ፦ ቁመቱ አምሳ ክንድ የሆነ ግንድ ይደረግ፥ ነገም መርዶክዮስ ይሰቀልበት ዘንድ ለንጉሡ ተናገር፤ ደስም ብሎህ ከንጉሡ ጋር ወደ ግብዣው ግባ አሉት ነገራቸውም ሐማን ደስ አሰኘው፥ ግንዱንም አስደረገ ይለናል :: ይህንን ምንባብ ስናይ እንግዲህ ማስቀረት ክፉኛ በሆነ ጥላቻ ውስጥ ገብቶ ፣ ለዓይን እንኳ ሳይቀር ለማየት ባለመፍቀድና በመሣሠሉትም ጭምር የሚያባራ አለመሆኑንና እስከ ሞት ድረስ የሚሄድ መሆኑን ነው የምንመለከተው :: የሚያስቀሩ ሰዎች አይሆንላቸውም ፣ ጌታም አይፈቅድላቸውም እንጂ ልባቸው ትልቅ ነው :: ነገር ግን ሊያስቀሩ ባዘጋጁት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ እነርሱ ይቀራሉ :: ከዚህ የተነሳ እናስቀራለን ሲሉ የተነሱ ሰዎች እናስቀራለን ሲሉ ያዘጋጁት ነገር ሁሉ ለእኛ የመሸጋገርያ ድልድይ ሲሆን ፣ ለእነርሱ ግን መቅሪያ ብቻ ሳይሆን መቀበርያቸውም ይሆናል :: ለዚህ ነው አንዳንዱ ሳያውቀው የራሱን መሞቻና የመቀበርያ ጉድጓድ የሚምሰው ( መጽሐፈ አስቴር ምዕራፍ 5 ፤ 6 እና 7 ን በሙሉ ተመልከቱ ) :: ወገኖቼ ሆይ መልዕክቴን ስጠቀልለው ቤተክርስቲያንንም ሆነ ሀገርን ለመጥቀም ለተነሱ ሰዎች በክፋታችን ምክንያት ሊደርሱ ካለው የራዕያቸው ፍጻሜ ደርሰው ለሕዝብ በረከት እንዳይሆኑ መንገዳቸው ላይ እየቆምን ተንኮል የምንሰራ ሰዎች ፣ የቱንም ያህል ተንኮል ብንሰራና ክፋትን ብንሸርብ ልናቆማቸው አንችልምና ፣ ሥራ ለሠሪው እሾክ ላጣሪው እንዲሉ ስለ ክፉ ሥራችን እግዚአብሔር ይቅር እንዲለን ንስሐ እየገባን ፣ የእግዚአብሔርንም ምሕረት እየጠየቅን ለቀጣዩ ጉዞ ቅኖችና መልካም ሰዎች ሆነን ብንችል የመልካም ሥራ ሁሉ ተባባሪዎች እንሁን :: አለበለዚያ ግን በዚሁ በክፋታችን ከቀጠልን ፣ ጊዜ ይቆያል እንጂ በሐማ ላይ የመጣች የእግዚአብሔር ፍርድ በእኛም ላይ ትሆናለች በማለት መልዕክቴን እጠቀልላለሁ :: እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን :: ግልባጭ ለአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ አገልግሎት