Friday 30 March 2018

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ (...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 4 ) ክፍል አራት የዛሬው ትምህርታችን ማርያም መካከለኛ የሆነችበትን የኦርቶዶክስ አስተምህሮን የምናይበት ጊዜ ነው ማርያም መካከለኛ ናት የተባለችባቸውን ወደ ሦስት የሚደርሱ ነጥቦችን እንመለከታለን 1ኛ ) የክብርዋም ገናናነት በማለት ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ብለዋታል 2ኛ ) ከረግረግ መሸጋገርያ የጽድቅ መሰላል የሆንሽ ማርያም ሆይ ለምኚልን ብለዋታል 3ኛ ) እንደገናም ለማርያም መካከለኛነትንና አስታራቂነትን ሊስጡም ፈልገው ማርያም አርጋለች ስለዚህ እንደ ልጅዋ ትንሣኤ አድርጋችሁ አክብርዋት ሲሉ ይገልጻሉ መጽሐፍቅዱሳችን ግን እውነተኛውና ትክክለኛው መካከለኛ ኢየሱስ ለመሆኑ መጽሐፍቅዱሳዊ አስረጂ በመስጠት ያብራራል ጥቅሶቹንም እነሆ ብለናል 1ኛ ጢሞቴዎስ 2 : 5 / ዘፍጥረት 28 : 12 / ዮሐንስ ወንጌል 1 : 52 ውድ ወገኖቼ ትምህርቱን በእንዲህ መልኩ በአክብሮት ላብራራላች ወድጃለሁ ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39 Primary: yonasasfaw8@gmail.com yonasgetaneh@ymail.com

No comments:

Post a Comment