Sunday 18 March 2018

D.r Zebene Lemma Debate with Loser Pastor ክፍል 1--አቤት ዉሸት ምነዉ ፓስተር? ደግሞ ኦ...በፓስተር ዶክተር ቶሎሳ ጉዲናና በዶክተር ቀሲስ ዘበነ ለማ የነበረውን ውይይት መሠረት በማድረግ የተዘጋጀ መጽሐፍቅዱሳዊ መልስ በዚህ ጉዳይ ከዚህ በፊት መልስ መስጠቴን አስታውሳለሁ ይሁን እንጂ አሁንም ይህንን መልስ ያዘጋጀሁት የውይይቱ ሃሳብ በፌስቡክ ፔጄ ላይ እኔና ትምህርቴን ለመቃወም ሲባል ተጽፎና ተለጥፎ ስላገኘሁት ፣ ላልፈውም ስላልፈለኩ ነው ተቃውሞውም እንዲህ የሚል ነው ሳራ የድንግል ማርያም ልጅ · Friends with N Lov Man and 3 others ህምምምምም በትክክል የመጽሃፍ ቅዱስ ቁጥርና ምእራፍ ሳታቁ ነው እንዴ የስነ መለኮት ምሩቅ ኣናት ላይ ፊጥ ምትሉት ለማንኛውም መብታችሁ ነው መለፍለፍ ማን ይከለክላችኋል ብትጮሁ ብታብዱ ። ሳራ የድንግል ማርያም ልጅ · 4 mutual friends https://youtu.be/uW1kSwfVB5g ለቢንያም እና ለኣቶ ዮናስ ይህ you tube ተመልከቱት ፡እንኳን እናንተን ከኛ የተሻለ እውቀት የሌላችሁ ዋናው የፕሮቴስታንት ምሁር ፕሮፊሰር ቶሎሳ እንዴት በመጽሃፍ ቅዱስ ዙርያ ስያጨናንቃቸው ማየት ትችላላቹ ወገኖች የጌታ ሰላም ይብዛላችሁ በማለት ሰላምታዬን እያስቀደምኩ አሁን በቀጥታ ወዳዘጋጀሁት መልስ እገባለሁ ቤተመቅደስ በሐዲስኪዳን አንድና በኢየሩሳሌም ብቻ ያለ ስለሆነ እንኩዋን አይደለም በሐዲስኪዳን በብሉይ ኪዳን እንኳ ከኢየሩሳሌም ውጪ ቤተመቅደስ እንዲሠራ የተነገረ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ የለም ከዚህ የተነሳ በሐዲስ ኪዳን ቤተመቅደስ ስንል የገነባነውና ወደፊትም የምንገነባው ጣራና ጉልላት ያለው ሕንጻ የለንም ወደፊትም አይኖረንም ሊኖረንም አይገባም ለምን? ስንል መጽሐፍቅዱሳችን እንደነገረን የዛሬዎቹ የሐዲስኪዳን ቤተመቅደሶች በክርስቶስ ኢየሱስ ደም ታጥበን የዳንን የጌታ አማኞች ነን 1ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 9 _ 11 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 3 ፥ 9 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 19 እና 20 ታድያ ዛሬ በሐዲስኪዳን ድንጋይ ኮልኩለን ፣ ሲሚንቶን በውሃ ለውሰንና አቡክተን የምንሰራው መቅደስ ከሌለን ደግሞ በቤተመቅደስ ውስጥ ልንቀድስበት የምናኖረው ታቦት የለንም ፣ ታቦት ከሌለን ደግሞ በመቅደስ ውስጥ ገብቶ የሚቀድስልን ክህነቱም ለእርሱ ብቻ የሆነ እኛም አስቀዳሽ ተብለንና ተሰይመን እርሱ ቀዳሽ እኛ አስቀዳሽ ልንሆንለት የተዘጋጀልን ካህን የለንም ደግሞም እንዲህ ያለ ካህን ልንሾምም ሆነ ልናዘጋጅ አይገባም ከዚህም ሌላ መጽሐፍቅዱሳችን የነገረን ቀዳሽነት ለካህን አስቀዳሽነት ደግሞ ለምዕመን ብሎ ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ እስከወጣን ድረስ እኛ ሁላችን የንጉሱ ቀዳሾችና አስቀዳሾች መሆናችንን ነው የነገረን 1ኛ ጴጥሮስ 2 ፥ 9 እና 10 ፤ ራዕይ 1 ፥ 6 ፤ ራዕይ 5 ፥ 9 _ 14 ዘበነ ግን ይህ ዓይነቱ የመጽሐፍቅዱስ እውነት ስላልተገለጠለትና ወደዚህም ዓይነት መጽሐፍቅዱሳዊ መረዳት ስላልመጣ እንዲሁ ያለ እውነተኛ ማስረጃ አካኪ ዘራፍ ብሎና ከሜዳ ተነስቶ ለፈለፈ 1ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 20 እና 21 ወንጌልን በመስበክ የክርስቶስ የመከራው ተካፋይ የሆኑትን ሐዋርያትና የብሉይ ኪዳን ነቢያትንም በዚሁ በወንጌሉ ምክንያት የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው በዋሻ በምድር ጉድጓድ እንደተቅበዘበዙ መጽሐፉ ስለሚናገር የገዳም ሕይወት ነው የኖሩት ሲል ባልተጻፈበት መንገድ ተርጉሞ ሰዎች ወደ ገዳም ገብተውና በዋሻ ተደብቀው በጸለዩት ጸሎት ነው የሚድኑት በማለት የኢየሱስን ብቸኛ አዳኝነትና በክርስቶስ ሥራ ብቻም የተገኘውን ደኅንነት ሊያስተባብል ሞከረ ነገር ግን አሁንም መዳን በኢየሱስ ብቻ ስለሆነ ኢየሱስ ብቻውን ያድናል የሐዋርያት ሥራ 4 ፥ 12 የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው በዋሻና በምድር ጉድጓድ ተቅበዘበዙ የምትለዋን ቃል ደግሞ ነጥሎ በማውጣትና ለገዳማዊ ሕይወትም ሆነ አመሠራረት በመስጠት ወንጌልን በዓለም ዞረው የመሠከሩትን አባቶች ሳይቀር እንደ ገዳም መነኩሴና ባሕታዊ ለጽድቅ ሲሉ በዋሻ ውስጥ የተቀረቀሩና የሞቱ እንደሆኑ አድርጎ በመቁጠር የምንኩስናንና የብሕትውናን አስፈላጊነት በጽኑ ሊያስረዳን ፈለገ ነገር ግን አሁንም ዘበነን አንድ እውነት ልነግረው የምፈልገው ኢየሱስ ስለ ኃጢአታችን ከሞተና እኛን ስለ ማጽደቅ ከተነሣ ሮሜ 4 ፥ 23 _ 25 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 15 ፥ 3 እና 4 ይሄ እውነት የበራላቸው ነቢያቱም ሆነ ሐዋርያቱ የኢየሱስን ብቸኛ አዳኝነቱን አጽዳቂነቱንም ጭምር በትክክል ሰብከው ከመከራው ጽናት የተነሣ በዋሻና በምድር ጒድጓድ ከተቅበዘበዙ አዳኙና አጽዳቂው የኃጢአትንም ሥርየት የሚሰጠው ኢየሱስ እያለ ለምን ይሆን ዛሬ ድረስ ሰዎች ገዳም ገብተው ሰንሰለት ታጥቀውና ዳዋ ለብሰው ከሰውም ተለይተው እንዲህ ሲሰቃዩ የሚኖሩት ? ኢየሱስ ለመዳኛቸውም ሆነ ለኃጢአታቸው ሥርየት በቂ ሳይሆን ቀርቶ ? ወይስ የእኛ ኢየሱስን አለመስበክ ? ቀሲስ ዘበነ ለእነዚህ መጠይቆች የሰጠኸው ወደፊትም ቢሆን የምትሠጠው መልስ የለህምና ትምህርትህን እንደ እግዚአብሔር ቃል ብታስተካክል የሚል ምክር አለኝ አስተካክለህና ከዚህ ስሕተትህም ፈጥነህ ተመልሰህ ባይህ ለብዙዎች በረከት እንደምትሆን አምናለሁ ጌታ ይርዳህ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39
 Primary: yonasasfaw8@gmail.com yonasgetaneh@ymail.com


No comments:

Post a Comment