Tuesday 27 February 2018

ለሰዎች ዕድል መስጠት ( ትንቢተ ኢሳይያስ 40 ፥ 11 ፣ ዘፍጥረት 33 ፥ 13 _ 14 ) ክፍል አንድለሰዎች ዕድል መስጠት ( ትንቢተ ኢሳይያስ 40 ፥ 11 ፣ ዘፍጥረት 33 ፥ 13 _ 14 ) ክፍል አንድ በዚህ ትምህርት ውስጥ በመጀመርያ ለሕይወታችን መዳን ቅድሚያውን ሰጥቶ ለሁላችንም ዕድል የሰጠንን እግዚአብሔርን የምናይበት ነው በመሆኑም ከዚህ እውነት ተነስተን ደግሞ እኛም ለሌሎች እንዲሁ እድል መስጠት አለብን ይሁን እንጂ ለሰዎች ዕድል ሰጠን ማለት ግን ከእውነት አፈገፈግን ወይንም በእውነት ላይ ዋሸን ማለት አይደለም በማለት በጊዜው የሆነውን እውነት ለማሳየት የቪዲዮ ማስረጃዎችን ማቅረቤ ይታወሳል በዚህ ውስጥ ግን ሊቀጠበብት ዶክተር ዘሪሁን ሙላቱ የትምህርቴ መነሻና ዋነኛ ሃሳቤ ናቸው ለምን ብትሉኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ መምህርና ሊቀ ጠበብት የሆኑት ዶክተር ዘሪሁን ሙላቱ አውቀውት ይሁን ሳያውቁ ብቻ ልክ እንደ እኛ በሰማይ ቅዱሳን የማማለድ ስራ አይሰሩም ብለው እርፍ ያሉበትን የቃላት መልልስና ንግግር አቅርቤ ነበርና አሁን ምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ለማወቅ ፈልጌ ነው እንደኛ ተሃድሶ ተብለው ተባረዋል ? ወይንስ አይ እኔ ተሃድሶ አይደለሁም ተሳስቼ ነው ይህንን ያልኩት ሲሉ ቤተክህነትን ይቅርታ ጠይቀው ተመልሰዋል የሚለው የእኔም ጥያቄ ስለነበረ ነው እነ መሪጌታ ሙሴና መሪጌታ ጽጌ በጊዜው በነበረው ውይይት ላይ ሊቀጠበብቱ የመጽሐፍቅዱሱን እውነት ፍርጥ አድርጎ በመናገር በሰማይ ያሉ ቅዱሳን ፍርድ ከተሰጠ በኋላ አንዳቸው ለአንዳቸው ተነጋግረው ያስታርቃሉ ወይንም ያማልዳሉ የሚል የቤተክርስቲያን ትምህርት የለም በማለታቸው ምክንያት ሊቀጠበብቱ ተሃድሶ ስለሆኑና እኛንም ስለመሰሉ ጌታን ሳናቋርጥ እናመሰግናለን ሲሉ ተደምጠዋል ስለዚህ እኔም የኚህን የሊቀጠበብቱን የመጨረሻ ሁኔታ ለመስማትም ሆነ ለማወቅ ስለጓጓሁ ይህንን ጽኑ የሆነውን ምስክርነታቸውን ሰምቼ በብዙ ሃሴት በማድረግ እስካሁን ድረስ እየጸለይኩላቸው እገኛለሁ ስለዚህ ይህንን ሁኔታም የምታውቁ ሰዎች ሊቀ ጠበብቱን አፈላልጋችሁ በመጠየቅ የነገሩን መጨረሻ ብታውቁና ብታሳውቁን ፣ እንደገናም እኚሁኑ ሊቀጠበብት ዶክተር ዘሪሁን ሙላቱን በዚሁ በመሠከሩት የእግዚአብሔር ቃል እውነት እንዲጸኑና እስከመጨረሻው እንዲሄዱ እንዳያፈገፍጉም ጠጋ ብላችሁ ብታበረታቷቸው ብትጸልዩላቸው እና የሚሆነውን ነገር ሁሉ ብታደርጉ በጣም ደስ ይለኛል ጌታ እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39 Primary: yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment