Friday 23 February 2018

ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን ተገቢውን የእግዚአብሔር እውነት እንዲያገኙ ለመምህር ልዑለቃል የተሰጠ ምላሽና የማስገንዘብ...ራሳችሁን ሁኑ እንጂ አታፈግፍጉ ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም ወደ ዕብራውያን ሰዎች የተላከ ምዕራፍ 10 : 32 - 39 ይመልከቱ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን ተባረኩ እስካሁን ድረስ በተለቀቁት ቪዲዮዎች በብዙ እንደተባረካችሁ አምናለሁ ተስፋም አደርጋለሁ መጽሐፍቅዱሳችን በግልጽ እንደሚነግረን ወንጌልን በተመቻቹ መድረኮችና በተዋቡ ፑልፒቶች ዙርያ ብቻ የምንሰብከው ሳይሆን በእስር ቤትና በፈተና በማስጠንቀቅያና በዛቻ ውስጥም ሆነን የምንሰብከው እውነት ነው ይሁን እንጂ በዚህ ውስጥም እንኳ ሆነን ጌታ በሰጠን የተስፋ ቃሉ መሠረት ስንጸልይ በራሱ በመንፈስቅዱስ አማካኝነት ቃሉን በግልጥነት ወደምንናገርበት አደባባይ እንሸጋገራለን የሚወስደን መንፈስም በላያችን ላይ ይመጣል እንጂ ወደ ኋላችን ልናፈገፍግ ምክንያት የሚሆኑንን ሃይማኖታዊ ቃላቶችን እየተጠቀምን መንሸራተትና ከእውነት ወንጌል የምናፈገፍግ አንሆንም የሚያፈገፍጉ ሰዎች ማምለጫ የሚሆናቸውን የትኛውንም ዓይነት መንፈሳዊ ቃላቶችን ቢጠቀሙም እግዚአብሔር ግን የሚያውቃቸው በመንሸራተታቸው እና በማፈግፈጋቸው ስለሆነ የሚሰጣቸው መልስ ይህንን የሚመስል ነው ነገር ግን ግማሽ በነቀፋና በጭንቅ እንደ መጫወቻ ስለ ሆናችሁ ግማሽም እንዲህ ካሉት ጋር ስለ ተካፈላችሁ፥ ብርሃን ከበራላችሁ በኋላ መከራ በሆነበት በትልቅ ተጋድሎ የጸናችሁበትን የቀደመውን ዘመን አስቡ የሚበልጥና ለዘወትር የሚኖር ገንዘብ በሰማይ ራሳችሁ እንዳላችሁ አውቃችሁ፥ በእስራቴ ራራችሁልኝ የገንዘባችሁንም ንጥቂያ በደስታ ተቀበላችሁ እንግዲህ ታላቅ ብድራት ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉ የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርጋችሁ የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋልና ገና በጣም ጥቂት ጊዜ ነው፥ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም ወደ ዕብራውያን ሰዎች የተላከ ምዕራፍ 10 : 32 - 39 ይመልከቱ የሚያፈገፍጉ ሰዎች እንዳልኳችሁ የትኛውንም ዓይነት ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ቃላቶችን ቢጠቀሙ ጌታ እግዚአብሔር አፈግፋጊዎች እንጂ በሳሎች አይላቸውም እንደገናም ከአዋቂዎችና ከአስተዋዮች ጎራም አይመድባቸውም ታድያ እንዲህ ዓይነት ሰዎችን ሐዋርያው የሕይወታቸውን ዓይነት እንድናውቅ ግልጽ አድርጎ ነግሮናል በገላትያ 6 ፥ 11 _ 16 መሠረት በሥጋ መልካም ሆነው ሊታዩ የሚወዱ ሁሉ እንድትገረዙ ግድ አሉአችሁ፥ ነገር ግን ስለ ክርስቶስ መስቀል እንዳይሰደዱ ብቻ ነው በሥጋችሁ እንዲመኩ ልትገረዙ ይወዳሉ እንጂ የተገረዙቱ ራሳቸው እንኳ ሕግን አይጠብቁም ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና አለን ስለዚህ ከዚህ የተነሳ ለሚያፈገፍጉ ሰዎች ቦታ የለንም ለወደፊቱም አይኖረንም ነገር ግን የሚያፈገፍግ ሰው ጥሩ የሆነ የእግዚአብሔር ቃል ምክር የሚያስፈልገው ነውና ከማፈግፈጉ ተመልሶ በትክክለኛ ቦታው እንዲሆን የሚያስችል በቂ የሆነ ምክር ልንሰጠው ዝግጁዎች ነን ስለዚህ ከእነዚህ ሃሳቦች በመነሳት ይህንን ቪዲዮ ለምትከታተሉ ወገኖቼና አድማጮቼ በሙሉ የምናገረው አንድና አንድ እውነት የሚያፈገፍግ ሰው በብዙ ሰዎች ልብ ውስጥ የሚታሰበው አዲስ ወደ ጌታ የመጣና የጌታ አማኝ የሆነ ሰው ነው ተብሎ ነውና አስተያየቱም ሆነ ምክሩ ፣ ጸሎቱ ፣ የፕሮግራም ግብዣውና ማንኛውም መንፈሳዊ የተባለ ነገር ሁሉ የሚዥጐደጐደው እንዲህ ላለ ሰው ነው ይሁን እንጂ ይህን ሁኔታ በትክክለኛው በእግዚአብሔር ቃል መነጽር ከተመለከትነው የሚያፈገፍጉ በአብዛኛው ለክርስትናው አዲስ የሆኑ ብቻ ሳይሆኑ በተለይም ዛሬ ላይ በእኛ ዘመን በጌታ ቆየሁ ፣ ስም ያለኝ አገልጋይ ነኝና ወዘተርፈ የሚለው ሰው ሁሉ ዓይን ያወጣ ማፈግፈግና መንሸራተት እጥፍም ብሎ መሄድና አላዋጣ ሲል ደግሞ ላሽ ማለትን የሚያሳይበት ጊዜ ላይ ደርሰናል አንዳንዱ ደግሞ ማፈግፈጉ ለራሱ እንኳ እስከማይታወቀው ጊዜ ድረስ ከሌላው ጋር በግብዝነት አብሮና ተተያይዞ ሲያፈገፍግ ይታያል ይህንን ማፈግፈግ ታድያ ባሳለፍኩት የክርስትና ጒዞና የአገልግሎት ቆይታ በብዙ አገልጋዮች ሕይወት ውስጥ አይቼዋቻለሁ በመሆኑም መልዕክቴን ስጠቀልል አሁን ላይ ያላችሁ ማናችሁም የፕሮቴስታንት አገልጋዮች ፓስተሮች ልትሆኑ ትችላላችሁ እንደገናም ከኦርቶዶክስ የወጣችሁ ተሃድሶዎችና ሌሎችም እራሳችሁን ሁኑ ፣ አታፈግፍጉ ፣ አታፈግፍጉ ፣ አታፈግፍጉ ስል ደግሜ ደጋግሜ በመናገር ጽኑ የሆነውን ወንድማዊ ምክሬን ለእናንተ ለወገኖቼ ማስተላለፍ እወዳለሁ ተባረኩልኝ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

No comments:

Post a Comment