Saturday 17 February 2018

.... ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ክፍል አራት ( ቊጥር 2 )የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ክፍል አራት ( ቊጥር 2 ) ክፍል አራት የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች እንዴት ናችሁ ተባረኩ ከኢየሱስ ጋር የተፋታችዋ ቤተክርስቲያን ቊልቊለት የሄደችበትን የቊጥር ሁለት ትምህርት አሁን አቀርባለሁ የሉቃስ ወንጌል 21 ፥ 28 ላይ ይህም ሊሆን ሲጀምር ቤዛችሁ ቀርቧልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሱ ይለናል በመሆኑም ዛሬ ቤዛዋን ያወቀች ቤተክርስቲያን ልትሆን የሚገባት እንዲህ ነው ቤዛዋ ማለትም ለበደልዋ ሥርየት ሊሰጣት ምትክ ሆኖ የሞተላት ኢየሱስ እርስዋን ስለማጽደቅ በመነሣት የተቤዣት ፣ የታደጋትና ያዳናት በመሆኑ አድራሻዋን በሰማይ ያደረገች ናት ቤዛዋ የሆነውን ዳግመኛም መጥቶ የሚወስዳትን ጌታ ከመጠበቅ ታክታና ምስጢሩም አልገባ ብሏት ምድር ምድር የምታይና የምትመለከት ልትሆን ግን አይገባትም ለሁልጊዜም አሻቅባና ራስዋን በተስፋ ቃል አንስታ ተመልሶ ሊመጣ ሊወስዳትም ያለውን ኢየሱስን በመጠበቅ ወደ ሰማይ የምታይ መሆን አለባት ይህንን የሚያደርጉ ደግሞ የቤዛነት ምስጢር የገባቸውና በኢየሱስ የዳኑ ፣ የጸደቁ ሰዎች ሁሉ ናቸው ከኢየሱስ የተፋታችውና የቊልቊለቱን መንገድ የተያያዘችዋ ቤተክርስቲያናችን ግን ቤዛዋ ኢየሱስ ብቻ ባለመሆኑ ለዚህ እውነት አልታደለችም ከኢየሱስም ይልቅ አፍዋን ሞልታ ቅድስት ማርያም ቤዛዊተ ኩሉ ዓለም ወደ አማርኛው ሲተረጎም የዓለም ሁሉ ቤዛ ቅድስት ማርያም ሆይ የሚለውን ትርጉም የሚሰጠን ነውና ይህንን ስለምትል ይህ ብቻ አይደለም መስቀል ቤዛዬ የነፍሴም መድኃኒት ነው ፣ ከዚህም ሌላ ኃይሌና ከጠላቴ ከሰይጣንም ነጻ አውጪዬ ነው በማለት ቤዛዋ የሆናትንና ሊሆናትም ያለውን ኢየሱስን ለመጠበቅ ዝግጁ ወይም የተዘጋጀች አይደለችም ከሁሉ በላይ በጣም የገረመኝ ደግሞ ክርስትናን በመቀበልና በትምህርተ ወንጌል ቀዳሚ ሆና ሳለ እርስዋ ግን የኋሊት ተጐትታና የወረደ ነገር ውስጥ ገብታ የቃዡ ፣ የዞረባቸውም ባሕታውያን በየገደሉ ውስጥ የጻፉትን ገድላትና ድርሳናትን የእምነት መመርያዋ አድርጋ በመውሰድ ማርያምና መስቀሉ ቤዛዬ ናቸው ማለትዋ ሳያንሳት ይባስ ብላ የኃጢአታችንን ቤዛ መቃብሩን የሰጠን ተክለኃይማኖት እያለች የተክለኃይማኖትን መቃብር ቤዛዬ ነው ማለቷ ፣ ይህ ብቻ አይደለም እዳሪው ማለትም ተቅማጡን እንኩዋ ሳይቀር እንደ ስቅለቴ ደም እቆጥርልሃለሁ የሚል ቃልኪዳን ጌታ ሰጥቶታልና በማለት ተቅማጥን ከክርስቶስ ደም ጋር አንድ አድርጋ ቆጥራ ለኃጢአቷ ሥርየት እንዲሆን መቀበልዋ ጉድ ከጉድም ጉድ የሚያስብላት ሆኗል ይህንን ጉድ ነው እንግዲህ እኔም ግራ ቢገባኝ ከኢየሱስ ጋር የመፋታትና የቊልቊለቱ መንገድ ያልኩት መቼም ተቅማጥና እዳሪ እንደ ክርስቶስ የስቅለቱ ደም ተቆጥሮ የኃጢአት ይቅርታን ያሰጣል እየተባለ እንደገናም የተክለሐይማኖት መቃብር ቤዛዬ ነውና የመሣሠሉትን ሲባል ተደማምሮ እየተነገረ ይህቺን ቤተክርስቲያን ከኢየሱስ ጋር ነች ከኢየሱስም አልተለያየችም ወይም አልተፋታችም ማለቱ የእናንተን አላውቅም እንጂ ለእኔ ከሆነ ግን ፍጹም ውሸትና ከውሸትም በላይ የሆነ የዲያብሎስ እንዲሁም የጥልቁ ውሸት ነው ብዬ ነው የማምነው ስለዚህ መፋታት ብቻ ሳይሆን ከመፋታትም አልፋ ገልሙታና ወድቃ ተገኝታለች የተወደዳችሁ ወገኖች ይህቺ ቤተክርስቲያን አሁንም ስሕተትዋ እየበዛ መጥቶ በእርሱ በኩል በመስቀሉ ደም ሰላምን አድርጎ በምድር ወይም በሰማይ ያሉትን ለራሱ እንዲያስታርቅ የፈቀደበትን እውነትና ኢየሱስም ይህንን እውነት ለመፈጸም ከሞት በኋላ በመንፈስ ሕያው ሆኖ ሄዶም በወህኒ ለነበሩት ነፍሳት የሰበከበትን ፣ ነጻ ያወጣበትንም እውነት ወደ ጎን በማድረግ ( ቆላስያስ 1 ፥ 19 እና 20 ፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 18 _ 2 )በተክለ ሐይማኖትም ይሁን በክርስቶስ ሰምራ እንዲሁም በድርሳነ ሚካኤል በተጻፉልን የገድላትና የድርሳናት ሃሳብ መሠረት ሊቆጠሩ የሚያቅቱ ነፍሳት ተመርተው ከሲኦል መውጣታቸውን ጽሑፎቹ ይተርኩልናል ስለዚህ ከዚህ የተነሳ ክርስቶስ በምድርም ይሁን በሰማይ ያሉትን ለራሱ እንዲያስታርቅ መፍቀዱ እንደገናም ይሄው ክርስቶስ በመንፈስ ሕያው ሆኖና ሄዶ በወህኒ ለነበሩት ነፍሳት መስበኩ ከእነዚህ ከተጻፉት ገድላትና ድርሳናት አንጻር ተረት ተረትና ቀልድም ነው እያለችን ነው የአሁንዋ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን በዚያው መጠን ደግሞ የኦርቶዶክስ ገድላትና ድርሳናት መጻሕፍቱም ትክክለኞቹና ነፍሳትንም ነጻ አውጪዎቹ እኛ ነን እያሉን ይገኛሉ ምን እነርሱ ብቻ የዚሁ የገድላቱና የድርሳናቱ ዋነኛ ሰባኪዎቹም የሚሉን ይህንኑ ነው ነገር ግን አለቃ መሠረት ስብሐት ለአብ በስምዓ ጽድቅ ብሔራዊ መጽሐፋቸው በገጽ 48 አሁን ላይ መጽሐፍቅዱስዋን ጥላ የገድልና የድርሳናት ተከታይ ለሆንችው ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንም ሆነ ለዘመኑ የገድላትና የድርሳናት ሰባኪዎች እንዲህ ሲሉ ሙሉ መልስ ሰጡ መልሱም ከዚህ የሚከተለው ነው ይደልወነ ናጽምዕ ቃላተ መለኮት ከመ ኢይባዕ ውስተ አልባቢነ ቃል ነኪር ትርጉም ባዕድ ቃል ወደ ልባችን እንዳይገባ ቃላተ መለኮትን ማድመጥ ይገባናል አሉ ይህ ቃላተ መለኮት የተባለው ደግሞ አሸናፊው የእግዚአብሔር ቃል ነው የሐዋርያት ሥራ 19 ፥ 19 እኚህ አባት ታድያ ዛሬ በሞት የተለዩን ሆነው በመካከላችን ባይኖሩም ትተውልን የሄዱት መጽሐፍና አባታዊ ምክራቸው ግን ለዘላለም ከእኛ ጋር የሚኖር ነው ስለዚህ ከዚህ በኋላ ባለ ዘመናችን እኛም ጠቃሚ በሆነው መጽሐፍቅዱሳዊ ምክራቸው ተጠቃሚዎች ሆነን ወደ ተጻፈልን የመጽሐፍቅዱስ እውነት በመመለስ በመጽሐፍቅዱሱ ቃል ብቻ እንድናምን እግዚአብሔር ይርዳን አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment