Friday 2 February 2018

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አመሠራረት ( ክፍል አንድ ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አመሠራረት ( ክፍል አንድ ) የተወደዳችሁ ወገኖቻችን እንዴት ናችሁ ተባረኩ ይህንን ትምህርት ዛሬ ለእናንተ አንድ ብለን ጀምረነዋል የምንወዳት አንጋፋዋ ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያናችን በ325 ዓመተ ምሕረት የመጀመርያው ሐዋርያችን በሆነው ፍሬምናጦስ ተብሎ በቀዳሚነት በተጠራውና አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በተባለው ሰው ነው የተቋቋመችው ይህ ሰው ክርስትናን ከእስክንድርያ ይዞልን ሲመጣ የእግዚአብሔርን ቃል መሠረት ያደረገ ክርስትናና የእምነት መግለጫንም ጭምር ይዞልን የመጣና በዚሁ መሠረትም ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት የምትለዋን ማኅበር ወይንም ቤተክርስቲያን ያቋቋመ ነው ታድያ ቤተክርስቲያንም ሆነ የቤተክርስቲያንን የእምነት አቋም የሚገልጸው የእምነት መግለጫ መሠረቱ የእግዚአብሔር ቃል ሲሆን ቤተክርስቲያን የገሃነም ደጆች የማይችሏት ጠንካራ ትሖናለችና ሥራው ለእግዚአብሔርም ሆነ ለሰው በጣም አስደሳች ነው የሚሆነው የኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የእምነት ሐዋርያችን አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ያደረገው እንግዲህ ይህንን ነው እንደ ዛሬው ዘመን አገልጋዮች ደርሶ ቤተክርስቲያንን የተከለና ስምም ያወጣ አይደለም ቅድሚያውን ይዞ ከዓለም አቀፍዋ ቤተክርስቲያን መሪ ከ20ኛው ፓትርያርክ ከሐዋርያው አትናቴዎስ የኤጲስቆጶስነትንና የሐዋርያነትን ሥልጣን ብቻ ሳይሆን ይኸው አትናቴዎስ 27 የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሲል በቃለ ቡራኬ የደነገገበትን ውሳኔ በመቀበል 27 ቱን የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትና 39ኙን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በአንድ ላይ አስተባብሮ ይዞ በመምጣት በዚህ በእግዚአብሔር መንፈስ በተጻፉ 66 ቱ ቅዱሳት መጻሕፍት አማካኝነት ወንጌልን ነገሥታት ጓዳ ድረስ በመግባትና በመስበክ ማኅበሩን ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት በማለት የመሠረተ ብቻ ሳይሆን እምነቱንም በመንግሥት ደረጃ ሳይቀር ታውጆና ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ በመንግሥት ሰነድም ጸድቆ የደርግ መንግሥት እስከ ተሻረበት ዘመን ድረስ ምድሪቱ የክርስቶስ እንድትሆን ያደረገ ታላቅ የቤተክርስቲያን ባለ ውለታና ለእኛም ምሳሌ የሆነን የእምነት ሐዋርያ ነው ይህ ሰው ሰው ይህንን ሁሉ ወደ ማድረግ የመጣው ትክክለኛውን 66 ቱን ቅዱስ መጽሐፍ ማለት መጽሐፍቅዱስን አምኖና ተቀብሎ የአገልግሎቱም መሠረት አድርጎ ስለተነሳ ነው ለዚህም ነው በዚህ በተሃድሶ አገልግሎት ከ50 ዓመት በላይ በአገልግሎት የገፉና ዛሬ በመካከላችን በሕይወት የሌሉ መጻሕፍቶቻቸውና ሥራዎቻቸው ግን ዛሬም ድረስ ሕያው ሆኖ ማንነታቸውን እየገለጸ ያለ ታላቁ ሊቅ አለቃ መሠረት ስብሐት ለአብ በስምዓ ጽድቅ ብሔራዊ መጽሐፋቸው ላይ ከዓለም አቀፋዊቷ ቤተክርስቲያን ሐዋርያና ከእስክንድርያው ፓትርያርክ አትናቴዎስ በሐዋርያችን አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አማካኝነት ሲያያዝ መጥቶ እኛ ጋር የደረሰው ይሄ እምነት መሠረቱ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ጠንቅቀው ያወቁና የተረዱ በመሆናቸው እንደገናም ቤተክርስቲያኒቱን ዛሬም ላይ ቢሆን ወደ መሠረቷ ሊመልሳት የሚችለው ይኸው የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ስለተገነዘቡ ፦ በሃይማኖተ አበው ያለ የዮሐንስ አፈወርቅን ሃሳብ በማንሳት ይደልወነ ናጽምዕ ቃላተ መለኮት ከመ ኢይባዕ ውስተ አልባቢነ ቃል ነኪር አሉን ትርጉም ባዕድ ቃል ወደ ልባችን እንዳይገባ ቃላተ መለኮትን ማድመጥ ይገባናል ሲሉ ሃይማኖተ አበው ላይ በሠፈረው የአባቶች መጽሐፍ ከመከሩን በኋላ ባዕድ ቃል ያሉበትን ሃሳብ ሊያብራሩልን ስለፈለጉ ደግሞ እንዲህ አሉን ያለንን በመገንዘብ በእግዚአብሔር ቃል ብቻ ተወስነን ከቊርዓንና እነርሱንም ከሚመሳስሉ ልዩ ልዩ የልብ ወለድ መጻሕፍት እምነት እንርቃለን በማለት ተናገሩ ( ምንጭ ስምዓ ጽድቅ ብሔራዊ ገጽ 48 ) መልዕክቴን ስጠቀልለው በእምነታችን ተመሥርተንና ጸንተንና እስከ መጨረሻውም ኖረን በፊቱ ለመቆም አለቃ መሠረት በመጽሐፋቸው ላይ አሁን ድረስ እንደነገሩን ቃላተ መለኮትን በማድመጥ መኖር ይሁንልን ታቦቱም በቂርያትይዓሪም ከተቀመጠበት ቀን ጀምሮ ወራቱ ረዘመ፥ ሀያ ዓመትም ሆነ፤ የእስራኤልም ቤት ሁሉ አዝኖ እግዚአብሔርን ተከተለ መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 7 : 1 እግዚአብሔርም ሳሙኤልን አለው፦ በእነርሱ ላይ እንዳልነግሥ እኔን እንጂ አንተን አልናቁምና በሚሉህ ነገር ሁሉ የሕዝቡን ቃል ስማ …..ሳሙኤልም የእግዚአብሔርን ቃል ሁሉ ንጉሥን ለፈለጉ ሕዝብ ነገራቸው ( ሳሙኤል ቀዳማዊ 8 : 7 ,10 ) ሕዝቡ ግን የሳሙኤልን ነገር ይሰማ ዘንድ እንቢ አለ። እንዲህ አይሁን፥ ነገር ግን ንጉሥ ይሁንልን እኛም ደግሞ እንደ አሕዛብ ሁሉ እንሆናለን፤ ንጉሣችንም ይፈርድልናል፥ በፊታችንም ወጥቶ ስለ እኛ ይዋጋል አሉት ሳሙኤልም የሕዝቡን ቃል ሁሉ ሰማ፥ ለእግዚአብሔርም ተናገረ እግዚአብሔርም ሳሙኤልን፦ ቃላቸውን ስማ፥ ንጉሥም አንግሥላቸው አለው ( መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 8 : 10 , 19 - 22 ) ሕዝቡም ሁሉ ሳሙኤልን፦ ንጉሥ በመለመናችን በኃጢአታችን ሁሉ ላይ ይህን ክፋት ጨምረናልና እንዳንሞት ስለ ባሪያዎችህ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ አሉት ( መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 12 : 19 ) ሳሙኤልም ሕዝቡን አለ፦ አትፍሩ በእውነት ይህን ክፋት ሁሉ አደረጋችሁ፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችሁ አምልኩት እንጂ እግዚአብሔርን ከመከተል ፈቀቅ አትበሉ ምናምንቴ ነውና የማይረባንና የማያድን ከንቱን ነገር ለመከተል ፈቀቅ አትበሉ ( መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 12 : 23 ) ያንም ነቢይ የማትሰማው ነፍስ ሁሉ ከሕዝብ ተለይታ ትጠፋለች አለ ( የሐዋርያት ሥራ 3 : 23 ) ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

No comments:

Post a Comment