Monday 5 February 2018

በከሣቴ ብርሃን አባ ሰላማ የተቋቋመችው የመጀመርያዋ ኦርቶዶክሳዊት ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኅብረት ያለፈችባቸው መ...በከሣቴ ብርሃን አባ ሰላማ የተቋቋመችው የመጀመርያዋ ኦርቶዶክሳዊት ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኅብረት ያለፈችባቸው መንገዶች ክፍል ሁለት የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን ትምህርቱ በእግዚአብሔር ጸጋና እርዳታ በእናንተም በቅዱሳኑ ጸሎትና እገዛ ቀጥሎ ዛሬ የክፍል ሁለትን ትምህርት ይዤ ቀርቤያለሁ ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ በክርስቶስ ላይ የተመሠረተች በምትሆንበት ጊዜ ለሁል ጊዜም ትፈተናለች ይሁን እንጂ የተመሠረተችበት ዓለቱ ጽኑ ስለሆነ አትወድቅም እንደገናም የገሃነም ደጆች አይችሏትም በሰላማ ከሣቴ ብርሃንም ጊዜ የተመሠረተችው ቤተክርስቲያን በሐዋርያዊው አባ ሰላማ የተቋቋመች ቤተክርስቲያን ብትሆንም የተመሠረተችው በክርስቶስ ላይ እንጂ በሐዋርያዊው አባ ሰላማ ላይ ባለመሆኑ ባለፈችባቸው መንገዶች ሁሉ መሠረትዋ የሆነው ጌታ በሌላ አነጋገር በራሱ ላይ የመሠረታት ኢየሱስ ባለ ድል አድርጎአታል ( የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 15 _ 19 ) ትምህርቱን በሰፊው በተለቀቀው ቪድዮ በኩል ስለምትከታተሉት ታሪኩን መድገም አያስፈልገኝም ነገር ግን የታሪኩን ዳራና ጠቅለል ያለውን መልዕክት በአጭሩ ለማስታወስ ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ክርስቲያኖች በነበሩት ነገሥታት ብርታትና በሕዝብዋም ጠንካራ ከሆነው መጽሐፍቅዱሳዊ እውቀት የተነሣ ከቄሣር ቁንስጣ የተላከውን መልዕክት ያልተቀበለችና በፍሬምናጦስ አባ ሰላም ምትክ መንፈሳዊ መሪዋ ሊሆን ተልኮ የመጣውን አርዮሳዊ እና ሕንዳዊ ቴዎፍሎስን አሳፍራ የመለሰች ነበረች ይህንንም ያደረገችው ከቃሉ የመረዳት ጉልበት ጭምር ብቻ ሳይሆን ከሮማ ቄሣሮች ተጽዕኖ ሳይቀር ነጻ በሆነ ጥላ ሥር ስለነበረች ጭምር ነው ታድያ ይህንን የአርዮስ ትምህርት ተቀብላ ቢሆን ኖሮ እንደገና ዘመን መጥቶ በእስክንድርያው መሪ በቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት ፈጽሞ የተወገዘውን ኑፋቄ አርዮስን ከአዕምሮዋ አስወጥቶ በምትኩ ታድሶ የጸናውን የኒቅያን የእምነት መግለጫ ( ጸሎተ ሃይማኖትን ) ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት እንድትቀበል የማድረግ ዕድሉ የመነመነ በሆነ ነበር ስለዚህ በደገኛው ሐዋርያዋና መሪዋ ፍሬምናጦስ በተሰኘው አባ ሰላማ ብርታትና አርቆ አስተዋይነት ቀደም ብላ የኒቅያን የእምነት መግለጫ እንደ እግዚአብሔር ቃል በሆነ መረዳት ድቅቅ አድርጋ በመማርዋና በመገንዘብዋ በኋላ ላይ በለሰለሰ መንገድ በአታላይነት ሊገባ የሞከረውን አርዮሳዊ ኑፋቄና መልዕክተኛውን ቴዎፍሎስን በመጡበት አኳኋን መመለስ እንድትችል አድርጓታል ይህ ብቻ አይደለም ለወደፊቱም ትምህርተ መለኮትዋን በመልካም ጐዳና ለመምራት ያስቻላትን ዕድልና ጸጋ በቸርነቱ እንደሰጣት ያረጋግጥልናል እኔም ታድያ ከዚህ ትምህርት የተነሳ ሳላመሰግናቸው የማላልፋቸው አንድ እውነተኛ አባቴና መንፈሳዊ መሪዬ የነበሩ ስላሉ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሃብተ ማርያም ሊቀ ጵጵስናን ከተቀበሉ በኋላ ደግሞ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የተባሉትን አባት ሳላመሰግን አላልፍም እኚህ አባት እኔ በነበርኩበት ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የትምህርት ቤታችን ዲን ነበሩ በጣም ተራማጅና መጽሐፍቅዱሳዊ አስተሳሰብ የነበራቸው በመሆኑ ያደረጉብን ብዙ የብዙ ብዙ በጎ ተጽእኖዎች ነበሩ እያንዳንዱን አሁን ዘርዝሬ አልጨርሰውም ነገር ግን ዋናውና ትልቁ በጎ ተጽዕኖ የእምነት መግለጫችሁንና ማብራርያውን ከነ ጥሬ ንባቡ እንዲሁም የቃሉ ትርጉም ጋር በቃላችሁ አጥኑ ይሉን ነበር ፈተናውም የሚመጣው ከዚሁ የእምነት መግለጫ ነበረና ይህንን ፈተና ያላለፈ ከበድ ያለ እርምጃ ይወሰድበት ስለነበር እኛም ታድያ እርሳቸውንም ሆነ የሚወስዱብንን እርምጃ ስለምንፈራ አልጋችንን ለቀን የምንማርበት የክፍል ወለል ላይ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ቁጭ ብለን እናጠና ነበር በጊዜው የነበረው የአባታችን ጭካኔ ያማረረንና የክፍል ወለል ላይ ያሳደረን ቢሆንም አሁን አሁን ላይ ሳስበው ለአባታችን ዕድሜ ዘመን ይጨመርልዎ እርስዎ የሚያውቁት ምስጢር ስላለ ነው እንዲህ ጠንክረን የእምነት መግለጫችንን እንድናጠናና እንድናውቅ ያደረጉን በማለት ልባርካቸው ወደድኩ አባታችን ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ እውነተኛ አባታችንና የወንጌል መምህራችን ኖት ትላንት ለማጥናት በከፈልነው ዋጋ ብንከፋም ዛሬ ላይ ጠንክረው በወሰዱት እርምጃ ያስጠኑን የእምነት መግለጫ የትም ሳንሄድ በእምነታችን መሠረት ላይ እንድንተከልና ሌላውንም እንድንተክል ያስቻለን በመሆኑ ዕድሜና ዘመንን ይጨምርልዎ ብድራትዎትንም በላይ በሰማይ እግዚአብሔር ይክፈልዎት ተባረኩልኝ በማለት ላመሰግንዎት እወዳለሁ የተወደዳችሁ ወገኖች ለዚህ ነው እንግዲህ እንዴት እንደተቀበልክና እንደ ሰማህ አስብ ጠብቀውም ንስሐም ግባ በማለት በትምህርቴ ማጠቃለያ ላይ የገለጽኩት ( ራዕይ 3 ፥ 3 ) እንዴት እንደተቀበለና እንደ ሰማ ያወቀ ሰው የተቀበለውንም እንዴት እንደሚጠብቅ ያውቃልና በቀላሉ ለስሕተት ትምህርት የተጋለጠ አይሆንም ከዚህም ሌላ ለሚጠይቁት ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጀ ነው 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3 : 15 ታድያ ለዛሬዋም ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ያለኝ መልዕክት የተቀበለችውና እየተቀበለች ያለው መልዕክት ከማን መሆኑን እንድትረዳ እንዴት እንደተቀበለች ማወቅ ይኖርባታል የሚል ነው ጌታ ያልሰጣትን ይዛ ወይም ተቀብላ ከሆነ ደግሞ ብትጠለው ፈውሷ ይበዛል እንጂ አትጎዳም የሚል መልዕክት አስተላልፋለሁ ከዚህ በመለስ ደግሞ ቪዲዮውን ደግማችሁ ስሙት ትባረኩበታላችሁ ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

No comments:

Post a Comment