Tuesday 13 February 2018

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 1) ክፍል አራት የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዛሬው ትምህርት ደግሞ ትውልድ የተሰጠውን የእግዚአብሔር እውነት የሚፈልግበትና ጌታ በሰጠው እውነት ላይም እስከ መጨረሻው ቆሞ የሚታገልበት በመሆኑ ይህንንና እነዚህን በመሣሠሉ ትምህርቶች እየተጠቀመ ሊነቃ ሊመረምር በብዙ ሊረዳና ሊገነዘብ ይገባል እላለሁኝ በሐዋርያዊው ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተች የመጀመርያዋ ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ቤተክርስቲያን ያቋቋማት ሐዋርያው ሰላማ ከሞተ በኋላ ጥሩ ሁኔታ አላጋጠማትም ከእርሱ በኋላ የተነሱት ሰዎች ጤናማዋን የወንጌል ቤተክርስቲያን ማን ማንን ሊመራ ይችላል በሚል ፉክክር የማን ቤት ጠፍቶ የማን ይበጅ ቀረርቶ ሲሉ ተርተውና በተረታቸውም እርስ በእርሳቸው ሳይቀር ተደባድበው ባለመስማማት ከሣቴ ብርሃን ሰላማን የሾሙት ግብጻውያን ስለሆኑ ግብጻውያን ይምሩን ሲሉ ለግብጻውያን አሳልፈው ሰጧት ግብጻውያንም ለ1600 ዓመታት በጨለማና በባርነት ገዟት ታድያ ሰላማ የመሰረታት ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ቤተክርስቲያን ውድቀቷ የጀመረው ያኔ ነው በዚህም ውስጥ ዘመን መምጣቱ አይቀርምና ዘመን ስለመጣልኝ ነጻነቴን አውጄ ከዚህ ባርነት ወጣሁ ብትልም ነገር ግን አሁንም በዚሁ በባርነቱ ምክንያት ለዓመታት የጣለችውን ወንጌል እንደሚገባ ልታነሳው ያልቻለች በመሆንዋ ዘርዓ ያዕቆብ የተባለው ንጉሥ በ15 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ተነስቶ ይህቺን ያላገገመችና ከቁስልዋም ፈጽሞ ያልተፈወሰችን ቤተክርስቲያን ወደማትፈልገው አቅጣቻ በመምራት ይባስ ብሎ ከአዳኝዋ ከኢየሱስ ለይቶ አፋታት በጅማሬዋና በቅድምና ዘመንዋ በተቀበለችው ጌታ አማካኝነት ወደላይ መውጣት የሚገባትን ይህቺኑ ቤተክርስቲያንም ወደታች አውርዶ የቁልቁለቱን መንገድ እንድትመርጥና በዚያው መንገድ ላይ እየተንደረደረች እንድትወድቅ እንድትንከባለልም አደረጋት የተወደዳችሁ ወገኖች በቪዲዮ የተለቀቀው ትምህርት እንግዲህ ይህንኑ አስመልክቶ የተነገረ ነው በመሆኑም ትምህርቱ ታድያ ቤተክርስቲያንዋ በተመሠረተችበት በቅድምና ዘመንዋ ያመነችው መጽሐፍቅዱሳዊ እውነት ምን እንደሆነ የሚገልጽ ሲሆን ይሄ መጽሐፍቅዱሳዊው እውነት ደግሞ በመጽሐፍቅዱሱ ላይ ሠፍሮ ያለ እውነት ብቻ ሳይሆን ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን እስከ ዛሬ ድረስ በምትጠቀምባቸው የቅዳሴ ፣ የሰዓታት ፣ የዚቅ ፣ የድጓ እንዲሁም የሃይማኖተ አበው እና የመሣሠሉት መጻሕፍት ውስጥ በትክክል ተጽፎና ሰፍሮ የሚገኝ ነው ይሁን እንጂ እነዚህን የመሠሉ የቃሉ እውነቶች በበተክርስቲያን መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈውና ሰፍረው ቢገኙም ደፋሩ ዘርዓያዕቆብ ግን ለእነዚህ ተጽፈው ላሉ እውነቶች ቦታ ባለመስጠት ሥልጣኑን ተገን አድርጎ እንደ ተአምረ ማርያም ያሉ የወንጌሉን እውነት የሸፈኑ የጨለማ መጻሕፍትን በመጻፍ ከዚህም ሌላ መጻሕፍትን በማያውቁ ፣ ቅዠት ናላቸውን ባዞረውና በተወናበዱ የዋሻ ፣ የገድል ነዋሪ ባሕታውያን የተጻፉ ገድላትና ድርሳናትን በመሰብሰብ ምን የመሰለችዋን ኦርቶዶክሳዊት የወንጌል ቤተክርስቲያን እስከዛሬ ድረስ የአሮጊቶች ተረት መከማቻና መጠራቀምያ አደረጋት ቅዱሳን ወገኖቼ ትምህርቱ በስፋት የሚጠቁመን አሁንም ይህንኑ እውነት ነው ታድያ ተጨባጭ የሆነውን ይህን እውነት ለሕዝባችን ለመስጠት እያንዳንዱን ሃሳብ በጥልቀት በተናጠልና በዝርዝር የምናይበት ትምህርት ስለሆነ ሰፊ ትንታኔ ለመስጠት በዚህ አርዕስት ዙርያ ለተወሰኑ ጊዜያቶች እንቆያለንና በማስተዋል እንድትከታተሉ ጥሪዬን ለእናንተ ለወገኖች በፍቅር ማስተላለፍ እወዳለሁ ግንዛቤያችሁ ይበልጥ እንዲጨምር ግን ይህንኑ የተለቀቀውን ቪዲዮ ደግማችሁ ስሙት ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

No comments:

Post a Comment