Thursday 26 May 2016

የመጽሐፍቅዱስ አንድነትና ኅብረት Part 5

የመጽሐፍቅዱስ አንድነትና ኅብረት Part 5



Related image

7ኛ ) የመጽሐፍቅዱስ አንድነትና ኅብረት


Related image

መጽሐፍቅዱስ የ66ቱ ቤተ መጻሕፍት መጽሐፍ ነው መጽሐፍቅዱስ የተጻፈው አንድ ሺህ ስድስት መቶ አመት በፊት ነበር ወደ 40 የሚደርሱ ጸሐፊዎች ነበሩ ወደ ሦስት ለሚደርሱ አህጉራት ተጽፈዋል ኢሲያ አፍሪካና ኤሮፕ ለተባሉ ሀገሮች የተጻፉ ናቸው መጽሐፍቅዱስ ብዙ ከማይስማሙና ከሚያከራክሩ ባለቤቶች ጋር  በጥልቀት ይወያያል ያወራል እስካሁን ግን አስደናቂ የሆነ የአንድነት ንግጝር አለው መጽሐፍቅዱስ ለእኛ ሲነበብልን በአንድ ሰው እንደተጻፈ ሆኖ ነው ተአምረኛው የመጽሐፍቅዱስ አንድነት የቀረበው በመለኮታዊ ተነሳሽነት ነው ማለትም በመለኮታዊ ኢንስፓይሬሽን ነው ልዩ ልዩ አይነት ጸሐፊዎች ሁሉም ተነሳሽነት ያገኙት ወይም ኢንስፓየርድ የሆኑት በአንዱ አይነት መንፈስ መንፈስቅዱስ ነው ሌሎች መጻሕፍቶች አይነጻጸሩትም ወይም አይወዳደሩትም በሀሳብ የተገናኙትም 40 ልዩ ልዩ ሰዎች እየኖሩ የነበሩት በልዩ ልዩ የአለም ክፍሎች ነው እንደገናም ልዩ ልዩ የታሪክ ጊዜያቶች ለመጻፍም ብዙ የሆኑ  የማይስማሙ የሚያከራክሩ ባለቤቶች  የሚመሳሰሉና አንድ አይነት ንጝግር ያላቸውን መጻሕፍት ከአንድ ጸሐፊ ማግኘት ያለ ነው መጽሐፍቅዱስ የተለየና ልዩ ጠባይም ያለው ነው


 

Related image



 Related image

8ኛ ) የኢየሱስ አቁዋም በብሉይና በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት

 Related image

ኢየሱስ በምድር ላይ ሲመላለስ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ነበሩ እርሱም በተከታታይ የሚጠቅሳቸውና ሥልጣን ያላቸው እምነትም የሚጣልባቸው ነበሩ ወንጌልን ስናነብ ኢየሱስ የብሉይኪዳን መጻሕፍት ሁኔታዎች ፍጹም የሆነ ታሪካዊነት ያላቸው መሆናቸውን ለእኛ ግልጽ አድርጎ አሳይቶአል ኢየሱስ የፍጥረትን የመምጣታቸውን ሂሳብ ማለትም በኖህ ዘመን የነበረውን የጥፋት ውሃ ቀን እና ዮናስ በአሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ የመኖሩን ትርጉዋሜ ያለውና ፍጹም ስሕተት የሌለበት ሁኔታ መሆኑን በሃላፊ ታሪክ ውስጥ ወስዶ አገናዝቦአል  ኢየሱስ እግዚአብሔር የሆነና የእኛንም ሥጋ ጨምሮ የያዘ ነው እግዚአብሔር በእኛ ሰብአዊ ሰውነት መጽሐፍቅዱስን  ማለትም የብሉይኪዳን መጻሕፍት በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል እንደነበሩ ያመነ ነው እኛም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ  አንድ አይነት እይታ መያዝ አስፈልጎናል እርሱ የእግዚአብሔር ቃል ነበረውና ሃሳባችንን ስናጠቃልል መጽሐፍቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ሆኖ  ተነሳሽነት ያለውና ሃሳብ የሰጠ ወይንም ኢንስፓየርድ እንደሆነ ማስረጃ አለ ስለዚህ ልናነበውና ልንታዘዘው ያስፈልጋል መጽሐፍቅዱስን ለሕይወታችን ታማኝ አድርገን  ( እምነት የምንጥልበት አድርገን ) መያዝ በሕይወታችንም ላይ የመጨረሻ ሥልጣን ያለው መሆኑን መረዳት እና  ማስተዋል አለብን መጽሐፍቅዱሳችን በበለጠ፣ በተሻለና በተለየ ሁኔታ እምነት የምንጥልበት   እግዚአብሔርንም  በእርግጠኝነት ምን እንደሚመስልና እኛም እንዴት መኖር እንዳለብን እንደሚፈልግ አበክረን የምንመለከትበት የዘገባችን የኢንፎርሜሺናችንም ምንጭ ነው



No comments:

Post a Comment