Wednesday 25 May 2016

የመጽሐፍቅዱስ መልእክት ሕይወትን ይለውጣል Part 3

የመጽሐፍቅዱስ መልእክት ሕይወትን ይለውጣል    

Part 3

Image result for The message of the bible transforms lives

5ኛ ) የመጽሐፍቅዱስ መልእክት ሕይወትን ይለውጣል


ሕዝቦች በቀጥታ በታሪካቸው ውስጥ በአሁኑ ሰአት በመጽሐፍቅዱስ መልእክት በእርግጠኝነትና በማያጠራጥር ሁኔታ ሕይወታቸው ይለወጣል ይህ የጋራ ልምምድ የቤተሰብ አስተዳደጋቸውን ሳይመለከቱ መጽሐፍቅዱስን በሕይወታቸው ሥራ ላይ ሊያውሉና ሊተረጉሙ በሚፈልጉ ሰዎች  የሚደርስ ነው ተመሳሳይ ለውጦች ልምምድ እየተደረጉ ያሉት በሃብታሙና በደሃው  እንደገናም በከፍተኛ ወይንም በዝቅተኛ ሁኔታ በተማሩ በሰለጠኑ ወንዶችና ሴቶች  ወጣቶችና ሽማግልኤዎች  ታዋቂ በሆኑና ባልታወቁ ሰዎች ነው በክርስቶስ እምነት ያሉና በመጽሐፍቅዱስ ትምህርት የሚኖሩ አዲስ ደስታን ሰላምንና የመኖር አላማን ልምምድ ያደርጋሉ

) የእግዚአብሔር ቃል ወደ እያንዳንዳችን ከተላከ በሁዋላ ምን ይሆናል ስንል መልሱን ከኢሳይያስ የትንቢት መጽሐፍ በሚገባ እናገኘዋለን

ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል፤ የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም ( ኢሳይያስ 55 11 )

 


) በእግዚአብሔር ቃል መሠረት የመኖር ውጤቱ ምንድነው ስንል አሁንም መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ ሲል መልስ ይሰጠናል


ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው (መዝሙር 119 9 )

) እምነት በሰውየው ውስጥ ምንን ያስገኛል ስንል መልሱን አሁንም ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ በተገቢው መንገድ ይሰጠናል

እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው( ሮሜ 10 17 )

 


6ኛ ) የጸሐፊዎች ምስክርነት


 

የመጽሐፍቅዱስ ጸሐፊዎች ለጻፉት የምስክርነት ሁኔታ ሁልጊዜ የአይን ምስክሮች ነበሩ በተመሣሣይ ምክንያትም ከእግዚአብሔር መገለጥን የተቀበሉ አይደሉም ወደ ወንጌል ስንመጣ ከሰው ያገኘነው እውቀት ወይም ወሬ የተዘጋጀው በአይን ምስክርነት ነው ከዮሐንስ በስተቀር የኢየሱስ ደቀመዛሙርት የሞቱት በሰማእትነት ነው የክርስቶስን ሕይወት ሂሳብ ከመካከላቸው ፍጹም የለወጠ የለም

) በዚህ ውስጥ ሉቃስ ያገኘው የራሱ ዘገባ ወይንም ኢንፎርሜሺን ምንድነው ስንል መልሱን __ በሉቃስ ወንጌል ምእራፍ 1 1 እና 2 ላይ በግልጽ ተጽፎ እናገኘዋለን የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ  ይለናል

) በ2ኛ ጴጥሮስ 1 16 ላይ ደግሞ  ጴጥሮስም ስለ ኢየሱስ ያገኘው ዘገባ ምንድነው ብለን ስንል የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ በማለት ይናገረናል

) እንደገናም ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ያገኘው ዘገባ ምንድነው ስንል አሁንም መልሱን በ1ኛ ዮሐንስ 1 1 _ 3 ላይ እናገኘዋለን


በ1ኛ ዮሐንስ 1 1 _ 3 ላይ ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው ይለናል





No comments:

Post a Comment