Thursday 24 October 2019

Sunday 20 October 2019

የልዳው ጊዮርጊስ የቤተክርስቲያን ራስ ነው ተብሎ የተነገረበትን የዘመናት ተረት የሻረ አስደናቂ የክርስቶስ ወንጌል ... = የልዳው ጊዮርጊስ የቤተክርስቲያን ራስ ነው ተብሎ የተነገረበትን የዘመናት ተረት የሻረ አስደናቂ የክርስቶስ ወንጌል ዛሬ ተሰበከ ክርስቶስ ራስ በሆነበት ቦታ ጊዮርጊስን ራስ ያለች ቤተክርስቲያን ይህ አልበቃ ብሏት ደግሞ የልዳው አንበሳ ሦስት ጊዜ ሞቶ ሦስት ጊዜ ተነሣ ስትል ጊዮርጊስን ቀን መድባና በዓል ሰርታ ብታከብረውም ፣ ሃይማኖተ አበው የተባለው የገዛ መጽሐፍዋ ግን ይህንን ተረት ተቃውሞ ክርስቶስ ጌታችን ከሙታንም ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ማንንም በሥጋ እንዳላስነሣ አስተውል ሲል ተናገረ ( ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 59 ፥ 49 እና 50 ) :: ይህንን እውነት ይዘን ነው እንግዲህ ከመጽሐፍቅዱስ እውነት ጋር በማገናዘብ ለእናንተ ለአድማጮች ዛሬ ይህንን መልዕክት ለማድረስ የወደድነው ስለዚህ መልዕክቱን በመስማት ተባረኩ ለሌሎችም ሼር ሸር ሼር አድርጉ ይብቃን እንግዲህ ዘመኑ የወንጌል እንጂ የተረትና የተረት አባቶች ዘመን አይደለም :: ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ

Saturday 19 October 2019

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ስድስት)

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ስድስት): (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! መ) ዶግማ እና ቀኖና   ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች! እንዴት አላችኁ? ...

Saturday 12 October 2019

ጌታ እንዲያገኝህ ፍቀድለት ( የሉቃስ ወንጌል 18 : 35 — 43 )





ጠቃሚ ምክር


( ክፍል አራት  )


ከሰማኋቸውና ካነበብኳቸው


የዕለት እንጐቻ



« ፎከስድ የሆነ ውሃ እኮ ድንጋይ ይሰብራል  »


ከኢንጂነር ዘማሪ ግዛቸው የተወሰደ የክፍል ሁለት የምስክርነት ቃል 


ሙሉውን ሃሳብ ለማግኘት ከዚህ በታች ሊንኩን ስለማስቀምጠው ገብታችሁ መስማት ትችላላችሁ   https://youtu.be/2Or8Ruv5x9U


ውድ ወገኖቼ ሆይ የጌታ ሰላም ይብዛላች በማለት መልዕክቴን እቀጥላለሁ :: ይሄ የድሮ ዘማሪ ይህንን ሃሳብ ያነሳው ፎከስድ የሆነ አገልግሎት የሚያስገኘውን ውጤታማነት ለመግለጽ ነው :: ከዚህም የተነሳ ይሄ የተወደደ ዘማሪ ከአምስት ዓመት በፊት ፎከስድ ወይንም ዳይሬክትድ ሆኖ ለማገልገል ምኞቱን ለጌታ በጸሎት እንዺህ ሲል ገለጸ :: «ጌታ ሆይ በጌታ ውጪ እንዳለ እንደሰበቀ ጦር ፎከስድ ሆኜ እንዳገለግልህ እርዳኝ » ::  ወገኖቼ ምን ዓይነት ድንቅ ጸሎት ነው :: ይሄ ሃሳብ ነው እንግዲህ  እኔንም ውስጤን ቀስቅሶ ከወንድሜ ኢንጂነር ዘማሪ ግዛቸው ጋር የተያያዘውን መልዕክቴን  እንዲህ ስል ለእናንተ ለማቅረብ የወደድኩት ::

የልብ ንጽሕናንና ለውጥን የሚፈልጉ ሰዎች በአንድ ወቅት በእግዚአብሔር ቃል ወደሚያገለግል ወደ አንድ አገልጋይ ሄደው እንዲህ ሲሉ ጠየቁት ይባላል :: የልብ ንጽሕናና ለውጥን ማግኘት እንፈልጋለን ስለዚህ ለዚህ ጉዳያችን ምን ማድረግ እንዳለብን ብትመክረን አሉት :: አገልጋዩም ሲመልስ  የወሃ ጠባይ ለስላሳ ነው  ፣ የድንጋይ ጠባይ ጠጣር ነው  ነገር ግን ውሃ በጠርሙስ ተደርጎ ከድንጋዩ በላይ ከተያዘና ውሃ የሚያንጠባጥብ ከሆነ ቀስ በቀስ ድንጋዩ መሰባበሩ አይቀርም  ፣ ቃለ እግዚአብሔርም ለስላሳ ነው  ፣ ልቡናችን ደግሞ ጠጣር ነው ነገር ግን ሰው የእግዚአብሔርን ቃል አዘውትሮ የሚሰማ ከሆነ ልቡናው ከጥቂት ጊዜ በኋላ ለፈሪሃ እግዚአብሔር ማለትም እግዚአብሔርን ለመፍራት ቦታ መስጠቱ አይቀሬ ነው አላቸው ይባላል :: ከዚህ ጋር ተያይዞ ፦————————————————

የዘማሪ መጋቢ ዳንኤል አምደ ሚካኤልን የመዝሙር ሊንክ አስቀምጫለሁ በመስማት ተባረኩ   https://youtu.be/alU0JgcK2hc 

https://youtu.be/b1yufNRFMs0


አባ ዮናስ ጌታነህ 


Monday 7 October 2019






ጠቃሚ ምክር


( ክፍል ሦስት )


ከሰማኋቸውና ካነበብኳቸው


የዕለት እንጐቻ



አንድ ወንድም ወደ አንድ አገልጋይ መጥቶ ብዙ ሃሳቦች ወደ ልቡናዬ መጥተው እያስቸገሩኝ ነው ብሎ ጠየቀው :: አገልጋዩም እንዲህ ሲል መከረው ::  በውስጥህ ያለውን አየር ተንፍሰህ ወደ ውጪ አውጣውና  መልሰህ አየር ወደ ውስጥ አስገብተህ ተንፍስ አለው :: ይህም ወንድም አገልጋዩ እንዳለው በውስጡ ያለውን አየር  ተንፍሶ  ወደ ውጪ አስወጣውና መልሶ አየር ወደ ውስጥ አስገብቶ ተነፈሰ:: አገልጋዩም እንደገና ይህንን ወንድም እንዲህ ሲል መከረው :: ከዚህ በኋላ አንዴ ወደ ውስጥ ያስገባኸውን አየር ተንፍሰህ ወደ ውጪ አስወጥተሃልና መልሰህ አየር ወደ ውስጥህ አታስገባ አለው :: ይህም ሰው አልችልም አለ :: አገልጋዩም ይህንን ሰው መልሶ አየህ ወደ ልቡናህ መጥተው የሚያስቸግሩህንም ሃሳቦች እንደዚህ ወደ ውስጥህ አለማስገባት ትችላለህ አለው ይባላል :: 

አንድ ዘማሪ እንዲህ ሲል ዘመረ ፦— 


አላስተናግድም በሬንም አልከፍትም 

ከኢየሱሴ ሌላ እንግዳ አልፈልግም …………………





አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ 

የሕይወትህ መውጫ ከእርሱ ነውና 

የአፍህን ጠማማነት ከአንተ አውጣ ሐሰተኞቹን ከንፈሮችም ከአንተ አርቅ 

( መጽሐፈ ምሳሌ 4 23 እና 24 )


እርሱም አለ ከሰው የሚወጣው ሰውን የሚያረክስ ነው ከውስጥ ከሰው ልብ የሚወጣ ክፉ ሃሳብ ዝሙት መስረቅ መግደል ምንዝርነት መጎምጀት ክፋት ተንኮል መዳራት ምቀኝነት ስድብ ትዕቢት ስንፍና ናቸውና ይህ ክፉ ሁሉ ከውስጥ ይወጣል ሰውንም ያረክሰዋል 

( የማርቆስ ወንጌል 7 14 - 23 )


በቀረውስ ወንድሞች ሆይ እውነተኛ የሆነውን ነገር ሁሉ ጭምትነት ያለበትን ነገር ሁሉ ጽድቅ የሆነውን ነገር ሁሉ ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ ፍቅር ያለበትን ነገር ሁሉ መልካም ወሬ ያለበትን ነገር ሁሉ በጎነት ቢሆን ስጋናም ቢሆን እነዚህን አስቡ ከእኔ የተማራችሁትንና የተቀበላችሁትን የሰማችሁትንም ያያችሁትንም እነዚህን አድርጉ የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል 

( ፊልጵስዩስ 4 8 እና 9 )


የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነውን ነገር ምን እንደሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ 

( ሮሜ 12 1 - 3 )


ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ በአዕምሮአችሁ መንፈስ ታደሱ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ 

( ኤፌሶን 4 22  - 24 )



አባ ዮናስ ጌታነህ 

ተዝካርና ፍትሐት በመጽሐፍቅዱስ ዕይታ ( ክፍል አምስት )

Sunday 6 October 2019







ሰላምን እንድንከተላት የተወለደልን ክርስቶስ ወይስ ጊዮርጊስ ?


የጥንትዋ ሐዋርያዊቷ ኦርቶዶክሳዊት ወንጌል ሰባኪዋ ሳትሆን የአሁንዋ ወይንም የዛሬዋ ኦርቶዶክስ እንዲህ ትለናለች 



ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ ጊዮርጊስ ተወልደ ነዋ 





ትርጉም ጊዮርጊስ እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ( የጥር 2 ዚቅ ) 


በዚሁ በኦርቶዶክስ መጽሐፍ ውስጥ ይህንን ሃሳብ የሚያፈርስ ቃል እንዲህ ሲል ተጽፎአል 



ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ መድኃኒነ ተወልደ ነዋ 


መድኃኒታችን እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ( የልደት ሰላም ምልጣን )

ወድ ወገኖቼ ሆይ ለዳኝነት መጽሐፍቅዱሳችንን ሳንገልጥ በዚህች ቤተክርስቲያን ውስጥ ሁለት የማይገናኙ ሃሳቦች እናገናኛችሁ ወይም እናስታርቃችሁ ብንላቸው እንኳ አንዱ በሌላው ከመሸነፍና ከመዋጥ ውጪ ሌላ መታረቅያ መንገድ የማናገኝላቸውን  ሃሳቦችን አግኝተናል :: ታድያ እነዚህ ሃሳቦች ለማናችንም የተሰወሩ ስላልሆኑ ለማመሳከርያ ስንል እንኳ መጽሐፍቅዱሳችንን መግለጥ ባንፈልግም  በመወለዱ ሰላምን ያመጣው ክርስቶስ መሆኑ ለመጥቀስ   ጌታ በተወለደበት ሌሊት መላዕክቱ ያሰሙት የሰላም መዝሙር ሳይጠቀስ አይታለፍም ( የሉቃስ ወንጌል  2 : 10 ) :: እንደገናም በዚህ ጉዳይ   መጽሐፍቅዱስን ያላነበበ ማንንም ሰው ብንጠይቀው እንኳ መድኃኒት ሊሆነው የተወለደለት ኢየሱስ መሆኑን ስለሚያውቅ ምርጫው አድርጎ መከተል የሚፈልገው  ኢየሱስን ነው :: ስለሆነም መድኃኒታችን እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ሲል በትክክለኛ ምርጫው ኢየሱስን ሊከተል ይወስናል  እንጂ ጊዮርጊስን መድኃኒት አድርጎ በመቀበል  ጊዮርጊስን ለመድኃኒትነት መርጦ ጊዮርጊስ እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት በማለት ጊዮርጊስን የመከተል ምርጫው አያደርግም:: ቤተክርስቲያኒቱ ግን ትምህርቷን እንደ ቃሉ ባለማድረግ በዚሁ የተረት መጽሐፏ ሕዝቡን በመንታ መንገድ ላይ  አቁማው ትገኛለች :: መድኃኒት የሚያስፈልገውን ጊዮርጊስ የተባለውንም ፍጡር መድኃኒት ከሆነው ከኢየሱስ ጋራ በእኩል ደረጃ አስቀምጣ ሰዉ መድኃኒቱና ምርጫውም አድርጎ ኢየሱስን እንዳይከተል ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ ጊዮርጊስ ተወልደ ነዋ ጊዮርጊስ እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ስትል ሰዎች መድኃኒት የሆነውን ኢየሱስን ከመከተል ይልቅ ጊዮርጊስን መድኃኒቴ ብሎና መድኃኒቱ አድርጎ እንዲከተል ስታበረታታ ትገኛለች :: ስለዚህ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሆይ እውነትን ከስሕተት ትለይ ዘንድ እነዚህ ሃሳቦች ቀርበውልሃል በመሆኑም ኢየሱስን ተከትለህ መዳን ሲገባህ ከዚህ ይልቅ ጊዮርጊስ ተወልዶልኛልና ሰላምን ልከተላት ብትል በራስህ  ላይ የፈረድክ ራስህ ነህና ምርጫው የአንተ ነው :: እንደገናም የተወለደልኝ ኢየሱስ ነውና ሰላምን ልከተላት ብትል አሁንም ምርጫው የአንተው የራስህ ነው :: ለዛሬ ጽሑፌን በዚሁ አበቃሁ ተባረኩ:: 


እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና ( ኤፌሶን 2: 14 - 18 )


ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ ከክፉ ፈቀቅ ይበል፥ መልካምንም ያድርግ፥ ሰላምን ይሻ ይከተለውም፤ የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፥ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው። ( 1ኛ ጴጥሮስ 3 : 10 - 12 )

አባ ዮናስ ጌታነህ 

Saturday 5 October 2019

https://images.app.goo.gl/sbKNCGpB7yZHxnbo9



ሰላምን እንድንከተላት የተወለደልን ክርስቶስ ወይስ ጊዮርጊስ ?


የጥንትዋ ሐዋርያዊቷ ኦርቶዶክሳዊት ወንጌል ሰባኪዋ ሳትሆን የአሁንዋ ወይንም የዛሬዋ ኦርቶዶክስ እንዲህ ትለናለች 



ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ ጊዮርጊስ ተወልደ ነዋ 





ትርጉም ጊዮርጊስ እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ( የጥር 2 ዚቅ ) 


በዚሁ በኦርቶዶክስ መጽሐፍ ውስጥ ይህንን ሃሳብ የሚያፈርስ ቃል እንዲህ ሲል ተጽፎአል 



ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ መድኃኒነ ተወልደ ነዋ 


መድኃኒታችን እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ( የልደት ሰላም ምልጣን )

ወድ ወገኖቼ ሆይ ለዳኝነት መጽሐፍቅዱሳችንን ሳንገልጥ በዚህች ቤተክርስቲያን ውስጥ ሁለት የማይገናኙ ሃሳቦች እናገናኛችሁ ወይም እናስታርቃችሁ ብንላቸው እንኳ አንዱ በሌላው ከመሸነፍና ከመዋጥ ውጪ ሌላ መታረቅያ መንገድ የማናገኝላቸውን  ሃሳቦችን አግኝተናል :: ታድያ እነዚህ ሃሳቦች ለማናችንም የተሰወሩ ስላልሆኑ ለማመሳከርያ ስንል እንኳ መጽሐፍቅዱሳችንን መግለጥ ባንፈልግም  በመወለዱ ሰላምን ያመጣው ክርስቶስ መሆኑ ለመጥቀስ   ጌታ በተወለደበት ሌሊት መላዕክቱ ያሰሙት የሰላም መዝሙር ሳይጠቀስ አይታለፍም ( የሉቃስ ወንጌል  2 : 10 ) :: እንደገናም በዚህ ጉዳይ   መጽሐፍቅዱስን ያላነበበ ማንንም ሰው ብንጠይቀው እንኳ መድኃኒት ሊሆነው የተወለደለት ኢየሱስ መሆኑን ስለሚያውቅ ምርጫው አድርጎ መከተል የሚፈልገው  ኢየሱስን ነው :: ስለሆነም መድኃኒታችን እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ሲል በትክክለኛ ምርጫው ኢየሱስን ሊከተል ይወስናል  እንጂ ጊዮርጊስን መድኃኒት አድርጎ በመቀበል  ጊዮርጊስን ለመድኃኒትነት መርጦ ጊዮርጊስ እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት በማለት ጊዮርጊስን የመከተል ምርጫው አያደርግም:: ቤተክርስቲያኒቱ ግን ትምህርቷን እንደ ቃሉ ባለማድረግ በዚሁ የተረት መጽሐፏ ሕዝቡን በመንታ መንገድ ላይ  አቁማው ትገኛለች :: መድኃኒት የሚያስፈልገውን ጊዮርጊስ የተባለውንም ፍጡር መድኃኒት ከሆነው ከኢየሱስ ጋራ በእኩል ደረጃ አስቀምጣ ሰዉ መድኃኒቱና ምርጫውም አድርጎ ኢየሱስን እንዳይከተል ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ ጊዮርጊስ ተወልደ ነዋ ጊዮርጊስ እነሆ ተወልዷልና አሁንም ሰላምን እንከተላት ስትል ሰዎች መድኃኒት የሆነውን ኢየሱስን ከመከተል ይልቅ ጊዮርጊስን መድኃኒቴ ብሎና መድኃኒቱ አድርጎ እንዲከተል ስታበረታታ ትገኛለች :: ስለዚህ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሆይ እውነትን ከስሕተት ትለይ ዘንድ እነዚህ ሃሳቦች ቀርበውልሃል በመሆኑም ኢየሱስን ተከትለህ መዳን ሲገባህ ከዚህ ይልቅ ጊዮርጊስ ተወልዶልኛልና ሰላምን ልከተላት ብትል በራስህ  ላይ የፈረድክ ራስህ ነህና ምርጫው የአንተ ነው :: እንደገናም የተወለደልኝ ኢየሱስ ነውና ሰላምን ልከተላት ብትል አሁንም ምርጫው የአንተው የራስህ ነው :: ለዛሬ ጽሑፌን በዚሁ አበቃሁ ተባረኩ:: 


አባ ዮናስ ጌታነህ 

ይድረስ ለሐዋርያው ይዲድያና ልጁ ነኝ ለሚለው ለሐዋርያው እሥራኤል ዳንሳ እንዲሁም ይህ መልዕክት ለሚመለከታችሁ ሁሉ...

Thursday 3 October 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ ሰዎች ለእግዚአብሔር መዝሙር ወይም ምሥጋና ሊያሰሙ የፈለጉበት ምክንያቶቻቸው ምንድናቸው ? ---- የመልዕክት ርዕስ ፦ ሰዎች ለእግዚአብሔር መዝሙር ወይም ምሥጋና ሊያሰሙ የፈለጉበት ምክንያቶቻቸው ምንድናቸው ? ከዚህ በመቀጠል እነዚህን ስምንት ነጥቦች የርዕሳችን መንደርደርያና የትምህርቱም ዋና ዋና ሃሳቦች ስለሆኑ በማስተዋል ተመልከቷቸው 1ኛ ) ከዳዊት ምክንያቶች ጥቂቶቹ ፦——— እግዚአብሔር ሰማ ማረኝም እግዚአብሔር ረዳቴ ሆነኝ ክብሬ ትዘምርልህ ዘንድ ዝምም እንዳትል ልቅሶዬን ለደስታ ለወጥህልኝ ማቄን ቀድደህ ደስታንም አስታጠቅኸኝ አቤቱ አምላኬ ለዘላለም አመሰግንሃለሁ - - - - - ( መዝሙር 29 ( 30 ) ፥ 10 - 12 ) 2ኛ ) ዳዊት በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ብቻ ዘምሮ ሊቀር ውሳኔ ያደረገ ነበረ መዝሙር 62 ( 63 ) ፥ 1 _ 11 ፤ መዝሙር 104 ፥ 33 ፤ መዝሙር 146 ፥ 2 3ኛ ) ሰዎች መዝሙርን ለእግዚአብሔር ሊያሰሙ የፈለጉበት ምክንያቶቻቸው ሲበላሽ መዝሙራቸውም ሆነ በአጠቃላይ መዝሙራቸውን ያቀረቡበት መንገዳቸውም ሁሉ አብሮ ይበላሻል ለእግዚአብሔር ዘመናዊ በሆኑ በሳክስፎንና በኦርጋን ስለዘመርን እግዚአብሔርን ዘመናዊ አናደርገውም ፣ በባሕላዊ መሣርያዎች በክራር በመሰንቆና በዋሽንት ስለዘመርን ደግሞ እግዚአብሔርን ጥንታዊ አናሰኘውም :: ይሄ እግዚአብሔር በክራርና በዋሽንት ስለስለተዘመረለት ኋላ ቀር አይደለም ፣ በሳክስፎንና በጊታር ስለዘመርንለት ደግሞ ዘመነኛ አይሆንም :: እርሱ ዘመን የማይቆጠርለት ዘመንም የማይወስነው አልፋና ኦሜጋ ነው ራዕይ 1 ፥ 8 ፤ መዝሙር 102 ፥ 12 ፣ 26 _ 27 ፤ ዕብራውያን 13 ፥ 8 :: ከዚህ የተነሳ የሰዎች መዝሙራቸው ሳይሆን መዝሙራቸውን ያቀረቡበትን መንገዳቸውንም ሆነ ምክንያቶቻቸውን በማስተዋል ልናይላቸው ይገባል ፣ ሊያስተካከሉ በተገባቸው ሁኔታ ደግሞ እንዲያስተካክሉ ልንረዳቸው ያስፈልጋል :: 4ኛ ) ምክንያቶቻቸው የተበላሹባቸው እሥራኤል ዘምረው የዘፈኑ ነበሩ ስለዚህ ዘፍነን ከሆነ ወደ መዘመር ያምጣን እንጂ ዘምሮ ከመዝፈን ግን እግዚአብሔር ይጠብቀን ዘጸአት 15 ፥ 19 _ 21 ፤ ዘጸአት 32 ፥ 15 _ 35 ፤ የማቴዎስ ወንጌል 26 ፥ 30 5ኛ ) የምንዘምርበት መንገድ በተለያዩ ምክንያቶች ሊበላሹ ይችላሉ ፣ የሚዘምሩበት ምክንያት ከተበላሹባቸው ሰዎች መካከል አንደኛው የጠፋው ልጅ ታላቅ ወንድም ነው ፣ ሌላዎቹ ደግሞ በሆሳዕና ዕለት የሕጻናቱን ምስጋና የተቃወሙ ፈሪሳውያኑ ናቸው :: የሉቃስ ወንጌል 15 ፥ 25 _ 32 ፤ የሉቃስ ወንጌል 19 ፥ 27 _ 40 6ኛ ) የምንዘምርበት ምክንያቶቻችን እንዳይበላሹብን የእግዚአብሔርን ዝማሬ በባዕድ ምድር እንዴት እንዘምራለን ? ልንል ፣ ኢየሩሳሌም ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ስንልም ባለንበት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ በውሳኔ ልንቆም ይገባል መዝሙር 136 ( 137 ) ፥ 1 _ 5 7ኛ ) ያ ካልሆነ ግን የሕይወት ብልሽት ይገጥመናል ፣ ሰዎችም ይዘባበቱብናል ( መሣፍንት 16 ፥ 23 -25 ) 8ኛ ) የመዘመር ምክንያቶቹ ያልተበላሸበት ዳዊት ልቤ ጽኑ ነው እቀኛለሁ እንዳለ ለሚስቱም ለሜልኮል ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት ዘፍኛለሁ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእሥራኤል ላይ አለቃ እሆን ዘንድ ከአባትሽና ከቤቱ ሁሉ የመረጠኝ እግዚአብሔር የተባረከ ይሁን ስለዚህም በእግዚአብሔር ፊት እጫወታለሁ ሲልም እንደተናገረ እኛም ከሃሳባቸው ጋር ባለመስማማታችን ምክንያት ለናቁን የዘመናችን ሜልኮሎች ሁሉ እንዲህ ልንል ይገባል ከዚያም መልስ በሰነዘሩት ሃሳባቸውም ሳይቀር ላለመሸነፍ ልባችንን በዚያው መንገድ ልናጸናው ያስፈልጋል መዝሙር ( 108 ) ፥ 1 _ 13 ፤ 2ኛ ሳሙኤል 6 ፥ 21 ወይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ አባ ዮናስ ጌታነህ