Saturday 28 December 2019

[ኦ አምላኬ አስደንጋጩ ሚስጥር ይፋ ሆነ] በእስራኤል ዳንሳ ገስት ሃውስ ውስጥ የሞቱ የ4 ሰዎችን አስክሬን ገንዣለሁ የሐዋርያነትንና የፓስተርነትን ስም ለብሰው ጉድ ያፈሉ ነጭ ዱርዬዎች አሳፋሪው ገበና የተጋለጠበት ይህችን ነጭ ዱርዬዎች የምትለዋን አባባል ያገኘሁት ወይዘሮ መዓዛና የተወደደው ወንድማችን አርቲስት ዳዊት ወልደ ዮሐንስ በየኔታ ቲዩብ ከሰጡት ኢንተርቪው ውስጥ ነው በመሆኑም ይህቺ ነጭ ዱርዬዎች የምትለዋ ቃል በነ እስራኤል ዳንሳ ሠፈር ብቻ ሳይሆን በየአብያተ ክርስቲያናቱ ሁሉ ገቢራዊ ድርጊትን በመፈጸም ዓይን አውጥታና ፍጥጥ ብላ የሌባ ዓይነ ደረቅ ወይንም ዓይኔን ግንባር ያርገው የሚለውንም ስያሜ ተቀጽላ አድርጋ ያለ ፍርሃትና ያለ ይሉኝታ የምትኖር በመሆንዋ እጅግ በጣም የወደድኩዋት እና የተመቸችኝ የቃል ገለጣ ናት በዚህ አጋጣሚ ይህንን ጉድ ወደ አደባባይ ብቅ ያደረጉልንን የየኔታ ቲዩብ ፕሮግራም አዘጋጅንም ሆነ ወይዘሮ መዓዛንና አርቲስት ዳዊት ወልደ ዮሐንስን ተባረኩ ዛሬም በዘመናችን እንደ እነዚህ ያሉ አስመሳይ አካኖችንም እንዲህ በማጋለጥ ነቢዩ ናታን ዳዊትን እንዳለው እናንተም እንዲህ በግላጭ በሚዲያ ያ ሰው አንተ ነህ ማለትን አታቁሙ እላለሁ መጽሐፈ ኢያሱ ምዕራፍ 7 በሙሉ ፤ 2ኛ ሳሙኤል ምዕራፍ 12 በሙሉ ይነበብ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው አለ እንጂ ሲያጭበረብሩ ሲያታልሉ ሲዘርፉና ሲበዘብዙ ሲዋሹ ሲያስፈራሩም የሚያገኛቸው ብጹአን ናቸው አላለንም እስቲ መጽሐፉ የሚለውን አስተውለን እንመልከት የሉቃስ ወንጌል 12 ፥ 32 _ 48 ታድያ ይሄ ነገር እንዳይወጣባቸው መሣይ እስራኤል ዳንሳዎች ከጀሌዎቻቸው ጋር በመሆን እናንተን እንዳስፈራሩ እኛንም ከማስፈራራት አልቦዘኑም ከዚህ የተነሳ እኛም እንደ እናንተ እያለቀስን እንባችንንም ወደ ሰማይ እየረጨን ፍርዱን ለጌታ ሰጥተን ቁጭ ብለናል ይሁን እንጂ መስፈራራቱን ዛቻውንም ሆነ ግልምጫውን ችለን ስለ እውነት በተገፋንበት ጠባቡ ክፍላችን እውነቱ ይሰማ እያልን እና እየጮህን ነው መጽሐፋችንም እውነትን ግዛት እንጂ አትሽጣት የሚል ቃል ነውና ያስነበበን ጫናው ቢኖርም እውነቱን ግን አንለውጠውም የተወደዳችሁ ወገኖች እነዚህ ወገኖች ኢንተርቪው ያደረጉበትን ሊንክ ከዚሁ ጽሑፌ ጋር አያይዤ አስቀምጠዋለሁ መስማትም ሆነ መከታተል ትችላላችሁ ተባረኩ https://youtu.be/dL0wgKv45XA

666 ኢሊሚናቲ የአዲሱ የአለም መንግሥት ምልክቶች ( ክፍል አስራ ስድስት )

በሰሜን አሜሪካና በአካባቢዋ ለምትገኙ አብያተ ክርስቲያናት





የቀናተኛን ሰው እንጀራ አትብላ ጣፋጭ መብልም አይመርህ በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና ብላ ጠጣ ይልሃል ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም ( ምሣሌ 23 ፥ 6 እና 7 )





ወተት አጠጥቶ መግደልም ሆነ መገደል  እንጀራ ቆርሶ አሳልፎ መስጠትም ሆነ መሰጠት አለና ክርስትና አብሮ በበላሽም ሆነ አብሮ በጠጣሽ አለመሆኑን ብንማርና ብንረዳ ፣ እንደገናም በአንድነት እንጀራ መቁረስ መጽሐፍቅዱሳዊና አንድ ልብንም ሆነ ጥሩ ልብን የሚጠይቅ ሆኖ የሚበረታታ ቢሆንም ምናልባትም ከላይ እንደገለጥኩት አሁንም ሰዎች በልዩ ልዩ ጉዳዮቻቸው የተለየውን ዓላማቸውንና ተልዕኮአቸውን ሊፈጽሙ ይህንን መንገድ ይጠቀሙበትና በዚሁ ጉዳይ ሰዎችን የሚጎዱበት ፣ እግዚአብሔርም የሚያዝንበት ቢሆንስ እላለሁ :: እንደገናም በሰሜን አሜሪካ ላለን ሰዎች አሁንም እንጀራውንም ሆነ ክትፎውን ማዘጋጀት እንደ ሀገር ቤቱ ሕዝባችን ብዙም ዳገት ስለማይሆንብን ድሆችን ከማሰብና ለሌሎችም ከማካፈል ጋራ ሲሆን እንጂ አብሮ ተሰባስቦ ስለተበላ ብቻ የተዋጣላቸው መንፈሳውያን ናቸው የሚያስብለን አይሆንምና  እናስብበት የሚል መልዕክትም አለኝ ከዚህ በመቀጠል ለሀሳቤ መነሻ ጥቅሶች የሆኑኝን የመጽሐፍቅዱስ ክፍሎች አስቀምጣለሁና መጽሐፍዎን ከፍተው ያንብቡ ( መጽሐፈ መሣፍንት 5 ፥ 24 - 31 ፤ የዮሐንስ ወንጌል 13 ፥ 21 - 30 ፤ የሐዋርያት ሥራ 2 ፥ 41 - 47 ፤ የሉቃስ ወንጌል 7 ፥ 36 - 50 ፤ ምሣሌ 23 ፥ 6 እና 7 ፤ ሮሜ 14 ፥ 5  - 23 ፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 10 ፥ 31 - 33 ፤ ገላትያ 2 ፥ 10 ፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6 ፥ 17  - 20 ፤ ዕብራውያን 13 ፥ 16  ) ተባረኩ



አባ ዮናስ ሐዋርያዊ አገልጋይ

Wednesday 25 December 2019

ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ ...ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ መዝሙር ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኳችሁ በዚህ መዝሙር እንድትባረኩ ይህንን መዝሙር ጋብዤያችኋለሁ ከዚሁ ጋራ አያይዤ ነገ በተለመደው ሰዓታችን የጌታን ልደትን ምክንያት በማድረግ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ይኖረኛል ጌታ ይናገረናል ያስተምረናል ሁላችሁም ስለተጋብዛችሁ መቅረት የተከለከለ ነው ጌታ ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ

ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ ...ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ መዝሙር ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኳችሁ በዚህ መዝሙር እንድትባረኩ ይህንን መዝሙር ጋብዤያችኋለሁ ከዚሁ ጋራ አያይዤ ነገ በተለመደው ሰዓታችን የጌታን ልደትን ምክንያት በማድረግ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ይኖረኛል ጌታ ይናገረናል ያስተምረናል ሁላችሁም ስለተጋብዛችሁ መቅረት የተከለከለ ነው ጌታ ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ

ህዝቡን ያስለቀስ ዝማሬ "ክርስቶስ አለልን" ይድነቃቸው ተፈሪ Ethiopian Orthodox tewahedo Song

Friday 20 December 2019

የዘመኗ ቤተክርስቲያን መልክ

የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁንን :: ዛሬ በፊታችሁ ይህንን ርዕስ ወደ እናንተ ይዤ የቀረብኩበትን ምክንያት እንደሚከተለው አብራራለሁ :: የዘመኗ ቤተክርስቲያን መልክ የሎጥና የአብርሃም ዘመን መልክ እየሆነ ከመጣ ሰንበትበት ብሎአል :: እንዴት ለሚለው ጥያቄ ምላሼን እነሆ ብያለሁና ተከታተሉኝ ::
ሎጥና አብርሃም በመጽሐፍቅዱሳችን ቃል መሠረት ዘመዳሞችና ሎጥም የአብርሃም የወንድሙ ልጅ እንደሆነ ከቃሉ እናነባለን ኦሪት ዘፍጥረት 12 : 5 :: ይሁን እንጂ አብራም የእግዚአብሔር ጥሪ ደርሶት ከሀገሩና ከዘመዶቹ ተለይቶ በወጣ ጊዜ ሎጥ አብሮት አልተጠራም ፣ ማለትም የእግዚአብሔር ጥሪ አልደረሰውም ፣ እንዲሁ አብርሃምን ተከትሎ የወጣ መሆኑን አሁንም ቃሉ በግልጥ ይነግረናል ኦሪት ዘፍጥረት 12 ፥ 4 ፤ ኦሪት ዘፍጥረት 13 ፥ 1 :: ታድያ በእግዚአብሔር ተጠርቶ የወጣው አብራም በከብት ፣ በብርና በወርቅ እጅግ በበለጠገበት ወራት ፣ ከአብራም ጋር የሄደው ሎጥ ደግሞ የላምና የበግ መንጋ ድንኳንም ነበረው በአንድነትም ይቀመጡ ዘንድ ምድር አልበቃቸውም ፣ የነበራቸው እጅግ ነበረና በአንድነት ሊቀመጡ አልቻሉም የአብራምንና የሎጥን መንጎች በሚጠብቁት መካከልም ጠብ ሆነ በዚያም ዘመን ከነአናውያንና ፌርዛውያን በዚያች ምድር ተቀምጠው ነበር ይለናል ቃሉ ዘፍጥረት 13 ፥ 2 - 8 :: ይሁን እንጂ ይህ ጠብ ሲጀመር የሎጥና የአብራም እንጂ በሁለቱም በኩል ያለ የጠባቂዎቹ ጠብ አለመሆኑን አብራም በትክክል ጠንቅቆ ያወቀ ነውና አብራም ሎጥን እንዲህ አለው :: እኛ ወንድማማች ነንና በእኔና በአንተ በእረኞቼና በእረኞችህ መካከል ጠብ እንዳይሆን እለምንሃለሁ አንተ ግራውን ብትወስድ እኔ ወደ ቀኝ እሄዳለሁ አንተም ቀኙን ብትወስድ እኔ ወደ ግራ እሄዳለሁ አለው ይለናል ::
ውድ ወገኖቼ ሆይ የዘመኗ ቤተክርስቲያን መልክ ያልኩት እንግዲህ ከዚህ ታሪክ ተነስቼ ነው :: ሎጥ ከአብራም ጋር በፈጠረው ግጭት የአብራምንና የሎጥን መንጎች በሚጠብቁት መካከል ጠብ እንደሆነ ሁሉ ዛሬም በዘመናችን ባለች ቤተክርስቲያን ውስጥ አንድ ሎጥ ብቻ ሳይሆን ብዙ ችግር ፈጣሪ ሎጦች አሉና እነዚህ ሎጦች አብራምን ከመሰሉ በእግዚአብሔር ተጠርተው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተግባራዊ ከሚያደርጉና ወደ ፍጻሜም ከሚወስዱ ሰዎች ጋር በሚፈጥሩት ግጭት አንድ መንጋና አንድ ሕዝብ ሆኖ በሚኖረው በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል ትልቅ የሆነ መበጣበጥና ጦርነት ይፈጠራል :: ታድያ ሎጥ ሰላማዊ መስሎ አብራምን ተከትሎ እንደወጣ ሁሉ እነዚህም በአሁን ዘመን ላለች ቤተክርስቲያን የጠብ መንስዔ የሆኑ ሎጦች አብራምን ከመሰሉ የእግዚአብሔር ጥሪ ከደረሳቸው ሰዎች ኋላ ኋላ ተከትለው የወጡ ሰዎች ቢሆኑም ሰላማዊነታቸው ግን የሚፈልጉትን እስኪያገኙ ድረስና ቢያገኙም የማይጠግቡም ሆነ በቃኝ የማይሉ በመሆናቸው ያሻቸውን ሁሉ ሊያገኙ በወደዱት መጠን ማግኘት እስከ ቻሉ ድረስ ብቻ ነው :: ድንገት ቀና ያሉ እና ቀናም የሚሉ በመሆናቸውም የሚያነሱት ረብሻ መጠን የሌለውና ገደቡንም የሳተ ስለሆነ መቋጫም ሆነ እልባት ልናበጅለት አይቻለንም :: እነዚህን የመሰሉ ሰዎችን መገላገል የሚቻለው ቀኝና ግራ ሳይሉ ሁሉንም ዕድል ለእነርሱ አሳልፎ በመስጠትና የወደዱትንም እንዲያደርጉ በመፍቀድ ብቻ ነው :: ቊሳዊና ማቴሪያሊስት ስለሆኑ ወንድምነት የሚባለው ቋንቋ እንዲህ ላሉ ሰዎች ግልጽ አይደለም አይገባቸውምም :: ከወንድምነት ይልቅ ገንዘብን ጥቅምንና ክብርንም ጭምር ያስቀደሙ በመሆናቸው ወንድምነት ለተባለው የቤተሰብነት ሕይወት የታወሩ ናቸው :: ከእነርሱ ሳይሆን ከመንጋው መካከል በሚነሳው ብጥብጥ በጥባጭነታቸው የሚታወቅ መሠርይ ሰዎች ናቸው :: የዘመኗ ቤተክርስቲያን ሎጦች ላማራቸው ፣ ለመረጡትና ለለመለመው ነገር ካልሆነ በስተቀር ለመንፈሳዊው ነገር ዓይኖቻቸው የማይነሳና ማየትም የማይችሉ ምድራዊና ሥጋውያን ሰዎች ናቸው ::
ሎጥ ዓይኑን ያነሳውና እንደ እግዚአብሔር ገነት አምሳል የሆነችውን ዞአርን የመረጠው አብራም ቀኝና ግራ ሳይል ሁሉንም ምርጫ ለእርሱ ከሰጠውና ከተወለት በኋላ ነው :: እስከዚያ ድረስ ግን ሰላማዊ መስሎ በእረኞች መካከል እየገባ ጠብን የሚጭርና የሚያቀጣጥል ጉድጓድንም መንፈሳዊ ለሆነው ለአጎቱ ለአብራም የሚምስ ሰው ሆኖ የተገኘ ነው :: ስለዚህ የጠብ መነሻና መገኛ የሆነው ሎጥ በእውነተኛው በእግዚአብሔር ሰው በአብራም ካልሆነ በስተቀር በሌላው ሰው በፍጹም የሚታወቅ አይደለም :: የዘመናችን ሎጦችም እንደዚህ ናቸው :: በእውነተኞቹ በእግዚአብሔር ሰዎች ካልሆነ በስተቀር ጠብን የጀመሩም ሆነ የቀሰቀሱ እነርሱ መሆናቸው ጨርሶ አይታወቅም :: ይልቁንም መንፈሳዊና የሚጸልዩልን ናቸው ብለን ምስጢራችንንም ሁሉ ዝክዝክ አድርገን ልንነግራቸው እንችላለን :: እነርሱ ግን ዓይን ያወጡና በእግዚአብሔርም ስም መነገድን የለመዱ ስለሆኑ እኽ ብለውም ሆነ ተቆርቋሪ መስለው ይሰሙናል ፣ ነገር ግን ከቀናት በኋላ ለሞታችን የሚሆንን ጉድጓድ ሲምሱብን እናገኛቸዋለን :: የዘመናችን የቤተክርስቲያን ሎጦችም ታድያ እንዲህ በመሆናቸው ዓይን ያውጡ ሌቦች ናቸው :: ተከትለው ወጥተው ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ባነሱት ረብሻና ብጥብጥ ምክንያት ዋናና ፊተኛ መሆንን የሚፈልጉ በመሆናቸው ዓይናችንን ከፍተን ልናያቸውና እንደሚገባም ልናውቃቸው ይገባል እላለሁኝ ::
ሎጥ አብራም ዕድሉን ሁሉ ለእርሱ ሰጥቶትና ለቆለት በመረጠው ምርጫ ምክንያት አንዱ ከሌላው እርስ በእርሳቸው ተለያዩ በማለት የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል ኦሪት ዘፍጥረት 13 : 11 :: የዘመናችን የቤተክርስቲያን ሎጦች ግን እንዲህ አይደሉም እናንተ እንኳ ማንነታቸውን አውቃችሁ ጠብን ከመጥላት የተነሳ ወንድምነት ይበልጣልና እስቲ ዕድሉን ሁሉ ልስጠው እርሱም የወደደውን ያድርግ ስትሉ ሁሉንም ነገር ብትተዉላቸው ፣ እነዚህ ሰዎች ግን እጅግ የተለዩ ፣ በአብራምም ዘመን ዓይነት እንደነበረው ሎጥ ያይደሉ በመሆናቸው ኃጢአታቸው ገጦና ፈጦ የወጣ ሆኖ ሳለ በኃጢአታቸው ተጸጽተው ንስሐ የማይገቡ መንፈስቅዱስም የማይወቅሳችው ናቸው :: ከዚህም ሌላ የመረጡትን ዞአር የያዙ እንኩዋ ቢሆኑም እጅግ በጣም ራስ ወዳዶችና ጥቅመኞች እንዲሁም ሃይማኖት ለበስ ፖለቲከኞች በመሆናቸው እንደ አብርሃሙ ዘመን ዓይነቱ ሎጥ በቀላሉ የሚፋቱአችሁ አይሆኑም :: እራሳቸውን ሎጦች ሳይሆን አብራሞች አድርገው የሚቆጥሩ በመሆናቸውም እናንተን የሎጥ ያክል ቆጥረው በሄዱበት መንገድ ሁሉ ተከትላችኋቸው እንድትሔዱ ፣ የራሳችሁ ምርጫ ቢኖራችሁም እንኳ ከእናንተ ምርጫ ይልቅ የእነርሱ ምርጫ እንደሚበልጥ አምናችሁና ተቀብላችሁ ምርጫቸውንም ምርጫዬ ነው ብላችሁ አጽድቃችሁ እንድትከተሏቸው መጣላታቸውንና መናከሳቸውን ባለማቆም የሚችሉትን ሁሉ ያደርጋሉ :: ይህንንም የሚያደርጉት አንድ ዓይነቶችና አንዱም ከሌላው የማይሻል ፣ የማይለይም ስለሆኑ ነው መጽሐፍቅዱሳችን በመጽሐፈ ምሳሌ 27 ፥ 17 ላይ ብረት ብረትን ይስለዋል ሰውም ባልንጀራውን ይስላል እንደሚል ፣ በእነርሱ ዘንድ አንዱ ከሌላው የተሻለ ሆኖ ባልንጀራውን የሚስል አይደለም :: በአጠቃላይ ሁሉም የማይሳሳሉ ዱልዱሞችና ከእጅ አይሻል ዶማዎች ናቸው :: እንደነዚህ ካሉ ፈጣጦች ፣ በሚሰሩት መልካም ያልሆነ ሥራም ከሚጸጸቱ ይልቅ ዓይኔን ግንባር ያርገው ሲሉ በከተሞች ሁሉ ከሚንቀሳቀሱ አወናባጅ ሎጦች እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ ይጠብቀን ተባረኩልኝ ::
አባ ዮናስ ጌታነህ

Sunday 8 December 2019

ወንድሞች ብሎ ሊጠራቸው አያፍርም

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች ሰላም ለእናንተ ይሁን


እነሆኝ እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ሲል ወንድሞች ብሎ ሊጠራቸው አያፍርም ይላል ( ዕብራውያን 2 ፥ 12 )


ውድ ወገኖቼ ሆይ ይህንን ቃል ልብ ብለን ተመልክተነዋል ? ከኢየሱስ በላይ ሐዋርያ ፣ ከኢየሱስ በላይ ነቢይ ፣ ከኢየሱስ በላይ እረኛ  ሊያውም ትልቅ እረኛና የእረኞችም አለቃ የሆነ ፣ ከኢየሱስ በላይ ወንጌላዊ ፣ ከኢየሱስ በላይ መምህር  ፣ ከኢየሱስ በላይ ሊቀ ካህን ሊያውም በሰማያት ያለፈና በአባቱ ቀኝ የተቀመጠ ትልቅ ሊቀ ካህን ፣ ከኢየሱስ በላይ ንጉሥ ሊያውም የእሾህ አክሊል ብቻ ሳይሆን  የክብርና የምሥጋናን ዘውድ ተጭኖ የታየ ንጉሥ እንደ እርሱ ያለ ማንም የለም :: ይሁን እንጂ ታድያ እንዲህ ያለው ጌታ ነው እንግዲህ ብዙዎቹ ሐዋርያ ፣ ነቢይ ፣ እረኛና የመሣሠሉትን ተብለው ስለተጠሩ ብቻ ወንድሞች ሊሉን ባፈሩበት በዚህ ዘመን ወንድሞች ብሎ ሊጠራን ያላፈረው :: ከዚህ የተነሣ እንግዲህ ዛሬ ዘመናችን ነው ወይንም በሌላኛው አባባል ዘመን መጥቶልናል ሲሉ  በእንዲህ ዓይነት አስተሳሰብ ተጠምደው ላሉ የዘመኑ እረኛ ፣ ነቢይ ፣ ሐዋርያና የመሣሠሉትን ሲባሉ ለተጠሩ ሰዎች እኛም የምንሰጣቸው ምላሽ  ከኢየሱስ ጋር ልትፍቁት የማትችሉት ወንድምነት ውስጥ የገባን ስለሆነ ወንድምነታችን ቀረባችሁ እንጂ አልቀራችሁብንም ነው ::  ደግሞም ክርስቶስ ወንድሞች ብሎ በመጥራት የሰጠን ወንድምነት የማያሳፍርና በመቤዠት ውስጥ የመጣ  የዘላለም  ወንድምነት ስለሆነ እናንተ ደግሞ ይህ ምስጢር ሳይገባችሁ ነውና ሐዋርያ ፣ መጋቢ ፣ ነቢይና የመሳሰሉትን የተባላችሁት ወንድሞች ብለን ስንጠራችሁ የሚያሳፍራችሁ ፣ የምትበሳጩ  ፣ የምታኮርፉና  የምትቆጡ ከዚህ የተነሳም ወንድምነታችንንም ጭምር ልትቀበሉት የምትቸገሩ ብትሆኑም  የተቤዠን ጌታ ግን ወንድሞቼ ብሎ ሊጠራን እኛም ወንድማችን ልንለው አያፍርብንም ፤ ደግሞም  ይሄ ጉዳይ ለእርሱ ደስታው እንጂ ችግሩ አይደለም :: በተለይ በወንጌላውያን ቤተክርስቲያን አንድን ፓስተር ወይንም አንድን ሐዋርያ አንድ አማኝ ድንገት እንኩዋን አፉን አዳልጦት ወንድም እገሌ ቢለው ፓስተሩ ፣ ሐዋርያውም በሉት ሌላው የሚሰማውን ስሜት በተለይ በዚህ ዘመን ሁላችንም እናውቀዋለን :: አንዳንዱማ  ሐዋርያ ፣ ነብይ እና የመሣሠሉትን ተብዬ ተጠርቼ ሳለ ለምን ወንድም ብላችሁ ጠራችሁኝ ? ሲል ከመጠን በላይ ያኮርፍና ላያገኘን ምሎና ተገዝቶ ፣ መንገዱንም አሳብሮ ይሄዳል በየከተማችን ያለ የመጋቢዎች ኩርፍያማ ከዚህም የባሰ ነው :: እግዚአብሔር ያስበን ወገኖቼ :: ከእኛ በፊት የአገልግሎት ቅድሚያና ብልጫም የነበረው ጳውሎስ እኮ ፣ ወንድማችን ጳውሎስ ደግሞ እንደተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ ተብሎ እስካሁን እስከ እኛ ዘመን ድረስ ይነገርለታል 2ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 15 እና 16 :: ታድያ ወንድማችን ጳውሎስ ወንድማችን ስለተባለ ወንድም ተብዬ ተጠርቻለሁና ተዋርጃለሁ ያዙኝ ልቀቁኝ አለ እንዴ አላለም :: ሐዋርያነቱንም ቢሆን እኮ ይገባኛል ብሎ በይገባኛል መንፈስ ያልተቀበለ በመሆኑ ወንድም ተብሎ መጠራቱ ለእርሱ ደስ ያሰኘው እንጂ የቆረቆረው አልሆነም 1ኛ ቆሮንቶስ 15 ፥ 9 – 11 ::  ደግሞም ከሐዋርያነት ይልቅ ወንድምነት እንደሚበልጥ በትክክል የተረዳና የገባው ስለሆነ እንደ እኛ አይደለም :: እኛ ብንሆን ግን እንደዚህ  ጳውሎስ እንደተጠራበት አጠራር ቅንነትንና ወዳጅነትን ተላብሶ  ወንድማችን ሲል በአደባባይ የጠራንን ሁሉ ልናጠፋው እንቅልፍ አይወስደንም :: እንደገናም ቤተክርስቲያንዋም የእኛ እንጂ የእርሱ ስለልሆነች ኮንትራቱ እንዳለቀ ሠራተኛ ከቤተክርስቲያን ምክንያት ፈጥረን አስፈንጥረን እናባርረዋለን :: ጌታ ዓይኖቻችንን ይክፈትልን ይህንን ያክል በአጭሩ ካልኩ እንግዲህ ይበቃኛል :: በዚህ ምንባብ ተጠቀሙ ተባረኩ ::


…..ጳውሎስም፦ ወንድሞች ሆይ፥ ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው፤ በሕዝብህ አለቃ ላይ ክፉ ቃል አትናገር ተብሎ ተጽፎአልና አላቸው
የሐዋርያት ሥራ 23 : 1 – 5


አባ ዮናስ ጌታነህ

Friday 6 December 2019

የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ከቪዲዮው መልዕክት በተጨማሪ ይህንን ጽሑፍ በማስተዋል እንድታነቡ እጋብዛለሁ ተባረኩልኝ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ እግዚአብሔርን እንደምትወድ ከጌታ ቤት በአንድም በሌላም መንገድ የከዱና የኮበለሉ ሰዎች እንደዚሁ አንድ ቀን ተመልሰው እግዚአብሔርን ይወዳሉ :: ይህም የሚሆነው በእኛ ቀን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቀን ነው :: ይህን ስል ግን እያንዳንዳችን ክርስቲያኖች ማድረግ የሚገባንን የበኩላችንን ነገር ሁሉ አናድርግ አንምከር አናስተምር አንገስጽ ማለቴ አይደለም ፣ ነገር ግን ያ ሁሉ እንዳለ ሆኖ እግዚአብሔር ደግሞ ብቻውን በሚያደርገው ነገር ከዳተኛይቱ ይሁዳ በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሰች ከመንግሥቱም ሆነ ከቤቱ የጠፉና የኮበለሉ ሰዎች ደግሞ እንዲሁ በእግዚአብሔር ክህሎት ወደ ቤቱ ይመለሳሉ :: ለዚህም ነው ጌታ እግዚአብሔር በትንቢተ ኤርምያስ 31 ፥ 22 ፤ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 14 - 22 ላይ ከዳተኛ ልጆች ሆይ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ ፣ በእውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ ያለው :: እንደገናም እኔም የተመረጠችውን ምድር የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቊጠርሽ አልሁ :: አባቴ ብለሽ የምትጠሪኝ እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር :: የእስራኤል ቤት ሆይ ለባልዋ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት ስታታልሉኝ ኖራችኋል ይላል እግዚአብሔር በማለት ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኤርምያስ ለከዳተኛዋ ይሁዳም ሆነ ለእስራኤል ቤት ተናገረ :: ታድያ ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኩል ማምጣቱ እስራኤል ዘወትር አምላኩዋ ያደረገላትን ሁሉ ማስታወስ ነበረባት :: በእርሱ ብቻ በመታመን እርሱንም ማምለክ ነበረባት ፣ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ረስታዋለች ከልብዋም አውጥታ ጥላዋለች ከዚህ የተነሳ በትንቢተ ኤርምያስ 2 ፥ 32 ላይ ጌታ እግዚአብሔር በውኑ ለእስራኤል ምድረበዳ ወይስ የጨለመች ምድር ሆንሁበትን ? ሕዝቤስ ስለምን እኛ ፈርጥጠናል ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ አንመለስም ይላል ? በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን ? ሕዝቤ ግን የማይቆጠር ወራት ረስቶኛል በማለት ሲናገር እንመለከታለን :: እንግዲህ ሕዝቤ ተብላ ወደ አንተ አንመለስም ስትል የማይቆጠር ወራት አምላኳን የረሳች እስራኤል ናት በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር ተመልሳ በዚሁ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 21 መሠረት እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት መንገዳቸውን አጣመዋልና የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኮረብታዎች ተሰማ የሚለን ::

ይህንን መልዕክት በተለቀቀው ቪዲዮ የሰማችሁም ሆነ ለማንበብ ፈቃደኛ ሆናችሁ መልዕክቱን የምታነቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥምና ለጠፉ ሰዎች በፍቅር ሆናችሁ የመናገርም ሆነ የመመስከር ፋይላችሁን አትዝጉ ደግሞም ፈራጁ እያለ እናንተንም ሆነ ሁላችንን ስላልተቀበሉን ፣ ስላልተቀበሏችሁ ፣ ስላላስተናገዱን ስላላስተናገዷችሁ መጸለይ አለበለዚያም እነርሱን በግል ሄዶ ማነጋገርና ማመካከር መጨረስ የሚገባንንም እዚያው በግል መጨረስ ነው እንጂ ከብስጭትም ሆነ ከመመረር የተነሳ እንዲሁ መድረኩ ስለተገኘ ብቻ እነዚሁኑ ሰዎች በየሶሻል ሚዲያው ገበናቸውን አውጥተን የውይይት አጀንዳ ባናድርጋቸው ፣ ደግሞም እንደ ጳውሎስና በርናባስም እስከ መከፋፋት ደርሰን ባንለያይባቸው እንደገናም ነገ የሚሆነውን አናውቅምና ከዚህም ሌላ ከጌታ ዘንድ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም እንባላለንና በችኮላ ተናደን የፍርድን ቃል በላያቸው ባንናገር የተሻለ ነው የሚሆነው :: እነዚህን ጥቅሶች በማስተዋል አንብቧቸው የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 51 - 56 ፤ የሐዋርያት ሥራ 15 ፥ 36 - 41 ፤ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥ 11 ፤ ፊልሞና ቊጥር 8 - 25 :: ዛሬ ላይ ሁላችንም ማለት ይቻላል ብለን ብለን ተስፋ የቆረጥንባቸውን ሰዎች በነገው ሕይወታቸው እግዚአብሔር ወደ ቤቱ በምን ዓይነት መንገድ ጠርቶና መልሶ እንደሚጠቀምባቸው ከአንዳንዶች በቀር አብዛኞቻችን ላናውቅ እንችላለን :: ይህ ሲባል ግን የተግሳጽም ሆነ የዘለፋ እንዲሁም የምክር መልዕክቶችን ጌታ እንደሰጠን መጠን አንናገር አናስተላልፍ እያልኩ አለመሆኔን በግልጽ ልትረዱልኝ ይገባል :: እንደውም መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር ነው የሚለን ትንቢተ ኢሳይያስ 58 ፥ 1 እንመልከት :: ከዚህ በመቀጠል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ የእስራኤልም ሆነ አሁን ላይ ያለ የሐዲስ ኪዳን ሕዝብን አሳዛኝ ጩኸትና የመመለስ ልቅሶ እንዲህ በማለት አስደናቂ በሆነው የመዝሙር ስንኞቹ እና ዜማው ገልጾታልና እርሱን እጋብዛችኋለሁ ተከታተሉ ::

አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው

በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው

ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት

ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት

ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት

በመራራ ፡ ጩኸት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት

መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል

ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል

ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም

ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)


ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አሳፍሮ

በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ

ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን

ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)

አባ ዮናስ ጌታነህ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ


የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ከቪዲዮው መልዕክት በተጨማሪ ይህንን ጽሑፍ በማስተዋል እንድታነቡ እጋብዛለሁ ተባረኩልኝ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ እግዚአብሔርን እንደምትወድ ከጌታ ቤት በአንድም በሌላም መንገድ የከዱና የኮበለሉ ሰዎች እንደዚሁ አንድ ቀን ተመልሰው እግዚአብሔርን ይወዳሉ :: ይህም የሚሆነው በእኛ ቀን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቀን ነው :: ይህን ስል ግን እያንዳንዳችን ክርስቲያኖች ማድረግ የሚገባንን የበኩላችንን ነገር ሁሉ አናድርግ አንምከር አናስተምር አንገስጽ ማለቴ አይደለም ፣ ነገር ግን ያ ሁሉ እንዳለ ሆኖ እግዚአብሔር ደግሞ ብቻውን በሚያደርገው ነገር ከዳተኛይቱ ይሁዳ በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሰች ከመንግሥቱም ሆነ ከቤቱ የጠፉና የኮበለሉ ሰዎች ደግሞ እንዲሁ በእግዚአብሔር ክህሎት ወደ ቤቱ ይመለሳሉ :: ለዚህም ነው ጌታ እግዚአብሔር በትንቢተ ኤርምያስ 31 ፥ 22 ፤ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 14 - 22 ላይ ከዳተኛ ልጆች ሆይ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ ፣ በእውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ ያለው :: እንደገናም እኔም የተመረጠችውን ምድር የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቊጠርሽ አልሁ :: አባቴ ብለሽ የምትጠሪኝ እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር :: የእስራኤል ቤት ሆይ ለባልዋ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት ስታታልሉኝ ኖራችኋል ይላል እግዚአብሔር በማለት ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኤርምያስ ለከዳተኛዋ ይሁዳም ሆነ ለእስራኤል ቤት ተናገረ :: ታድያ ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኩል ማምጣቱ እስራኤል ዘወትር አምላኩዋ ያደረገላትን ሁሉ ማስታወስ ነበረባት :: በእርሱ ብቻ በመታመን እርሱንም ማምለክ ነበረባት ፣ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ረስታዋለች ከልብዋም አውጥታ ጥላዋለች ከዚህ የተነሳ በትንቢተ ኤርምያስ 2 ፥ 32 ላይ ጌታ እግዚአብሔር በውኑ ለእስራኤል ምድረበዳ ወይስ የጨለመች ምድር ሆንሁበትን ? ሕዝቤስ ስለምን እኛ ፈርጥጠናል ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ አንመለስም ይላል ? በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን ? ሕዝቤ ግን የማይቆጠር ወራት ረስቶኛል በማለት ሲናገር እንመለከታለን :: እንግዲህ ሕዝቤ ተብላ ወደ አንተ አንመለስም ስትል የማይቆጠር ወራት አምላኳን የረሳች እስራኤል ናት በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር ተመልሳ በዚሁ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 21 መሠረት እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት መንገዳቸውን አጣመዋልና የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኮረብታዎች ተሰማ የሚለን ::

ይህንን መልዕክት በተለቀቀው ቪዲዮ የሰማችሁም ሆነ ለማንበብ ፈቃደኛ ሆናችሁ መልዕክቱን የምታነቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥምና ለጠፉ ሰዎች በፍቅር ሆናችሁ የመናገርም ሆነ የመመስከር ፋይላችሁን አትዝጉ ደግሞም ፈራጁ እያለ እናንተንም ሆነ ሁላችንን ስላልተቀበሉን ፣ ስላልተቀበሏችሁ ፣ ስላላስተናገዱን ስላላስተናገዷችሁ መጸለይ አለበለዚያም እነርሱን በግል ሄዶ ማነጋገርና ማመካከር መጨረስ የሚገባንንም እዚያው በግል መጨረስ ነው እንጂ ከብስጭትም ሆነ ከመመረር የተነሳ እንዲሁ መድረኩ ስለተገኘ ብቻ እነዚሁኑ ሰዎች በየሶሻል ሚዲያው ገበናቸውን አውጥተን የውይይት አጀንዳ ባናድርጋቸው ፣ ደግሞም እንደ ጳውሎስና በርናባስም እስከ መከፋፋት ደርሰን ባንለያይባቸው እንደገናም ነገ የሚሆነውን አናውቅምና ከዚህም ሌላ ከጌታ ዘንድ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም እንባላለንና በችኮላ ተናደን የፍርድን ቃል በላያቸው ባንናገር የተሻለ ነው የሚሆነው :: እነዚህን ጥቅሶች በማስተዋል አንብቧቸው የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 51 - 56 ፤ የሐዋርያት ሥራ 15 ፥ 36 - 41 ፤ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥ 11 ፤ ፊልሞና ቊጥር 8 - 25 :: ዛሬ ላይ ሁላችንም ማለት ይቻላል ብለን ብለን ተስፋ የቆረጥንባቸውን ሰዎች በነገው ሕይወታቸው እግዚአብሔር ወደ ቤቱ በምን ዓይነት መንገድ ጠርቶና መልሶ እንደሚጠቀምባቸው ከአንዳንዶች በቀር አብዛኞቻችን ላናውቅ እንችላለን :: ይህ ሲባል ግን የተግሳጽም ሆነ የዘለፋ እንዲሁም የምክር መልዕክቶችን ጌታ እንደሰጠን መጠን አንናገር አናስተላልፍ እያልኩ አለመሆኔን በግልጽ ልትረዱልኝ ይገባል :: እንደውም መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር ነው የሚለን ትንቢተ ኢሳይያስ 58 ፥ 1 እንመልከት :: ከዚህ በመቀጠል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ የእስራኤልም ሆነ አሁን ላይ ያለ የሐዲስ ኪዳን ሕዝብን አሳዛኝ ጩኸትና የመመለስ ልቅሶ እንዲህ በማለት አስደናቂ በሆነው የመዝሙር ስንኞቹ እና ዜማው ገልጾታልና እርሱን እጋብዛችኋለሁ ተከታተሉ ::

አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው

በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው

ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት

ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት

ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት

በመራራ ፡ ጩኸት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት

መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል

ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል

ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም

ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)


ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አሳፍሮ

በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ

ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን

ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)

አባ ዮናስ ጌታነህ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ


የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ከቪዲዮው መልዕክት በተጨማሪ ይህንን ጽሑፍ በማስተዋል እንድታነቡ እጋብዛለሁ ተባረኩልኝ
ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ እግዚአብሔርን እንደምትወድ ከጌታ ቤት በአንድም በሌላም መንገድ የከዱና የኮበለሉ ሰዎች እንደዚሁ አንድ ቀን ተመልሰው እግዚአብሔርን ይወዳሉ :: ይህም የሚሆነው በእኛ ቀን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቀን ነው :: ይህን ስል ግን እያንዳንዳችን ክርስቲያኖች ማድረግ የሚገባንን የበኩላችንን ነገር ሁሉ አናድርግ አንምከር አናስተምር አንገስጽ ማለቴ አይደለም ፣ ነገር ግን ያ ሁሉ እንዳለ ሆኖ እግዚአብሔር ደግሞ ብቻውን በሚያደርገው ነገር ከዳተኛይቱ ይሁዳ በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሰች ከመንግሥቱም ሆነ ከቤቱ የጠፉና የኮበለሉ ሰዎች ደግሞ እንዲሁ በእግዚአብሔር ክህሎት ወደ ቤቱ ይመለሳሉ :: ለዚህም ነው ጌታ እግዚአብሔር በትንቢተ ኤርምያስ 31 ፥ 22 ፤ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 14 – 22 ላይ ከዳተኛ ልጆች ሆይ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ ፣ በእውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ ያለው :: እንደገናም እኔም የተመረጠችውን ምድር የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቊጠርሽ አልሁ :: አባቴ ብለሽ የምትጠሪኝ እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር :: የእስራኤል ቤት ሆይ ለባልዋ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት ስታታልሉኝ ኖራችኋል ይላል እግዚአብሔር በማለት ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኤርምያስ ለከዳተኛዋ ይሁዳም ሆነ ለእስራኤል ቤት ተናገረ :: ታድያ ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኩል ማምጣቱ እስራኤል ዘወትር አምላኩዋ ያደረገላትን ሁሉ ማስታወስ ነበረባት :: በእርሱ ብቻ በመታመን እርሱንም ማምለክ ነበረባት ፣ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ረስታዋለች ከልብዋም አውጥታ ጥላዋለች ከዚህ የተነሳ በትንቢተ ኤርምያስ 2 ፥ 32 ላይ ጌታ እግዚአብሔር በውኑ ለእስራኤል ምድረበዳ ወይስ የጨለመች ምድር ሆንሁበትን ? ሕዝቤስ ስለምን እኛ ፈርጥጠናል ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ አንመለስም ይላል ? በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን ? ሕዝቤ ግን የማይቆጠር ወራት ረስቶኛል በማለት ሲናገር እንመለከታለን :: እንግዲህ ሕዝቤ ተብላ ወደ አንተ አንመለስም ስትል የማይቆጠር ወራት አምላኳን የረሳች እስራኤል ናት በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር ተመልሳ በዚሁ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 21 መሠረት እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት መንገዳቸውን አጣመዋልና የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኮረብታዎች ተሰማ የሚለን ::
ይህንን መልዕክት በተለቀቀው ቪዲዮ የሰማችሁም ሆነ ለማንበብ ፈቃደኛ ሆናችሁ መልዕክቱን የምታነቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥምና ለጠፉ ሰዎች በፍቅር ሆናችሁ የመናገርም ሆነ የመመስከር ፋይላችሁን አትዝጉ ደግሞም ፈራጁ እያለ እናንተንም ሆነ ሁላችንን ስላልተቀበሉን ፣ ስላልተቀበሏችሁ ፣ ስላላስተናገዱን ስላላስተናገዷችሁ መጸለይ አለበለዚያም እነርሱን በግል ሄዶ ማነጋገርና ማመካከር መጨረስ የሚገባንንም እዚያው በግል መጨረስ ነው እንጂ ከብስጭትም ሆነ ከመመረር የተነሳ እንዲሁ መድረኩ ስለተገኘ ብቻ እነዚሁኑ ሰዎች በየሶሻል ሚዲያው ገበናቸውን አውጥተን የውይይት አጀንዳ ባናድርጋቸው ፣ ደግሞም እንደ ጳውሎስና በርናባስም እስከ መከፋፋት ደርሰን ባንለያይባቸው እንደገናም ነገ የሚሆነውን አናውቅምና ከዚህም ሌላ ከጌታ ዘንድ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም እንባላለንና በችኮላ ተናደን የፍርድን ቃል በላያቸው ባንናገር የተሻለ ነው የሚሆነው :: እነዚህን ጥቅሶች በማስተዋል አንብቧቸው የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 51 – 56 ፤ የሐዋርያት ሥራ 15 ፥ 36 – 41 ፤ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥ 11 ፤ ፊልሞና ቊጥር 8 – 25 :: ዛሬ ላይ ሁላችንም ማለት ይቻላል ብለን ብለን ተስፋ የቆረጥንባቸውን ሰዎች በነገው ሕይወታቸው እግዚአብሔር ወደ ቤቱ በምን ዓይነት መንገድ ጠርቶና መልሶ እንደሚጠቀምባቸው ከአንዳንዶች በቀር አብዛኞቻችን ላናውቅ እንችላለን :: ይህ ሲባል ግን የተግሳጽም ሆነ የዘለፋ እንዲሁም የምክር መልዕክቶችን ጌታ እንደሰጠን መጠን አንናገር አናስተላልፍ እያልኩ አለመሆኔን በግልጽ ልትረዱልኝ ይገባል :: እንደውም መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር ነው የሚለን ትንቢተ ኢሳይያስ 58 ፥ 1 እንመልከት :: ከዚህ በመቀጠል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ የእስራኤልም ሆነ አሁን ላይ ያለ የሐዲስ ኪዳን ሕዝብን አሳዛኝ ጩኸትና የመመለስ ልቅሶ እንዲህ በማለት አስደናቂ በሆነው የመዝሙር ስንኞቹ እና ዜማው ገልጾታልና እርሱን እጋብዛችኋለሁ ተከታተሉ ::
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው
በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው
ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት
ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት
ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት
በመራራ ፡ ጩኸት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት
መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል
ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል
ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም
ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አሳፍሮ
በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ
ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን
ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
አባ ዮናስ ጌታነህ

Friday 22 November 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ ወደ ሥራችን እንመለስ ( መጽሐፈ ነህምያ 4 ፥ 15 ) . ___ የመልዕክት ርዕስ ፦ ወደ ሥራችን እንመለስ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ሕዝቦች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን :: ይህ የተለቀቀው የቪዲዮ መልዕክት ሐዋርያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን የወንጌላውያኑን ወይንም የፕሮቴስታንቱን ቤተክርስቲያንም ጭምር የሚመለከት ጉዳይ በመሆኑ ሁላችሁም በማስተዋል ሰምታችሁ እንድትጠቀሙ እጋብዛለሁ :: መልዕክቱ በቪዲዮው ላይ በግልጥ ስለተቀመጠ ብዙ ማብራራት አይጠበቅብኝም :: በአጭሩ ለማስቀመጥ ግን ይህንን ቃል የተጠቀመው ነህምያ ሲሆን በመጽሐፈ ነህምያ 4 ፥ 15 ላይ ጠላቶቻችንም ይህ ነገር እንደ ደረሰልን እግዚአብሔርም ምክራቸውን ከንቱ እንዳደረገው ሰሙ እኛም ሁላችን ወደ ቅጥሩ እያንዳንዳችንም ወደ ሥራችን ተመለስን በማለት ተናገረ :: በዚህ ውስጥ ታድያ ጌታ እግዚአብሔር የተስተጓጐለውን የራሱን ሥራ ለአስተጓጓዮች ነግሮ ሳይሆን የሚመልሰን የአስተጓጓዮችን ምክር አፍርሶና ከንቱ ምክራቸውም እንደፈረሰባቸው ለራሳቸው ሳይቀር ነግሮና አሳውቆ ነው የሚመልሰን :: እኛም ታድያ ይህን አውቀን እግዚአብሔር እስኪመልሰን መጠበቅ የለብንም :: እኛው ራሳችን ወደ ሥራው ተመለሰን መመለሳችንንም እንደ ነህምያ በሁሉም ፊት ማወጅ እና ማሳወቅ አለብን :: ነህምያ የነገረንም ሆነ ያሳየን ቁምነገር እንግዲህ ይህንን ይመስል ነበር :: ጠላት ሁልጊዜ የማይተኛ ሆኖ የእግዚአብሔርን ሥራ ለማስተጓጐል የመከረና እየመከረም ያለ ቢሆንም ምክሩ ግን ትላንት ፈርሶ የሚቀር አይሆንም ፣ ዛሬም እስከ ለዘላለምም እየፈረሰበት ይኖራል :: ይሁን እንጂ ታድያ ይሄ ጊዜ ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜው ስለሆነ እኛም የእግዚአብሔር አገልጋዮችና ቅዱሳን ሕዝቦች ይህን እውነት አውቀን ቶሎ ፈጠን በማለት እግዚአብሔር ወደ ሰጠን ሥራ መመለስ ይሁንልን እላለሁ :: ለበለጠ መረጃ ይህንን ቪዲዮ እንድትሠሙት እጋብዛለሁ :: መልዕክቱንም ሌሎች ሼር ማድረግ አትርሱ ተባረኩ :: ወንድማችሁ አባ ዮናስ ነኝ

Saturday 16 November 2019


የሥልጣን ሽኩቻ መንስዔዎች ምን ምን ናቸው 


የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን 

 ውድ ወገኖቼ ሆይ የሥልጣን ሽኩቻ መንስዔዎች ምን ምን ናቸው በሚል ርዕስ ጥቂት ቆይታ ከእናንተ ከአንባቢዎቼ ጋር አደርጋለሁና ተከታተሉኝ :: ሰዎች በቤተክርስቲያን በመሪነትና በአገልግሎት ሥልጣን ለምን ይሻኮታሉ ? ሀገርን ወደ መምራትና ወደ ማስተዳደር ጉዳይ አልፈንም ስንሄድ ይሄ የስልጣን ሽኩቻ ብሶና ተባብሶ ሰዎችን በብሔር በጎሳና በቋንቋ እስከመከፋፈል ያዳረሰና ያጨራረሰ    ደምንም ያቃባ ብርቱ መዘዝ ሆኖ አግኝተነዋል :: ታድያ ሰዎች በዚህ የሥልጣን ሽኩቻ እንዲጠመዱና እዚህ ደረጃም ላይ እንዲደርሱ የሚያደርጋቸው ምንድነው ስንል ከጦርነት መልስ የመጣ የተንበሸበሸ ዕረፍት ነው የሚል ሙሉ የሆነ መልስ እናገኛለን :: ሰዎች ዕረፍት ሲበዛላቸው ወይንም ወደ ዕረፍት ሲመለሱ የሚሠሩት ነገር ስለሌላቸው ሥራ ፈት ይሆናሉ :: አንድ ሰው ሲናገር እንዲህ አለ ሥራ የፈታ አዕምሮ የሰይጣን ወርክ ሾፕ ነው በማለት ተናገረ :: ታድያ ሰዎችም ሥራ በሚፈቱ ጊዜ እንዲሁ የሰይጣን ወርክ ሾፕ ይሆናሉ :: ጊዜያቸውንም እንዲሁ በሃሜትና በአሉባልታ የሚያሳልፉ ይሆኑና  አንዱን ሲያነሱ ሌላውን ሲጥሉ ፣ ሲቀዱና ሲሰፉ ይውላሉ :: ወደገዛ ወንድሞቻቸውም ተመልሰው በወንድሞቻቸው ላይ በአገልግሎት በሥራ በእውቀት በደሞዝ እርከንና በመሣሠሉት  ቀደመን ያሉትን ሁሉ ሰው ብቻ ከንቱ በሆነ ቅንዓት ይጠሉትና እንዲሁ ሲያሳድዱት ስሙንም ሲያጠፉት ይገኛሉ :: ለዚህም ነው መጽሐፍቅዱሳችን በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ እርስ በእርሳችን እየተነሳሳንና እየተቀናናን በከንቱ አንመካ ሲል የመከረን  ገላትያ 5 25 እና 26   እንመልከት ::

ወገኖቼ ሆይ የሥልጣን ሽኩቻን የወለደው እንዳልኳችሁ የተንበሸበሸ ዕረፍት ሲሆን ፣ ይሄ ከልክ በላይ የሆነ የተንበሸበሸው ዕረፍት ደግሞ ሰዎችን ሥራ ፈት ከማድረጉ ባሻገር  እያንዳንዱ በገዛ ወንድሙ ላይ ጠላት ሆኖና በጠላትነትም ተነስቶ ይህንኑ ወንድሙን እንዲገድል ሆኗል ፣ እግዚአብሔር ይቅር ይበለን :: የሚደንቀው ደግሞ ይሄ ሁኔታ በደጅ ወይም በውጪ ሳይሆን በእግዚአብሔር ቤት መጀመሩ ነው :: እግዚአብሔር ቤት ያለው ግድያ የክላሽ ድምጽና የጠመንጃ ተኩስ የማይሰማበት ከባዱ ግድያ ሲሆን ፣ በሀገር ላይ እየተሰማ ያለው ግድያ ግን ጩቤውን ፣ ስለቱን ፣ ካራውንና ድንጋዩን ሁሉ ያስተባበረ ፣ በመሣርያም ጭምር የሆነ ነፍስ የማጥፋት ግድያ ነው:: ይሁን እንጂ ታድያ ሁለቱም ግድያዎች በእግዚአብሔር ዘንድ በእኩል ዓይን የሚታዩ በመሆናቸው  ልዩነት የላቸውም :: ገዳዮቹንም በእግዚአብሔር ዙፋን ፍርድ በነፍሰ ገዳይነት  የሚያስጠይቃቸው ይሆናል :: 

የተወደዳችሁ ወገኖች ለዚህ እውነታዬ ብርቱ ማስረጃ ለመስጠት ወደ ኢትዮጵያ ታሪክ ሄጄ አንድ ክፍል ለማንሳት እገደዳለሁ :: እርሱም ምንድነው ብትሉኝ ከ900 —- 1200 ( ከዘጠኝ መቶ እስከ አንድ ሺህ ሁለት መቶ ) ዓመት ባለ ክፍለ ዘመን የተነሳች ዮዲት የተባለች አይሁዳዊት ሴት ኢትዮጵያን ለአርባ ዓመት ስትገዛ በትልቅ ጭካኔ ነበር የገዛችው :: የኦርቶዶክስን ገዳማትና አድባራትን አቃጥላለች የሀገርን ቅርስና ታሪክ አውድማለች ፣ ሰዎችን አርዳለች ፣ ገድላለች ፣ አጥፍታለች :: ጭካኔዋና የአገዛዝ ቀንበርዋም ከልክ ያለፈ ፣ አረመኔነትንም ጭምር የተላበሰ ነበር :: በዚህ ሁኔታ ውስጥ ታድያ  በሀገር ደረጃ ያሉ ሰዎችም ይሁኑ ከቤተክርስቲያን ሰዎች መካከል ከለቅሶ ፣ ከዋይታና እግዚአብሔርንም ከመማጸን ውጪ አንድም ትንፍሽ ያለ ሰው አልነበረም :: ዘማሪ ተስፋዬ ጫላ እንደማያልፍ የለም ሁሉ አለፈና የሰቆቃ ዘመን በደስታ ተተካ ብሎ እንደዘመረው ክፉው የ40 ዓመቱ የዮዲት ጉዲት የጭካኔ አገዛዝ ካከተመ ፣ በምትኩም ለሀገርም ሆነ ለቤተክርስቲያን የነጻነትና የጸጥታ  ዘመን ከመጣ በኋላ ቤተክርስቲያንም ሆነ ሀገር ይህንን እግዚአብሔር ያመጣውን ዕረፍት በጎ ለሆነው ሥራ  ሲጠቀሙበት አልተስተዋለም :: ይልቁንም  ሁለቱም ወደየግል ጉዳዮቻቸው ተመልሰው የእርስ በእርስ ግጭትና ጠብን ነው የጀመሩት  :: ሰላምን ሻ ተከተላትም እንደሚል ቃሉ የመጣውን ሰላም እንደ ትልቅ ዕድል ቆጥረው ይህንኑ ሰላም የፈለጉም ሆነ የሻቱም አልነበሩም ፣ አልተከተሉትምም 1ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 10 - 12  :: በዚያን ጊዜ የነበረ  ሥልጣን ከነገደ ሳባ ወደ ነገደ ዛጉዬ ስለተመለሰ ይሄ ሁኔታ ያስከፋቸው የሳባውያን ነገድ በዛጉዬ መንግሥት ላይ ትልቅ ሽኩቻ ፈጠሩ :: በወቅቱ ሆኖም ተደርጎም የማይታወቅ ሽኩቻ በእነዚህ ጎሳዎች መካከል ተካሄደ :: በዚህ ውስጥ ታድያ ቤተክርስቲያን የማስታረቅ ቃል በውስጥዋ ከመኖሩ የተነሳ ሥልጣንን አስመልክቶ በነገዶች መካከል በተደረገው ግጭት የአስታራቂነቱን ቅድሚያ በመውሰድና ሕዝቦችንም ማለትም የሳባንና የዛጉዬ ነገድ ወደ አንድነት በማምጣት እነዚሁኑ ሰዎች እንደ አንድ ሕዝብ አድርጋ ማስታረቅም ሆነ ማስማማት ሲገባት ከእነርሱ ይልቅ እርስዋ ብሳና ጎራም ለይታ  የጥቅሙም ሆነ የግጭቱ ተባባሪና ፊት መር በመሆንዋ  ምክንያት ፍቅር ጠፍቶ አምልኮተ እግዚአብሔር ተዘንግቶ ይህቺው እዚያ ዘመን ላይ የነበረች ቤተክርስቲያን የዘርና የፖለቲካ ዓላማ ማስፈጸምያ ወደ መሆን አዘመመች :: ከላይ ባየነው ተጽዕኖም አማካኝነት በ1300 ( በአንድ ሺህ ሦስት መቶ ዓመት ) በአቡነ ተክለ ሃይማኖት የፖለቲካና የሃይማኖት መሪ መሆን ጀምሮ እስከ አፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ድረስ ( 1966 ዓመተ ምሕረት ) ቤተ መንግሥት ከቤተ ክህነት ጋር ተጣመረ ፣ ነገሥታቱም ሁሉም ባይባሉም የራሳቸው ስምና ዝና እንዲጻፍላቸው እንዲመሰገኑ ምስላቸውም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲሰቀልና ማዕጠንት እንዲታጠን ለብቻቸው ማስቀደሻ ሥፍራ እንዲዘጋጅላቸው ፣ ሲሞቱም ቃልኪዳን ተቀብለዋል በሚል ጻድቃን ተብለው በዕለተ ሞታቸው እንዲዘከርላቸው በስማቸው ታቦት እንዲቀረጽላቸው አጥንታቸውም ሳይቀር ሕዝቡን እንዲገዛ አስምለውና አስገዝተው የሄዱ በመሆናቸው ቤተክርስቲያን ዛሬ ላለችበት ትልቅ ውድቀት ምክንያት ሆኖአል :: ሌላው ቀርቶ የእነርሱ ካባና መቋምያ ፣ መቀመጫ መንበሮቻቸው ሳይቀር ሻማ እየተለኮሰለትና እየታጠነ ፣ መልክአ ውዳሴ ተደርሶላቸው ማሕሌት የሚቆምላቸው ጊዜያት ነበረ :: ታድያ በዚህ ሁኔታ በ14ኛው ክፍለ ዘመን የተነሳው ንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብ ከምንኩስናው ዓለም  ወደ ቤተመንግሥት በማናለብኝነት ዘው ብሎ ገብቶ ራሱን በማንገሥ እና በትረ መንግሥቱንም በመጨበጥ  በወንጌል እውነት ተዋጅተው  እየሰበኩ ያሉትን ወገኖች ለንጉሥ አልሰገዱም በማለት የሞት ጭፍጨፋና ግድያን ያካሄደባቸው ከዚህ የተነሳ ነው :: እነርሱም ሲመልሱለት ራሳችንን ለሥሉስ ቅዱስ አስገዝተናልና በሥላሴ ላይ አራተኛ አካል አንጨምርም ፣ ለዛም ለአራተኛው አካል አንሰግድም በማለታቸው ምክንያት አስረውና አርባ ጅራፍ እያንዳንዳቸውን በመግረፍ በጉድጉዋድ ውስጥ አንገታቸውን ብቻ ብቅ በማድረግ የጋማ ከብት ነድተውባቸዋል :: ታድያ ከዚያን ጊዜ የጀመረው ክፋት ነው ዛሬ ድረስ ቀጥሎ ቤተ ክርስቲያንዋ ወደ ጥንተ መሠረትዋ ተመልሳ ወንጌልን ብቻ እንድትሠብክ በሚታገሉላት  አገልጋዮች ላይ አሁን ድረስ ትልቅ የሆነ ስደትና ሰልፍ ያለው :: በዚህ ውስጥ እንግዲህ ወንጌልን መመከቻ አድርገው ሥልጣን ለምኔ ጥቅም ለምኔ ያሉ አገልጋዮች ሲሰደዱ ሆዳቸው አምላካቸውና ክብራቸው በነውራቸው የሆኑ አገልጋዮች ደግሞ  በዚያው መጠን አሳዳጆች ሆነው ይኸው አሁን ያለንበት ደረጃ  ላይ ደርሰናል :: እነዚህ ሆዳቸው አምላካቸው የሆኑ አገልጋዮች ደግሞ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ብቻ የሚገኙ ሳይሆኑ በወንጌላውያን ቤተክርስቲያንም ጭምር ሳይቀር የአገልግሎት ሥልጣንና ስም ለብሰው ከዚህ በከፋ ሁኔታ እያሳደዱ ያሉ ሰዎችም በብዛት ይገኙበታል :: 

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ክፋቱ እየጨመረ ሄዶ የአባ እስጢፋኖስ ደቀመዛሙርት እጃቸውና እግራቸው እየተቆራረጠ ፣ አፍንጫቸውም እየተፎነነ ወይንም እየተቆረጠ እንዲሞቱ ቢደረግም እነርሱ ግን ይሄ ሁሉ ሳይበግራቸው ለእውነት ወንጌል ቆመውና መከራውንም ታግሰው ያስተማሩ ነበሩ ይሁን እንጂ በዚያ ዘመን እንደገናም ይባስ ተብሎ በአፄ በዕደ ማርያም በአፄ እስክንድር በአፄ ዘመደ ጽዮን ፣ በአፄ ናኦድ በአፄ ልብነ ድንግልና በመሳሰሉት እየታደኑ ተደበደቡ ተገደሉ ከቅጽረ ቤተክርስቲያንም ሳይቀር እንዲባረሩ ተደረጉ :: ዛሬም ታድያ ሥልጣንን መውደድ የሚያመጣው መዘዝ ከዚህ ሁለት እጥፍ የጨመረ ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም :: ሥልጣናቸውን የሚወዱ ሰዎች አሁንም በዚህ ጉዳይ ምንም ከማድረግ ወደ ኋላ አይመለሱም :: ይህ ነው እንግዲህ ቤተክርስቲያንንም ሆነ ሀገርን ወደ ኋላ ያስቀረና ወደ ከፋ ነገርም የወሰደ  :: ራሳቸውን የወደዱ ሰዎች በሀገር ደረጃም ይሁን በቤተክርስቲያን ዕርቅን የማይሰሙ ጨካኞች ፣ ከዳተኞች ፣ ችኩሎች ፣ በትዕቢት የተነፉ ናቸው 2ኛ ጢሞቴዎስ ምዕራፍ 3 ን በሙሉ  እንመልከት ::

መልዕክቴን ስጠቀልል በሀገር ጉዳይ መረጋጋትና ሰላም እንዲመጣ በቤተክርስቲያንም እንዲሁ እውነተኛው የጽድቅ ወንጌል ተሰብኮ ለሕዝብ መዳን እንዲሆንና ጌታም እንዲከብር ራስ ወዳድም ሆነ ራስ ተኮር የሆኑ ሰዎች ከነገሮቻቸውና ከየግል ጥቅሞቻቸው በፍጥነት ተመልሰው ሕዝባዊና ሀገራዊ አስተሳሰብ ሊይዙ ይገባል እላለሁ :: በቤተክርስቲያንም ደረጃ ያሉ ሰዎች ደግሞ በእግዚአብሔር ሥራ ውስጥ ራሳቸውን ደብቀው የግል ጥቅማቸውን ለማስከበር ሲሉ  እንደ አንድ ትንንሽ መንግሥት ራሳቸውን ሊቆጥሩና ሊያስቆጥሩ ቢወዱም ከዚህ  ይልቅ የሚመጣውን የክርስቶስን መንግሥት በጽድቅ ሊሰብኩ ራሳቸውን ቢሰጡ የምንፈልገው ዘላለማዊ የጌታ ሰላም ይመጣል :: እንደገናም ይህንን የጌታ ሰላም በማምጣትና   ወደ ሰዎችም ሁሉ በማድረስ  ቤተክርስቲያን የመጀመርያዋ ትሆናለች :: ጌታ እግዚአብሔር ከራሳችን ነገር አውጥቶ ለዚህ እውነት ያቁመን ተባረኩ !! 

አባ ዮናስ ጌታነህ 

ከስምዓ ጽድቅ ሐዋርያዊ ኦርቶዶክስ ተሃድሶ