Friday 22 November 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ ወደ ሥራችን እንመለስ ( መጽሐፈ ነህምያ 4 ፥ 15 ) . ___ የመልዕክት ርዕስ ፦ ወደ ሥራችን እንመለስ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ሕዝቦች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን :: ይህ የተለቀቀው የቪዲዮ መልዕክት ሐዋርያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን የወንጌላውያኑን ወይንም የፕሮቴስታንቱን ቤተክርስቲያንም ጭምር የሚመለከት ጉዳይ በመሆኑ ሁላችሁም በማስተዋል ሰምታችሁ እንድትጠቀሙ እጋብዛለሁ :: መልዕክቱ በቪዲዮው ላይ በግልጥ ስለተቀመጠ ብዙ ማብራራት አይጠበቅብኝም :: በአጭሩ ለማስቀመጥ ግን ይህንን ቃል የተጠቀመው ነህምያ ሲሆን በመጽሐፈ ነህምያ 4 ፥ 15 ላይ ጠላቶቻችንም ይህ ነገር እንደ ደረሰልን እግዚአብሔርም ምክራቸውን ከንቱ እንዳደረገው ሰሙ እኛም ሁላችን ወደ ቅጥሩ እያንዳንዳችንም ወደ ሥራችን ተመለስን በማለት ተናገረ :: በዚህ ውስጥ ታድያ ጌታ እግዚአብሔር የተስተጓጐለውን የራሱን ሥራ ለአስተጓጓዮች ነግሮ ሳይሆን የሚመልሰን የአስተጓጓዮችን ምክር አፍርሶና ከንቱ ምክራቸውም እንደፈረሰባቸው ለራሳቸው ሳይቀር ነግሮና አሳውቆ ነው የሚመልሰን :: እኛም ታድያ ይህን አውቀን እግዚአብሔር እስኪመልሰን መጠበቅ የለብንም :: እኛው ራሳችን ወደ ሥራው ተመለሰን መመለሳችንንም እንደ ነህምያ በሁሉም ፊት ማወጅ እና ማሳወቅ አለብን :: ነህምያ የነገረንም ሆነ ያሳየን ቁምነገር እንግዲህ ይህንን ይመስል ነበር :: ጠላት ሁልጊዜ የማይተኛ ሆኖ የእግዚአብሔርን ሥራ ለማስተጓጐል የመከረና እየመከረም ያለ ቢሆንም ምክሩ ግን ትላንት ፈርሶ የሚቀር አይሆንም ፣ ዛሬም እስከ ለዘላለምም እየፈረሰበት ይኖራል :: ይሁን እንጂ ታድያ ይሄ ጊዜ ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜው ስለሆነ እኛም የእግዚአብሔር አገልጋዮችና ቅዱሳን ሕዝቦች ይህን እውነት አውቀን ቶሎ ፈጠን በማለት እግዚአብሔር ወደ ሰጠን ሥራ መመለስ ይሁንልን እላለሁ :: ለበለጠ መረጃ ይህንን ቪዲዮ እንድትሠሙት እጋብዛለሁ :: መልዕክቱንም ሌሎች ሼር ማድረግ አትርሱ ተባረኩ :: ወንድማችሁ አባ ዮናስ ነኝ

No comments:

Post a Comment