Monday 24 July 2017

የኢየሱስ አማላጅነት ( ክፍል አምስት ) የኢየሱስ አማላጅነት ( ክፍል አምስት ) የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች እንዴት ከረማችሁ ለዚህች ለተባረከች ቀን ያደረሰን አምላክ ክብር ይግባው በመቀጠልም በዛሬው ዕለት የምንመለከተው ሃሳብ የብሉይ ኪዳኑን ሊቃነ ካህናት አስታራቂነት ከሐዲስኪዳኑ ሊቀካህናችን ከኢየሱስ ጋራ ያላቸውን ልዩነት በንጽጽርና በዝርዝር የምንመለከተው ይሆናል ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ዕብራውያን 7 ፥ 23 _ 25 ን መሠረት በማድረግ የአባቶች መጽሐፍና የቤተክርስቲያን መጽሐፍ የሆነው ሃይማኖተ አበው የተሰኘው መጽሐፍ እንዲህ ይለናል ፦ ኤጲፋንዮስም ፦ ጌታ አስታራቂ ሆኖ በመምጣቱ የቀደሙ አስታራቂዎች የነበራቸውን ጉድለት ያሟላ መካከለኛ ነውና ቤዛ ( ምትክ ሆኖ የሚሞት ) እና አዳኝ መሆኑን አስረድቷል እንዲህ በማለት « ወበእንተ ዝንቱ እግዚእ መጽአ ወተሠገወ እምእጓለ እመሕያው ወኮነ እግዚአብሔር ቃል ሰብአ ከመ የኃበነ መድኃኒተ በመለኮቱ ወይሙት ቤዛነ በትስብእቱ » ጌታ ከወዲያ ዓለም ወደዚህ ዓለም መጥቶ ከሰው ወገን ተወለደ እግዚአብሔር ቃል ሰው ሆነ አምላክ በመሆኑ ያድነን ዘንድ ሰው በመሆኑም ቤዛ ሆኖ ይሞትልን ዘንድ ( ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 58 ፥ ክፍል 13 ቊጥር 50 ) በማለት ነገረን በመሆኑም ጌታ አስታራቂ ሆኖ በመምጣቱ የቀደሙ አስታራቂዎች የነበራቸው ጉድለት ምን እንደሚመስል ወደ ሰባት ያህል የሚደርሱ ነጥቦችን ከመጽሐፍቅዱሳችን በማንሳትና ከሊቀካህኑ ከኢየሱስ አስታራቂነት ጋር በማነጻጸር ትምህርቱ በዚህ መልኩ በቪዲዮ በሰፊው ተብራርቶ ቀርቦላችኋል ስሙት ተባረኩበት ለሌሎች ላልሰሙ ሰዎችም ሼር በማድረግ የአግልግሎቱ ተካፋዮች ሁኑ ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ነኝ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment