Thursday 13 July 2017

የኢየሱስ አማላጅነት ክፍል ሁለት (ቊጥር 2 ) የኢየሱስ አማላጅነት ክፍል ሁለት ስለተፈጠረው የኔትዎርክ ችግር ይቅርታ እንጠይቃለን ይሁን እንጂ ትምህርቱ ሳይቋረጥ በሁለት ተከታታይ ቪቪዲዮዎች የቀረበ በመሆኑ ተከታተሉት የተወደዳችሁ ወገኖች በክፍል ሁለት የኢየሱስ አማላጅነት ትምህርት ከመጽሐፍቅዱሳችን ባሻገር በቤተክርስቲያኒቱ ካሉ የአባቶች መጽሐፍ ውስጥ ተጠቅሰውና ተጽፈው ስለሚገኙ በትምህርቱ ውስጥ ደረጃ በደረጃ ተዘርዝረውል ከዚያ መልስ ደግሞ የኢየሱስ ምልጃ ያመጣውን ውጤት ከመጽሐፍቅዱሳችን መልስ እንዲሁ የአባቶችን መጽሐፍ አንስተን ተመልክተናል ከእነዚህ ሃስቦች ውስጥም ዋና ዋናዎቹን መጥቀስ ቢያስፈልግ መጽሐፍቅዱሳችን በትንቢተ ኢሳይያስ 53 ፥ 12 ላይ ከዓመጸኞችም ጋር ተቆጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ ስለ ዓመጸኞችም ማለደ ያለውን በአባቶች መጽሐፍ በሃይማኖተ አበው ገጽ 124 ( 1986 ) ወይም ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 79 ክፍል 50 ቊጥር 38 ላይ እርሱ ራሱ ልመናን የሚሻ መስሎ ከጥንት ጀምሮ ያገኘንን ፍዳ ከእኛ ያርቅ ዘንድ አብን ማለደው እንደገና ደግሞ እንዲያስበን ከእርሱም እንዳይለየን ስለ እኛ አብን ይማልደው ዘንድ ባሕርያችንን ነስቶአልና አለን ምልጃው ስላስገኘልንና ስላመጣልን ውጤት ደግሞ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ሊነግረን ወዶ የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ ከፊትሕ ት ጋር ደስታን አጠገብከኝ በቀኝህም የዘላለም ፍስሐ አለ አለን መዝሙር 16 ፥ 11 ፣ የሐዋርያት ሥራ 2 ፥ 28 ታድያ የሕይወትን መንገድ ያየነው ክርስቶስ በመስቀል ጐዳና ተጉዞና በዚሁ መስቀል ላይ ሕይወቱን ከፍሎ ባሳየው ምልጀ ውስጥ ነው በዚህ የኢየሱስ የማማለድ ጸሎት በተገኘ ውጤት ራሱ ኢየሱስ መንገድና እውነት ሕይወትም ሆነን በእኔ በቀር ካልሆነ ማንም ወደ አብ አይመጣም አለን የሐንስ 14 ፥ 16 ዕብራውያን 10 ፥ 19 ይህንን የመጽሐፍቅዱስ እውነታ ተንተርሰው አባቶቻችን ደግሞ እስመ መኑሂ ዘይክል በፂሃ ኃበ እግዚአብሔር ዘእንበለ ወልድ አሉን ወደ አማርኛው ስተረጉመው ያለ ወልድ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የሚቻለው የለም የሚለውን ትርጉም የሚሰጠን ነው ሃይማኖተ አበው ገጽ 297 ፥ 8 ይመልከቱ ውድ ወገኖቼ ሆይ ትምህርቱ ወሳኝና በጣም ጠቃሚ ፣ ብዙ የሆኑ የእግዚአብሔር እውነቶችን ያዘሉ ሃሳቦችን የያዘ ስለሆነ ደግማችሁ ደጋግማችሁ ቪዲዮውን ስሙት በመካከል ግን በኔት ወርክ ችግር ምክንያት ትምህርቱ ተቋርጦ ነበር ወዲያው ብዙም ሳልቆይ ሁለተኛውን ክፍል ቀጥዬ ለዛሬ ያዘጋጀሁትን ትምህርት በለቀኩት የሁለተኛው የቪዲዮ መልዕክት አጠቃልዬዋለሁ ስለተፈጠረው ችግር ከእኔ የመጣ ሳይሆን የኔት ወርክ ችግር በመሆኑ ይቅርታ ለማለት እወዳለሁ እንግዲህ እነዚህን የተለቀቁ ሁለት ቪዲዮዎች በየተራ ስሟቸው በሚቀጥለው የትምህርት ክፍለ ጊዜ እስከምንገናኝ ሰላም ሁኑ በማለት የምሰናበታሁ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ነኝ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment