Monday 17 July 2017

የኢየሱስ አማላጅነት ክፍል ሦስት የኢየሱስ አማላጅነት ክፍል ሦስት የክፍል ሦስት ትምህርት የኢየሱስን አስታራቂነት የምንመለከትበት ክፍል ነው 1ኛ ) ኢየሱስ ያስታረቀን በሞቱ ነው እናንተም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁ ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በሃሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ ቆላስያስ 1 ፥ 21 _ 23 2ኛ ) ሞቱ ምክንያታዊ ነው በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕማማችንንም ተሸክሞአል እኛ ግን እንደተቸገረ ቆጠርነው …………………ትንቢተ ኢሳይያስ 53 ፥ 4 ፤ 1 _ 12 3ኛ ) የመሞቱና የማስታረቁ ውጤትና አጀማመሩ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር ይኸውም ዲያብሎስ ነው በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ ዕብራውያን 2 ፥ 14 ኢየሱስ ያስታረቀን በሞቱ ነው ሞቱ ደግሞ ምክንያታዊ እና ለውጤት የሆነ ሞት ነው ኢየሱስ ያስታረቀን በሞቱ ስለነበረ እርቁ ሙሉ ነው በመሆኑም ኢየሱስ ከአባቱ ጋር ግማሽ የሆነ ማስታረቅን አላደረገልንም ስለዚህ እርቁ ሙሉ ነው ያልኩት ከዚህ የተነሳ ነው ታድያ በሞቱ የተፈጸመ እርቅ እያለ ሌላ የመታረቅያ መንገድ መፈለጉ አግባብነት ያለው አይደለም መጽሐፍቅዱሳችንም ሲናገር እንዲህ አለ ሰው በሕግ ሥራ የሚጸድቅ ከሆነ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ አለን ገላትያ 2 ፥ 21 ይመልከቱ የትምህርቱ ዋና ዋና ሃሳቦች እንግዲህ እነዚህ ናቸው ይበልጥ ቪዲዮውን ስትሰሙ ደግሞ ትባረኩበታላችሁ ጌታ እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ነኝ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment