Friday 24 January 2020


የጥቅምት ገድለ አቡነ አረጋዊ
https://youtu.be/lXRIhUa9qY4 የጥቅምት ገድለ አቡነ አረጋዊ

የጥቅምት ገድለ አቡነ አረጋዊ
https://youtu.be/lXRIhUa9qY4 የጥቅምት ገድለ አቡነ አረጋዊ

https://youtu.be/m-7SN0Pzfhw ክብረ ቅዱሳን - ገድለ አቡነ አረጋዊ


"ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃል ኪዳን ሰጠው ዳግመኛም ጸሎትህ እነሆ በኔ ዘንድ ደርሶ ተሰምቷል።
ስለዚህም ከድካም ወደዕረፍት ከኀዘን ደስታ ወዳለበት ከኃሣር ወደክብር በታላቅ ደስታ እወስድህ ዘንድ ወደአንተ መጥቻለሁ አለው።
የዚህን የሀላፊውን ዓለም ክብር ስለናቅህ በመንግስተ ሰማያት የማያልፈውን የማይጠፋውን ክብር አቀዳጅሃለሁ።
በዚህ ዓለም የሐሩን ልብስ የወርቅና የብሩን ጌጥ እንደናቅህ እኔ አይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቡና ያልታሰበውን አለብስሃለሁ አስጌጥሃለሁ።
ከትውልድ ሀገርህ ወጥተህ በባዕድ አገር ስለኖርክ እኔ ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን እሰጥሃለሁ የሚያልፉ የሚፈርሱ የዚህን ዓለም ቤት ንብረት ስለናቅህ የማይፈርስ የማያልፍ የሕይወት ቤት እኔ እሰጥሃለሁ።
መታሰቢያህን ያደረገ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ።
በእውነተኛ ሃይማኖት ሁኖ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ ያጻፈ የተረጎመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ።
መታሰቢያህ በሚደረግበት ዕለት የራበውን ያጠገበ የጠማውን ያጠጣ እኔ የሕይወት እንጀራ አበላዋለሁ የሕይወት ጽዋም አጠጣዋለሁ።
በዓልህ በሚከበርበት ዕለት ለራበው ምሳውን ያበላ እኔ በምሳሐ ደብረ ጽዮን የምሳ ግብዣ አደርግለታለሁ።
በስምህ በተሠራው ቤተ መቅደስ ውስጥ የጸለየ የለመነ ፈጥኜ ጸሎቱን እሰማዋለሁ ልመናውንም እቀበለዋለሁ ቤተ ክርስቲያንህንም ለሠራ ዐሥራ ሁለት የብርሃን አዳራሽ አዘጋጅለታለሁ።
የገድልህን መጽሐፍ በመታመን በንጽሕና አድርጎ በቤቱ ያስቀመጠ ወረርሽኝ በሽታ ወይም ቸነፈር በቤቱ አይገባም ድንገተኛም የሰውና የእንስሳ ሞት አይደርስበትም የእህል ችግርም አይኖርበትም።
በጥቡዕ ልብ ሆኖ የገድልህን መጽሐፍ የሰማ ያለስንፍና በፍጹም መታመን የንባቡን ኃይለ ቃል የሰማ እኔ ለችግሩ ሁሉ ፈጥኜ እደርስለታለሁ።
ለቤተ ክርስቲያንህ መባ ያገባ ዕጣን ወይም ቅብዓ ሜሮን ወይም ዘይት የሰጠ እኔ በሰማያዊት መንግሥቴ አስገባዋለሁ።
ንጉሥም ቢሆን ለቤተ ክርስቲያንህ የሐር መጎናጸፊያ ቢሰጥ በዓልህ በሚከበርበት ዕለት ቢያከብር እኔ በመንግሥቴ አከብረዋለሁ በጠላቱም ላይ ድልን አቀዳጀዋለሁ ከመኳንንቱ ከመሳፍንቱ ጋር ሰላምን እሰጠዋለሁ በምድርም ላይ ዘመኑን ወይም ዕድሜውን አረዝምለታለሁ።
ከሁሉም ይልቅ የሞት ጥላ አያርፍብህም መልአከ ሞትም ሊያስደነግፅህ አይችልም እንደ ነቢያቶቼ ኤልያስና ሄኖክ ትሠወራለህ እንጂ።
በቡሩካን እጆችህ የቀበርካት እናትህ ዕድናንም በትንሣኤ ሕይወት እስካስነሣት ድረስ መቃብሯን አፍርሶ ሌላ ሰው እንዳይቀበርበት ወይም ለማንም እንዳይታይ እንደ እንበረም ልጅ እንደሙሴ መቃብር ይሰወራል።
ይህቺን ቤተ መቅደስህንም ታላቅና የተከበረች አደርጋታለሁ የበቁ የደጋግ ነገሥታትና ጳጳሳት የመቃብራቸው ወይም የማረፊያቸው ቦታ ትሆናለች።
ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን በሰጠው ጊዜ ክቡር አባታችን አቡነ አረጋዊ ጌታችንን አቤቱ በፊትህ ሞገስ አግኝቼስ ከሆነ እናገር ዘንድ ይፈቀድልኝ አለው።
ጌታም ወዳጄ አረጋዊ ሆይ ፈቅጄልሃለሁ ተናገር ከኔ የምትፈልገውንም ሁሉ ጠይቅ ወይም ለምን አለው።
ከዚያም አባታችን አቡነ አረጋዊ ይህን ሁሉ ለሰጠኸኝ እስከ ዘላለሙ ድረስ ስምህ የተመሰገነ የጌትነትህም ክብር የተባረከ ነው ብሎ አመሰገነ።
አሁንም ጌታ ሆይ መታሰቢያየን ያደረገ የገድሌን መጽሐፍ የጻፈ በጸሎቴ የተማመነ እስከ ስንት ትውልድ ድረስ ትምርልኛለህ አለው።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም አቤቱ ይህች ቦታ የነገሥታት የጳጳሳት የክቡራን መኳንንትና መሳፍንት ብቻ መቀበሪያ ሁና አትቅር ነገር ግን ለተገፉ ለነዳያን አባት እናት ለሞቱባቸው ለዕውራንና ለሐንካሳን መጠጊያ ትሆን ዘንድ ማንኛውም ግለሰብ ይቀበርባት እንጂ እኔ በዚች አገር እንግዳና ስደተኛ ነኝና አለው።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የተመሰገንህ አረጋዊ እንደ ቃልህ ይደረግልህ አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አቤቱ ከሩቅ ወይም ከቅርብ መጥተው ንስሐ ሳይገቡና በድንገተኛ ሞተው በዚች በአፀደ ቤተ ክርስቲያኔ የተቀበሩትን ሁሉ ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው አለ።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳንስ በተራራው ጫፍ ላይ የተቀበረ ይቅርና ከተራራው ሥር እንኳ ቢሆን ይልቁንም በስምህ የተሰየመ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ በዚያ የተቀበረው ኃጢአቱ ይሠረይለታል እነዚህንም ሁሉ ዓሥራት አድርጌ ሰጠሁህ አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም አቤቱ ይህችን ቤተ መቅደስና በውስጡዋም የሚኖሩትን ባርክ አለው።
መድኃኒታችንም ይህች ቤተ መቅደስህ የተባረከች የተቀደሰች ትሁን በውስጧም ሰው አይታጣ መብራቷ አይጥፋ ሥጋዬና ደሜ በውስጧ በተዘጋጀ ጊዜ ልምላሜ ሙቀት ያልተለየው የሠመረ በፊቴም ተቀባይነት ያለው ይሁን አለው።
አባታችን አቡነ አረጋዊም መልሶ አቤቱ ይህችን መንፈሳዊ ማኅበር ልጆቼንና ቅዱሳኖቼንም ሁሉ ባርክ አለው።
ይህች ማኅበር የተባረከች ትሁን የችግረኞች መጠጊያ የተራቡ የሚጠግቡባት የታረዙ የሚለብሱባት ወይም ለተራቡት ምግብ ለተራቆቱት ልብስ ትሁን አለው።
እሊህ ቅዱሳን ልጆችህም እልፍ አእላፋት ይሁኑ እንደባህር አሸዋ እንደሰማይ ከዋክብትም ትውልዱ ነገዱ እንደተስፋፋ ዘሩም እንደበዛ እንደ ያዕቆብ ልጆች የበዙ ይሁኑ።
ድንገተኛ በሽታ መቅሠፍት ሰውነትን የሚያዝግ የሚያጠወልግ ሕማም ወደነሱ አይቀርብም።
አባታችን አቡነ አረጋዊ አቤቱ ይህችን የማድርባትን በዓቴንና ከአንተም ጋር ቆሜ ቃል ኪዳን የተቀበልኩባትን ቦታ ባርክ።
ይልቁንም ይህቺ እግርህ ከቆመባት መሬት አፈሯን ወስደው በመቀባት መድኃኒት ትሆናቸውና ወይም ከሕመማቸው ይፈወሱ ዘንድ ባርካት አክብራትም።
ሕመም ያለበት ቢኖር ፈጥኖ ይወገድለት በፍጹም መታመን በአንገቱ ላይ እምነቱን ቢአሥር ከክፉ ደዌ ከሚያንቀጠቅጥ ወይም ከሚያንዘፈዝፍ በሽታ ይድን ዘንድ መሬቱን ወይም እምነቱን በተቀባ ጊዜ በሱ ላይ ድንቅ ድንቅ ተአምር ተፈጽሞ ከሕመሙ ነፃ ይሆን ዘንድ ፈቃድህ ይሁን በማለት አባታችን አቡነ አረጋዊ ለመነ።
ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ይሁን ይደረግልህ በማለት በማይታበል ቃሉ ቃል ኪዳን ገባለት።"
+++አሜን+++
ምንጭ፦
ገድለ አቡነ አረጋዊ፤ ዘሰኔ፤ ምዕራፍ 2 ከቁጥር 1 – 36 1978 .




ጻድቁ አቡነ አረጋዊ




እኚህ አባት ከተሰሐቱ ቅዱሳን (ከሮምና ኤሽያ ከመጡት 9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበር፡፡ እናታቸው ንገሰተ እደና ትባላለች፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳዊ ሲማሩ አድገው ወደ እሰከነድረያ ኮብልለው ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውነ አውቀው መዓርገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡
ንጉስ የሆኑ ቤታቸው የሞቀ ቤተ ሰቦቻቸውነ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አበምኔቱም ወደዚህች የሕየወት መንገድ ስለመራሀን ብፁህ አረጋዊ መባል ይገባሃልብለዋቸዋል፡፡ አረጋዊ የተባሉት ከዚያ ወዲህ ነው፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ መዐረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል። በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሶ ሲያስተምሩየሀገራችንን ዜና ሰምተው ለመምጣት 480 . ከአባ ፍሪሚናጦስ | መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በክነፉ ተሸክሞ አክሱ አድርሷቸዋል፡፡ ተመልሶ ሄደው ስለ ኢትዮጵያ ቅድስት ሀገር መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበውመነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱ ሁሉ ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም 480 . ወደ ኢትዮጵያ ራሳቸውን ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡ አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀመዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረመንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሱ፡፡ ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/9111-16 ላይበመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡
ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላች ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላ ግን ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡ ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል፡፡

በረከታቸው፣ ቃልኪዳናቸው፣ አማላጅነታቸው በሁላችን ይደር አሜን።

Copy and paste one of these options to share this book elsewhere.
Link to this page view:
http://digitalscholarship.utsc.utoronto.ca/islandora/object/gundagunde%3A6822
Link to the book:












ይህ ድረ ገጽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያሏትን መጽሐፍ ቅዱሳዊ፣ ትውፊታዊና ያሬዳዊ ሃብታት ለሚፈልግ ሁሉ ግልጽ በሆነ አቀራረብ ያቀርባል betekristian.org/gez/gitsawes 






እንደምን ሰነበታችሁ ውድ ክርስቲያኖች? . . . እስቲ አንዲት ጥያቄ ልጠይቃችሁ?
ሞትን ታውቁታላችሁ?
እኔማ አሁን ባለፈው ዕለት እንዳጋጣሚ አገኘሁት እና እባክህ ቃለ መጠይቅ ላድርግህ ብዬ ብጠይቀው አሻፈረኝ አለ፡፡ ብለው ብሰራው . . . ወይ ፍንክች!!! "ኧረ ባክህ እንደው ለአጭር ሰዓት ላስቸግርህ?" እሱ መቼ ሰምቶኝ፡፡
በመጨረሻም "በዮሐንስ አፈወርቅ?" ብዬ ስለምነው "ያኔ አስራ ሁለት አመት ገትሮ አቁሞኛል፡፡ አሁን ደግሞ ሃያ አራት ዓመት ያደርግብኝ እንደሆነ መከራ ታሳየኛለህ፡፡" አለና እሺ አለኝ፡፡ እኔም የነገረኝን በማስታወሻዬ ፃፍኩት፡፡ ይኸው አሁን በክፍል በክፍል እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌ ለእናንተ እንደሚከተለው አቀረብኩት . . .


ጥያቄ፡-   ስለትውልድህ እና እድገትህ ብታጫውተኝ?





Friday, March 6, 2015

             
ከእለታት ባንድቀን አባት የሚጠባ ልጁን እንዲጠብቅለት ከውሻው ጋር ትቶት ወደ አደን ይሄዳ።  ከአደን ሲመለስ ውሻውን በደም ተጨማልቆ በሩ ላይ አገኘው። ውሻው የተጨማለቀበትን ደም ሲመለከት ልጁን በልቶት እንደሆነ ገመተ። ልክ ሁላችንም እንደምንገምተው በጣም ተናዶ ለአደን ይዞት የነበረውን መሳሪያ አቀባበለና ውሻውን የጥይት ሩምታ አወረደበት።የተረፉ የልጁን አካል ለማየት ወደ ውስጥ እየሮጠ ገባ። ነገር ግን ልጁ አንዳችም መጥፎ ነገርአላገኘውም። ይልቁንስ ከፊትለፊት በደም የተጨማለቀ ተኩላ ሞቶ ተመለከተ።ተመልከቱ ስሜቱ ሸፍኖት የዕድሜ ልክ ፀፀት የሆነበት ስራ ፈፀመ!!! ስንቶቻችን ነገሮችን ሳናረጋግጥ ከብዙዎች
ተቆራርጠናልልልህ የፈለኩት አንተ የሰው ልጅ ሆይ! ፊትለፊት በምታይበት አይንህ ብቻ አትፍረድ! አዕምሮህንም ለፍርዱ ሹመት ስጠው! በችኮላ ስህተትን ሰርተህ ህይወትህን በሙሉ የሚፀፅትህ ነገር ውስጥ እንዳትገባ ተጠንቀቅ!!!



እንደምን ሰነበታችሁ ውድ ክርስቲያኖች? . . . እስቲ አንዲት ጥያቄ ልጠይቃችሁ?
ሞትን ታውቁታላችሁ?
እኔማ አሁን ባለፈው ዕለት እንዳጋጣሚ አገኘሁት እና እባክህ ቃለ መጠይቅ ላድርግህ ብዬ ብጠይቀው አሻፈረኝ አለ፡፡ ብለው ብሰራው . . . ወይ ፍንክች!!! "ኧረ ባክህ እንደው ለአጭር ሰዓት ላስቸግርህ?" እሱ መቼ ሰምቶኝ፡፡
በመጨረሻም "በዮሐንስ አፈወርቅ?" ብዬ ስለምነው "ያኔ አስራ ሁለት አመት ገትሮ አቁሞኛል፡፡ አሁን ደግሞ ሃያ አራት ዓመት ያደርግብኝ እንደሆነ መከራ ታሳየኛለህ፡፡" አለና እሺ አለኝ፡፡ እኔም የነገረኝን በማስታወሻዬ ፃፍኩት፡፡ ይኸው አሁን በክፍል በክፍል እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌ ለእናንተ እንደሚከተለው አቀረብኩት . . .


ጥያቄ፡-   ስለትውልድህ እና እድገትህ ብታጫውተኝ?





Friday, March 6, 2015

             
ከእለታት ባንድቀን አባት የሚጠባ ልጁን እንዲጠብቅለት ከውሻው ጋር ትቶት ወደ አደን ይሄዳ።  ከአደን ሲመለስ ውሻውን በደም ተጨማልቆ በሩ ላይ አገኘው። ውሻው የተጨማለቀበትን ደም ሲመለከት ልጁን በልቶት እንደሆነ ገመተ። ልክ ሁላችንም እንደምንገምተው በጣም ተናዶ ለአደን ይዞት የነበረውን መሳሪያ አቀባበለና ውሻውን የጥይት ሩምታ አወረደበት።የተረፉ የልጁን አካል ለማየት ወደ ውስጥ እየሮጠ ገባ። ነገር ግን ልጁ አንዳችም መጥፎ ነገርአላገኘውም። ይልቁንስ ከፊትለፊት በደም የተጨማለቀ ተኩላ ሞቶ ተመለከተ።ተመልከቱ ስሜቱ ሸፍኖት የዕድሜ ልክ ፀፀት የሆነበት ስራ ፈፀመ!!! ስንቶቻችን ነገሮችን ሳናረጋግጥ ከብዙዎች
ተቆራርጠናልልልህ የፈለኩት አንተ የሰው ልጅ ሆይ! ፊትለፊት በምታይበት አይንህ ብቻ አትፍረድ! አዕምሮህንም ለፍርዱ ሹመት ስጠው! በችኮላ ስህተትን ሰርተህ ህይወትህን በሙሉ የሚፀፅትህ ነገር ውስጥ እንዳትገባ ተጠንቀቅ!!!





No comments:

Post a Comment