Saturday 28 December 2019

[ኦ አምላኬ አስደንጋጩ ሚስጥር ይፋ ሆነ] በእስራኤል ዳንሳ ገስት ሃውስ ውስጥ የሞቱ የ4 ሰዎችን አስክሬን ገንዣለሁ የሐዋርያነትንና የፓስተርነትን ስም ለብሰው ጉድ ያፈሉ ነጭ ዱርዬዎች አሳፋሪው ገበና የተጋለጠበት ይህችን ነጭ ዱርዬዎች የምትለዋን አባባል ያገኘሁት ወይዘሮ መዓዛና የተወደደው ወንድማችን አርቲስት ዳዊት ወልደ ዮሐንስ በየኔታ ቲዩብ ከሰጡት ኢንተርቪው ውስጥ ነው በመሆኑም ይህቺ ነጭ ዱርዬዎች የምትለዋ ቃል በነ እስራኤል ዳንሳ ሠፈር ብቻ ሳይሆን በየአብያተ ክርስቲያናቱ ሁሉ ገቢራዊ ድርጊትን በመፈጸም ዓይን አውጥታና ፍጥጥ ብላ የሌባ ዓይነ ደረቅ ወይንም ዓይኔን ግንባር ያርገው የሚለውንም ስያሜ ተቀጽላ አድርጋ ያለ ፍርሃትና ያለ ይሉኝታ የምትኖር በመሆንዋ እጅግ በጣም የወደድኩዋት እና የተመቸችኝ የቃል ገለጣ ናት በዚህ አጋጣሚ ይህንን ጉድ ወደ አደባባይ ብቅ ያደረጉልንን የየኔታ ቲዩብ ፕሮግራም አዘጋጅንም ሆነ ወይዘሮ መዓዛንና አርቲስት ዳዊት ወልደ ዮሐንስን ተባረኩ ዛሬም በዘመናችን እንደ እነዚህ ያሉ አስመሳይ አካኖችንም እንዲህ በማጋለጥ ነቢዩ ናታን ዳዊትን እንዳለው እናንተም እንዲህ በግላጭ በሚዲያ ያ ሰው አንተ ነህ ማለትን አታቁሙ እላለሁ መጽሐፈ ኢያሱ ምዕራፍ 7 በሙሉ ፤ 2ኛ ሳሙኤል ምዕራፍ 12 በሙሉ ይነበብ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው አለ እንጂ ሲያጭበረብሩ ሲያታልሉ ሲዘርፉና ሲበዘብዙ ሲዋሹ ሲያስፈራሩም የሚያገኛቸው ብጹአን ናቸው አላለንም እስቲ መጽሐፉ የሚለውን አስተውለን እንመልከት የሉቃስ ወንጌል 12 ፥ 32 _ 48 ታድያ ይሄ ነገር እንዳይወጣባቸው መሣይ እስራኤል ዳንሳዎች ከጀሌዎቻቸው ጋር በመሆን እናንተን እንዳስፈራሩ እኛንም ከማስፈራራት አልቦዘኑም ከዚህ የተነሳ እኛም እንደ እናንተ እያለቀስን እንባችንንም ወደ ሰማይ እየረጨን ፍርዱን ለጌታ ሰጥተን ቁጭ ብለናል ይሁን እንጂ መስፈራራቱን ዛቻውንም ሆነ ግልምጫውን ችለን ስለ እውነት በተገፋንበት ጠባቡ ክፍላችን እውነቱ ይሰማ እያልን እና እየጮህን ነው መጽሐፋችንም እውነትን ግዛት እንጂ አትሽጣት የሚል ቃል ነውና ያስነበበን ጫናው ቢኖርም እውነቱን ግን አንለውጠውም የተወደዳችሁ ወገኖች እነዚህ ወገኖች ኢንተርቪው ያደረጉበትን ሊንክ ከዚሁ ጽሑፌ ጋር አያይዤ አስቀምጠዋለሁ መስማትም ሆነ መከታተል ትችላላችሁ ተባረኩ https://youtu.be/dL0wgKv45XA

666 ኢሊሚናቲ የአዲሱ የአለም መንግሥት ምልክቶች ( ክፍል አስራ ስድስት )

በሰሜን አሜሪካና በአካባቢዋ ለምትገኙ አብያተ ክርስቲያናት





የቀናተኛን ሰው እንጀራ አትብላ ጣፋጭ መብልም አይመርህ በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና ብላ ጠጣ ይልሃል ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም ( ምሣሌ 23 ፥ 6 እና 7 )





ወተት አጠጥቶ መግደልም ሆነ መገደል  እንጀራ ቆርሶ አሳልፎ መስጠትም ሆነ መሰጠት አለና ክርስትና አብሮ በበላሽም ሆነ አብሮ በጠጣሽ አለመሆኑን ብንማርና ብንረዳ ፣ እንደገናም በአንድነት እንጀራ መቁረስ መጽሐፍቅዱሳዊና አንድ ልብንም ሆነ ጥሩ ልብን የሚጠይቅ ሆኖ የሚበረታታ ቢሆንም ምናልባትም ከላይ እንደገለጥኩት አሁንም ሰዎች በልዩ ልዩ ጉዳዮቻቸው የተለየውን ዓላማቸውንና ተልዕኮአቸውን ሊፈጽሙ ይህንን መንገድ ይጠቀሙበትና በዚሁ ጉዳይ ሰዎችን የሚጎዱበት ፣ እግዚአብሔርም የሚያዝንበት ቢሆንስ እላለሁ :: እንደገናም በሰሜን አሜሪካ ላለን ሰዎች አሁንም እንጀራውንም ሆነ ክትፎውን ማዘጋጀት እንደ ሀገር ቤቱ ሕዝባችን ብዙም ዳገት ስለማይሆንብን ድሆችን ከማሰብና ለሌሎችም ከማካፈል ጋራ ሲሆን እንጂ አብሮ ተሰባስቦ ስለተበላ ብቻ የተዋጣላቸው መንፈሳውያን ናቸው የሚያስብለን አይሆንምና  እናስብበት የሚል መልዕክትም አለኝ ከዚህ በመቀጠል ለሀሳቤ መነሻ ጥቅሶች የሆኑኝን የመጽሐፍቅዱስ ክፍሎች አስቀምጣለሁና መጽሐፍዎን ከፍተው ያንብቡ ( መጽሐፈ መሣፍንት 5 ፥ 24 - 31 ፤ የዮሐንስ ወንጌል 13 ፥ 21 - 30 ፤ የሐዋርያት ሥራ 2 ፥ 41 - 47 ፤ የሉቃስ ወንጌል 7 ፥ 36 - 50 ፤ ምሣሌ 23 ፥ 6 እና 7 ፤ ሮሜ 14 ፥ 5  - 23 ፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 10 ፥ 31 - 33 ፤ ገላትያ 2 ፥ 10 ፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6 ፥ 17  - 20 ፤ ዕብራውያን 13 ፥ 16  ) ተባረኩ



አባ ዮናስ ሐዋርያዊ አገልጋይ

Wednesday 25 December 2019

ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ ...ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ መዝሙር ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኳችሁ በዚህ መዝሙር እንድትባረኩ ይህንን መዝሙር ጋብዤያችኋለሁ ከዚሁ ጋራ አያይዤ ነገ በተለመደው ሰዓታችን የጌታን ልደትን ምክንያት በማድረግ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ይኖረኛል ጌታ ይናገረናል ያስተምረናል ሁላችሁም ስለተጋብዛችሁ መቅረት የተከለከለ ነው ጌታ ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ

ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ ...ያሬዳዊ መዝሙር ፦ በቤተልሔም ተወልደ ተወልደ ዓማኑኤል ፤ መጣልን ጌታ ሊጎበኘን ( ዘማሪና መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ መዝሙር ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን እያልኳችሁ በዚህ መዝሙር እንድትባረኩ ይህንን መዝሙር ጋብዤያችኋለሁ ከዚሁ ጋራ አያይዤ ነገ በተለመደው ሰዓታችን የጌታን ልደትን ምክንያት በማድረግ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ይኖረኛል ጌታ ይናገረናል ያስተምረናል ሁላችሁም ስለተጋብዛችሁ መቅረት የተከለከለ ነው ጌታ ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ

ህዝቡን ያስለቀስ ዝማሬ "ክርስቶስ አለልን" ይድነቃቸው ተፈሪ Ethiopian Orthodox tewahedo Song

Friday 20 December 2019

የዘመኗ ቤተክርስቲያን መልክ

የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁንን :: ዛሬ በፊታችሁ ይህንን ርዕስ ወደ እናንተ ይዤ የቀረብኩበትን ምክንያት እንደሚከተለው አብራራለሁ :: የዘመኗ ቤተክርስቲያን መልክ የሎጥና የአብርሃም ዘመን መልክ እየሆነ ከመጣ ሰንበትበት ብሎአል :: እንዴት ለሚለው ጥያቄ ምላሼን እነሆ ብያለሁና ተከታተሉኝ ::
ሎጥና አብርሃም በመጽሐፍቅዱሳችን ቃል መሠረት ዘመዳሞችና ሎጥም የአብርሃም የወንድሙ ልጅ እንደሆነ ከቃሉ እናነባለን ኦሪት ዘፍጥረት 12 : 5 :: ይሁን እንጂ አብራም የእግዚአብሔር ጥሪ ደርሶት ከሀገሩና ከዘመዶቹ ተለይቶ በወጣ ጊዜ ሎጥ አብሮት አልተጠራም ፣ ማለትም የእግዚአብሔር ጥሪ አልደረሰውም ፣ እንዲሁ አብርሃምን ተከትሎ የወጣ መሆኑን አሁንም ቃሉ በግልጥ ይነግረናል ኦሪት ዘፍጥረት 12 ፥ 4 ፤ ኦሪት ዘፍጥረት 13 ፥ 1 :: ታድያ በእግዚአብሔር ተጠርቶ የወጣው አብራም በከብት ፣ በብርና በወርቅ እጅግ በበለጠገበት ወራት ፣ ከአብራም ጋር የሄደው ሎጥ ደግሞ የላምና የበግ መንጋ ድንኳንም ነበረው በአንድነትም ይቀመጡ ዘንድ ምድር አልበቃቸውም ፣ የነበራቸው እጅግ ነበረና በአንድነት ሊቀመጡ አልቻሉም የአብራምንና የሎጥን መንጎች በሚጠብቁት መካከልም ጠብ ሆነ በዚያም ዘመን ከነአናውያንና ፌርዛውያን በዚያች ምድር ተቀምጠው ነበር ይለናል ቃሉ ዘፍጥረት 13 ፥ 2 - 8 :: ይሁን እንጂ ይህ ጠብ ሲጀመር የሎጥና የአብራም እንጂ በሁለቱም በኩል ያለ የጠባቂዎቹ ጠብ አለመሆኑን አብራም በትክክል ጠንቅቆ ያወቀ ነውና አብራም ሎጥን እንዲህ አለው :: እኛ ወንድማማች ነንና በእኔና በአንተ በእረኞቼና በእረኞችህ መካከል ጠብ እንዳይሆን እለምንሃለሁ አንተ ግራውን ብትወስድ እኔ ወደ ቀኝ እሄዳለሁ አንተም ቀኙን ብትወስድ እኔ ወደ ግራ እሄዳለሁ አለው ይለናል ::
ውድ ወገኖቼ ሆይ የዘመኗ ቤተክርስቲያን መልክ ያልኩት እንግዲህ ከዚህ ታሪክ ተነስቼ ነው :: ሎጥ ከአብራም ጋር በፈጠረው ግጭት የአብራምንና የሎጥን መንጎች በሚጠብቁት መካከል ጠብ እንደሆነ ሁሉ ዛሬም በዘመናችን ባለች ቤተክርስቲያን ውስጥ አንድ ሎጥ ብቻ ሳይሆን ብዙ ችግር ፈጣሪ ሎጦች አሉና እነዚህ ሎጦች አብራምን ከመሰሉ በእግዚአብሔር ተጠርተው የእግዚአብሔርን ጥሪ ተግባራዊ ከሚያደርጉና ወደ ፍጻሜም ከሚወስዱ ሰዎች ጋር በሚፈጥሩት ግጭት አንድ መንጋና አንድ ሕዝብ ሆኖ በሚኖረው በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል ትልቅ የሆነ መበጣበጥና ጦርነት ይፈጠራል :: ታድያ ሎጥ ሰላማዊ መስሎ አብራምን ተከትሎ እንደወጣ ሁሉ እነዚህም በአሁን ዘመን ላለች ቤተክርስቲያን የጠብ መንስዔ የሆኑ ሎጦች አብራምን ከመሰሉ የእግዚአብሔር ጥሪ ከደረሳቸው ሰዎች ኋላ ኋላ ተከትለው የወጡ ሰዎች ቢሆኑም ሰላማዊነታቸው ግን የሚፈልጉትን እስኪያገኙ ድረስና ቢያገኙም የማይጠግቡም ሆነ በቃኝ የማይሉ በመሆናቸው ያሻቸውን ሁሉ ሊያገኙ በወደዱት መጠን ማግኘት እስከ ቻሉ ድረስ ብቻ ነው :: ድንገት ቀና ያሉ እና ቀናም የሚሉ በመሆናቸውም የሚያነሱት ረብሻ መጠን የሌለውና ገደቡንም የሳተ ስለሆነ መቋጫም ሆነ እልባት ልናበጅለት አይቻለንም :: እነዚህን የመሰሉ ሰዎችን መገላገል የሚቻለው ቀኝና ግራ ሳይሉ ሁሉንም ዕድል ለእነርሱ አሳልፎ በመስጠትና የወደዱትንም እንዲያደርጉ በመፍቀድ ብቻ ነው :: ቊሳዊና ማቴሪያሊስት ስለሆኑ ወንድምነት የሚባለው ቋንቋ እንዲህ ላሉ ሰዎች ግልጽ አይደለም አይገባቸውምም :: ከወንድምነት ይልቅ ገንዘብን ጥቅምንና ክብርንም ጭምር ያስቀደሙ በመሆናቸው ወንድምነት ለተባለው የቤተሰብነት ሕይወት የታወሩ ናቸው :: ከእነርሱ ሳይሆን ከመንጋው መካከል በሚነሳው ብጥብጥ በጥባጭነታቸው የሚታወቅ መሠርይ ሰዎች ናቸው :: የዘመኗ ቤተክርስቲያን ሎጦች ላማራቸው ፣ ለመረጡትና ለለመለመው ነገር ካልሆነ በስተቀር ለመንፈሳዊው ነገር ዓይኖቻቸው የማይነሳና ማየትም የማይችሉ ምድራዊና ሥጋውያን ሰዎች ናቸው ::
ሎጥ ዓይኑን ያነሳውና እንደ እግዚአብሔር ገነት አምሳል የሆነችውን ዞአርን የመረጠው አብራም ቀኝና ግራ ሳይል ሁሉንም ምርጫ ለእርሱ ከሰጠውና ከተወለት በኋላ ነው :: እስከዚያ ድረስ ግን ሰላማዊ መስሎ በእረኞች መካከል እየገባ ጠብን የሚጭርና የሚያቀጣጥል ጉድጓድንም መንፈሳዊ ለሆነው ለአጎቱ ለአብራም የሚምስ ሰው ሆኖ የተገኘ ነው :: ስለዚህ የጠብ መነሻና መገኛ የሆነው ሎጥ በእውነተኛው በእግዚአብሔር ሰው በአብራም ካልሆነ በስተቀር በሌላው ሰው በፍጹም የሚታወቅ አይደለም :: የዘመናችን ሎጦችም እንደዚህ ናቸው :: በእውነተኞቹ በእግዚአብሔር ሰዎች ካልሆነ በስተቀር ጠብን የጀመሩም ሆነ የቀሰቀሱ እነርሱ መሆናቸው ጨርሶ አይታወቅም :: ይልቁንም መንፈሳዊና የሚጸልዩልን ናቸው ብለን ምስጢራችንንም ሁሉ ዝክዝክ አድርገን ልንነግራቸው እንችላለን :: እነርሱ ግን ዓይን ያወጡና በእግዚአብሔርም ስም መነገድን የለመዱ ስለሆኑ እኽ ብለውም ሆነ ተቆርቋሪ መስለው ይሰሙናል ፣ ነገር ግን ከቀናት በኋላ ለሞታችን የሚሆንን ጉድጓድ ሲምሱብን እናገኛቸዋለን :: የዘመናችን የቤተክርስቲያን ሎጦችም ታድያ እንዲህ በመሆናቸው ዓይን ያውጡ ሌቦች ናቸው :: ተከትለው ወጥተው ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ባነሱት ረብሻና ብጥብጥ ምክንያት ዋናና ፊተኛ መሆንን የሚፈልጉ በመሆናቸው ዓይናችንን ከፍተን ልናያቸውና እንደሚገባም ልናውቃቸው ይገባል እላለሁኝ ::
ሎጥ አብራም ዕድሉን ሁሉ ለእርሱ ሰጥቶትና ለቆለት በመረጠው ምርጫ ምክንያት አንዱ ከሌላው እርስ በእርሳቸው ተለያዩ በማለት የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል ኦሪት ዘፍጥረት 13 : 11 :: የዘመናችን የቤተክርስቲያን ሎጦች ግን እንዲህ አይደሉም እናንተ እንኳ ማንነታቸውን አውቃችሁ ጠብን ከመጥላት የተነሳ ወንድምነት ይበልጣልና እስቲ ዕድሉን ሁሉ ልስጠው እርሱም የወደደውን ያድርግ ስትሉ ሁሉንም ነገር ብትተዉላቸው ፣ እነዚህ ሰዎች ግን እጅግ የተለዩ ፣ በአብራምም ዘመን ዓይነት እንደነበረው ሎጥ ያይደሉ በመሆናቸው ኃጢአታቸው ገጦና ፈጦ የወጣ ሆኖ ሳለ በኃጢአታቸው ተጸጽተው ንስሐ የማይገቡ መንፈስቅዱስም የማይወቅሳችው ናቸው :: ከዚህም ሌላ የመረጡትን ዞአር የያዙ እንኩዋ ቢሆኑም እጅግ በጣም ራስ ወዳዶችና ጥቅመኞች እንዲሁም ሃይማኖት ለበስ ፖለቲከኞች በመሆናቸው እንደ አብርሃሙ ዘመን ዓይነቱ ሎጥ በቀላሉ የሚፋቱአችሁ አይሆኑም :: እራሳቸውን ሎጦች ሳይሆን አብራሞች አድርገው የሚቆጥሩ በመሆናቸውም እናንተን የሎጥ ያክል ቆጥረው በሄዱበት መንገድ ሁሉ ተከትላችኋቸው እንድትሔዱ ፣ የራሳችሁ ምርጫ ቢኖራችሁም እንኳ ከእናንተ ምርጫ ይልቅ የእነርሱ ምርጫ እንደሚበልጥ አምናችሁና ተቀብላችሁ ምርጫቸውንም ምርጫዬ ነው ብላችሁ አጽድቃችሁ እንድትከተሏቸው መጣላታቸውንና መናከሳቸውን ባለማቆም የሚችሉትን ሁሉ ያደርጋሉ :: ይህንንም የሚያደርጉት አንድ ዓይነቶችና አንዱም ከሌላው የማይሻል ፣ የማይለይም ስለሆኑ ነው መጽሐፍቅዱሳችን በመጽሐፈ ምሳሌ 27 ፥ 17 ላይ ብረት ብረትን ይስለዋል ሰውም ባልንጀራውን ይስላል እንደሚል ፣ በእነርሱ ዘንድ አንዱ ከሌላው የተሻለ ሆኖ ባልንጀራውን የሚስል አይደለም :: በአጠቃላይ ሁሉም የማይሳሳሉ ዱልዱሞችና ከእጅ አይሻል ዶማዎች ናቸው :: እንደነዚህ ካሉ ፈጣጦች ፣ በሚሰሩት መልካም ያልሆነ ሥራም ከሚጸጸቱ ይልቅ ዓይኔን ግንባር ያርገው ሲሉ በከተሞች ሁሉ ከሚንቀሳቀሱ አወናባጅ ሎጦች እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ ይጠብቀን ተባረኩልኝ ::
አባ ዮናስ ጌታነህ

Sunday 8 December 2019

ወንድሞች ብሎ ሊጠራቸው አያፍርም

የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች ሰላም ለእናንተ ይሁን


እነሆኝ እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች ሲል ወንድሞች ብሎ ሊጠራቸው አያፍርም ይላል ( ዕብራውያን 2 ፥ 12 )


ውድ ወገኖቼ ሆይ ይህንን ቃል ልብ ብለን ተመልክተነዋል ? ከኢየሱስ በላይ ሐዋርያ ፣ ከኢየሱስ በላይ ነቢይ ፣ ከኢየሱስ በላይ እረኛ  ሊያውም ትልቅ እረኛና የእረኞችም አለቃ የሆነ ፣ ከኢየሱስ በላይ ወንጌላዊ ፣ ከኢየሱስ በላይ መምህር  ፣ ከኢየሱስ በላይ ሊቀ ካህን ሊያውም በሰማያት ያለፈና በአባቱ ቀኝ የተቀመጠ ትልቅ ሊቀ ካህን ፣ ከኢየሱስ በላይ ንጉሥ ሊያውም የእሾህ አክሊል ብቻ ሳይሆን  የክብርና የምሥጋናን ዘውድ ተጭኖ የታየ ንጉሥ እንደ እርሱ ያለ ማንም የለም :: ይሁን እንጂ ታድያ እንዲህ ያለው ጌታ ነው እንግዲህ ብዙዎቹ ሐዋርያ ፣ ነቢይ ፣ እረኛና የመሣሠሉትን ተብለው ስለተጠሩ ብቻ ወንድሞች ሊሉን ባፈሩበት በዚህ ዘመን ወንድሞች ብሎ ሊጠራን ያላፈረው :: ከዚህ የተነሣ እንግዲህ ዛሬ ዘመናችን ነው ወይንም በሌላኛው አባባል ዘመን መጥቶልናል ሲሉ  በእንዲህ ዓይነት አስተሳሰብ ተጠምደው ላሉ የዘመኑ እረኛ ፣ ነቢይ ፣ ሐዋርያና የመሣሠሉትን ሲባሉ ለተጠሩ ሰዎች እኛም የምንሰጣቸው ምላሽ  ከኢየሱስ ጋር ልትፍቁት የማትችሉት ወንድምነት ውስጥ የገባን ስለሆነ ወንድምነታችን ቀረባችሁ እንጂ አልቀራችሁብንም ነው ::  ደግሞም ክርስቶስ ወንድሞች ብሎ በመጥራት የሰጠን ወንድምነት የማያሳፍርና በመቤዠት ውስጥ የመጣ  የዘላለም  ወንድምነት ስለሆነ እናንተ ደግሞ ይህ ምስጢር ሳይገባችሁ ነውና ሐዋርያ ፣ መጋቢ ፣ ነቢይና የመሳሰሉትን የተባላችሁት ወንድሞች ብለን ስንጠራችሁ የሚያሳፍራችሁ ፣ የምትበሳጩ  ፣ የምታኮርፉና  የምትቆጡ ከዚህ የተነሳም ወንድምነታችንንም ጭምር ልትቀበሉት የምትቸገሩ ብትሆኑም  የተቤዠን ጌታ ግን ወንድሞቼ ብሎ ሊጠራን እኛም ወንድማችን ልንለው አያፍርብንም ፤ ደግሞም  ይሄ ጉዳይ ለእርሱ ደስታው እንጂ ችግሩ አይደለም :: በተለይ በወንጌላውያን ቤተክርስቲያን አንድን ፓስተር ወይንም አንድን ሐዋርያ አንድ አማኝ ድንገት እንኩዋን አፉን አዳልጦት ወንድም እገሌ ቢለው ፓስተሩ ፣ ሐዋርያውም በሉት ሌላው የሚሰማውን ስሜት በተለይ በዚህ ዘመን ሁላችንም እናውቀዋለን :: አንዳንዱማ  ሐዋርያ ፣ ነብይ እና የመሣሠሉትን ተብዬ ተጠርቼ ሳለ ለምን ወንድም ብላችሁ ጠራችሁኝ ? ሲል ከመጠን በላይ ያኮርፍና ላያገኘን ምሎና ተገዝቶ ፣ መንገዱንም አሳብሮ ይሄዳል በየከተማችን ያለ የመጋቢዎች ኩርፍያማ ከዚህም የባሰ ነው :: እግዚአብሔር ያስበን ወገኖቼ :: ከእኛ በፊት የአገልግሎት ቅድሚያና ብልጫም የነበረው ጳውሎስ እኮ ፣ ወንድማችን ጳውሎስ ደግሞ እንደተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ ተብሎ እስካሁን እስከ እኛ ዘመን ድረስ ይነገርለታል 2ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 15 እና 16 :: ታድያ ወንድማችን ጳውሎስ ወንድማችን ስለተባለ ወንድም ተብዬ ተጠርቻለሁና ተዋርጃለሁ ያዙኝ ልቀቁኝ አለ እንዴ አላለም :: ሐዋርያነቱንም ቢሆን እኮ ይገባኛል ብሎ በይገባኛል መንፈስ ያልተቀበለ በመሆኑ ወንድም ተብሎ መጠራቱ ለእርሱ ደስ ያሰኘው እንጂ የቆረቆረው አልሆነም 1ኛ ቆሮንቶስ 15 ፥ 9 – 11 ::  ደግሞም ከሐዋርያነት ይልቅ ወንድምነት እንደሚበልጥ በትክክል የተረዳና የገባው ስለሆነ እንደ እኛ አይደለም :: እኛ ብንሆን ግን እንደዚህ  ጳውሎስ እንደተጠራበት አጠራር ቅንነትንና ወዳጅነትን ተላብሶ  ወንድማችን ሲል በአደባባይ የጠራንን ሁሉ ልናጠፋው እንቅልፍ አይወስደንም :: እንደገናም ቤተክርስቲያንዋም የእኛ እንጂ የእርሱ ስለልሆነች ኮንትራቱ እንዳለቀ ሠራተኛ ከቤተክርስቲያን ምክንያት ፈጥረን አስፈንጥረን እናባርረዋለን :: ጌታ ዓይኖቻችንን ይክፈትልን ይህንን ያክል በአጭሩ ካልኩ እንግዲህ ይበቃኛል :: በዚህ ምንባብ ተጠቀሙ ተባረኩ ::


…..ጳውሎስም፦ ወንድሞች ሆይ፥ ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው፤ በሕዝብህ አለቃ ላይ ክፉ ቃል አትናገር ተብሎ ተጽፎአልና አላቸው
የሐዋርያት ሥራ 23 : 1 – 5


አባ ዮናስ ጌታነህ

Friday 6 December 2019

የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ከቪዲዮው መልዕክት በተጨማሪ ይህንን ጽሑፍ በማስተዋል እንድታነቡ እጋብዛለሁ ተባረኩልኝ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ እግዚአብሔርን እንደምትወድ ከጌታ ቤት በአንድም በሌላም መንገድ የከዱና የኮበለሉ ሰዎች እንደዚሁ አንድ ቀን ተመልሰው እግዚአብሔርን ይወዳሉ :: ይህም የሚሆነው በእኛ ቀን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቀን ነው :: ይህን ስል ግን እያንዳንዳችን ክርስቲያኖች ማድረግ የሚገባንን የበኩላችንን ነገር ሁሉ አናድርግ አንምከር አናስተምር አንገስጽ ማለቴ አይደለም ፣ ነገር ግን ያ ሁሉ እንዳለ ሆኖ እግዚአብሔር ደግሞ ብቻውን በሚያደርገው ነገር ከዳተኛይቱ ይሁዳ በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሰች ከመንግሥቱም ሆነ ከቤቱ የጠፉና የኮበለሉ ሰዎች ደግሞ እንዲሁ በእግዚአብሔር ክህሎት ወደ ቤቱ ይመለሳሉ :: ለዚህም ነው ጌታ እግዚአብሔር በትንቢተ ኤርምያስ 31 ፥ 22 ፤ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 14 - 22 ላይ ከዳተኛ ልጆች ሆይ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ ፣ በእውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ ያለው :: እንደገናም እኔም የተመረጠችውን ምድር የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቊጠርሽ አልሁ :: አባቴ ብለሽ የምትጠሪኝ እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር :: የእስራኤል ቤት ሆይ ለባልዋ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት ስታታልሉኝ ኖራችኋል ይላል እግዚአብሔር በማለት ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኤርምያስ ለከዳተኛዋ ይሁዳም ሆነ ለእስራኤል ቤት ተናገረ :: ታድያ ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኩል ማምጣቱ እስራኤል ዘወትር አምላኩዋ ያደረገላትን ሁሉ ማስታወስ ነበረባት :: በእርሱ ብቻ በመታመን እርሱንም ማምለክ ነበረባት ፣ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ረስታዋለች ከልብዋም አውጥታ ጥላዋለች ከዚህ የተነሳ በትንቢተ ኤርምያስ 2 ፥ 32 ላይ ጌታ እግዚአብሔር በውኑ ለእስራኤል ምድረበዳ ወይስ የጨለመች ምድር ሆንሁበትን ? ሕዝቤስ ስለምን እኛ ፈርጥጠናል ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ አንመለስም ይላል ? በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን ? ሕዝቤ ግን የማይቆጠር ወራት ረስቶኛል በማለት ሲናገር እንመለከታለን :: እንግዲህ ሕዝቤ ተብላ ወደ አንተ አንመለስም ስትል የማይቆጠር ወራት አምላኳን የረሳች እስራኤል ናት በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር ተመልሳ በዚሁ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 21 መሠረት እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት መንገዳቸውን አጣመዋልና የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኮረብታዎች ተሰማ የሚለን ::

ይህንን መልዕክት በተለቀቀው ቪዲዮ የሰማችሁም ሆነ ለማንበብ ፈቃደኛ ሆናችሁ መልዕክቱን የምታነቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥምና ለጠፉ ሰዎች በፍቅር ሆናችሁ የመናገርም ሆነ የመመስከር ፋይላችሁን አትዝጉ ደግሞም ፈራጁ እያለ እናንተንም ሆነ ሁላችንን ስላልተቀበሉን ፣ ስላልተቀበሏችሁ ፣ ስላላስተናገዱን ስላላስተናገዷችሁ መጸለይ አለበለዚያም እነርሱን በግል ሄዶ ማነጋገርና ማመካከር መጨረስ የሚገባንንም እዚያው በግል መጨረስ ነው እንጂ ከብስጭትም ሆነ ከመመረር የተነሳ እንዲሁ መድረኩ ስለተገኘ ብቻ እነዚሁኑ ሰዎች በየሶሻል ሚዲያው ገበናቸውን አውጥተን የውይይት አጀንዳ ባናድርጋቸው ፣ ደግሞም እንደ ጳውሎስና በርናባስም እስከ መከፋፋት ደርሰን ባንለያይባቸው እንደገናም ነገ የሚሆነውን አናውቅምና ከዚህም ሌላ ከጌታ ዘንድ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም እንባላለንና በችኮላ ተናደን የፍርድን ቃል በላያቸው ባንናገር የተሻለ ነው የሚሆነው :: እነዚህን ጥቅሶች በማስተዋል አንብቧቸው የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 51 - 56 ፤ የሐዋርያት ሥራ 15 ፥ 36 - 41 ፤ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥ 11 ፤ ፊልሞና ቊጥር 8 - 25 :: ዛሬ ላይ ሁላችንም ማለት ይቻላል ብለን ብለን ተስፋ የቆረጥንባቸውን ሰዎች በነገው ሕይወታቸው እግዚአብሔር ወደ ቤቱ በምን ዓይነት መንገድ ጠርቶና መልሶ እንደሚጠቀምባቸው ከአንዳንዶች በቀር አብዛኞቻችን ላናውቅ እንችላለን :: ይህ ሲባል ግን የተግሳጽም ሆነ የዘለፋ እንዲሁም የምክር መልዕክቶችን ጌታ እንደሰጠን መጠን አንናገር አናስተላልፍ እያልኩ አለመሆኔን በግልጽ ልትረዱልኝ ይገባል :: እንደውም መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር ነው የሚለን ትንቢተ ኢሳይያስ 58 ፥ 1 እንመልከት :: ከዚህ በመቀጠል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ የእስራኤልም ሆነ አሁን ላይ ያለ የሐዲስ ኪዳን ሕዝብን አሳዛኝ ጩኸትና የመመለስ ልቅሶ እንዲህ በማለት አስደናቂ በሆነው የመዝሙር ስንኞቹ እና ዜማው ገልጾታልና እርሱን እጋብዛችኋለሁ ተከታተሉ ::

አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው

በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው

ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት

ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት

ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት

በመራራ ፡ ጩኸት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት

መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል

ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል

ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም

ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)


ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አሳፍሮ

በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ

ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን

ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)

አባ ዮናስ ጌታነህ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ


የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ከቪዲዮው መልዕክት በተጨማሪ ይህንን ጽሑፍ በማስተዋል እንድታነቡ እጋብዛለሁ ተባረኩልኝ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ እግዚአብሔርን እንደምትወድ ከጌታ ቤት በአንድም በሌላም መንገድ የከዱና የኮበለሉ ሰዎች እንደዚሁ አንድ ቀን ተመልሰው እግዚአብሔርን ይወዳሉ :: ይህም የሚሆነው በእኛ ቀን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቀን ነው :: ይህን ስል ግን እያንዳንዳችን ክርስቲያኖች ማድረግ የሚገባንን የበኩላችንን ነገር ሁሉ አናድርግ አንምከር አናስተምር አንገስጽ ማለቴ አይደለም ፣ ነገር ግን ያ ሁሉ እንዳለ ሆኖ እግዚአብሔር ደግሞ ብቻውን በሚያደርገው ነገር ከዳተኛይቱ ይሁዳ በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሰች ከመንግሥቱም ሆነ ከቤቱ የጠፉና የኮበለሉ ሰዎች ደግሞ እንዲሁ በእግዚአብሔር ክህሎት ወደ ቤቱ ይመለሳሉ :: ለዚህም ነው ጌታ እግዚአብሔር በትንቢተ ኤርምያስ 31 ፥ 22 ፤ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 14 - 22 ላይ ከዳተኛ ልጆች ሆይ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ ፣ በእውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ ያለው :: እንደገናም እኔም የተመረጠችውን ምድር የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቊጠርሽ አልሁ :: አባቴ ብለሽ የምትጠሪኝ እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር :: የእስራኤል ቤት ሆይ ለባልዋ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት ስታታልሉኝ ኖራችኋል ይላል እግዚአብሔር በማለት ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኤርምያስ ለከዳተኛዋ ይሁዳም ሆነ ለእስራኤል ቤት ተናገረ :: ታድያ ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኩል ማምጣቱ እስራኤል ዘወትር አምላኩዋ ያደረገላትን ሁሉ ማስታወስ ነበረባት :: በእርሱ ብቻ በመታመን እርሱንም ማምለክ ነበረባት ፣ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ረስታዋለች ከልብዋም አውጥታ ጥላዋለች ከዚህ የተነሳ በትንቢተ ኤርምያስ 2 ፥ 32 ላይ ጌታ እግዚአብሔር በውኑ ለእስራኤል ምድረበዳ ወይስ የጨለመች ምድር ሆንሁበትን ? ሕዝቤስ ስለምን እኛ ፈርጥጠናል ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ አንመለስም ይላል ? በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን ? ሕዝቤ ግን የማይቆጠር ወራት ረስቶኛል በማለት ሲናገር እንመለከታለን :: እንግዲህ ሕዝቤ ተብላ ወደ አንተ አንመለስም ስትል የማይቆጠር ወራት አምላኳን የረሳች እስራኤል ናት በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር ተመልሳ በዚሁ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 21 መሠረት እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት መንገዳቸውን አጣመዋልና የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኮረብታዎች ተሰማ የሚለን ::

ይህንን መልዕክት በተለቀቀው ቪዲዮ የሰማችሁም ሆነ ለማንበብ ፈቃደኛ ሆናችሁ መልዕክቱን የምታነቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥምና ለጠፉ ሰዎች በፍቅር ሆናችሁ የመናገርም ሆነ የመመስከር ፋይላችሁን አትዝጉ ደግሞም ፈራጁ እያለ እናንተንም ሆነ ሁላችንን ስላልተቀበሉን ፣ ስላልተቀበሏችሁ ፣ ስላላስተናገዱን ስላላስተናገዷችሁ መጸለይ አለበለዚያም እነርሱን በግል ሄዶ ማነጋገርና ማመካከር መጨረስ የሚገባንንም እዚያው በግል መጨረስ ነው እንጂ ከብስጭትም ሆነ ከመመረር የተነሳ እንዲሁ መድረኩ ስለተገኘ ብቻ እነዚሁኑ ሰዎች በየሶሻል ሚዲያው ገበናቸውን አውጥተን የውይይት አጀንዳ ባናድርጋቸው ፣ ደግሞም እንደ ጳውሎስና በርናባስም እስከ መከፋፋት ደርሰን ባንለያይባቸው እንደገናም ነገ የሚሆነውን አናውቅምና ከዚህም ሌላ ከጌታ ዘንድ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም እንባላለንና በችኮላ ተናደን የፍርድን ቃል በላያቸው ባንናገር የተሻለ ነው የሚሆነው :: እነዚህን ጥቅሶች በማስተዋል አንብቧቸው የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 51 - 56 ፤ የሐዋርያት ሥራ 15 ፥ 36 - 41 ፤ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥ 11 ፤ ፊልሞና ቊጥር 8 - 25 :: ዛሬ ላይ ሁላችንም ማለት ይቻላል ብለን ብለን ተስፋ የቆረጥንባቸውን ሰዎች በነገው ሕይወታቸው እግዚአብሔር ወደ ቤቱ በምን ዓይነት መንገድ ጠርቶና መልሶ እንደሚጠቀምባቸው ከአንዳንዶች በቀር አብዛኞቻችን ላናውቅ እንችላለን :: ይህ ሲባል ግን የተግሳጽም ሆነ የዘለፋ እንዲሁም የምክር መልዕክቶችን ጌታ እንደሰጠን መጠን አንናገር አናስተላልፍ እያልኩ አለመሆኔን በግልጽ ልትረዱልኝ ይገባል :: እንደውም መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር ነው የሚለን ትንቢተ ኢሳይያስ 58 ፥ 1 እንመልከት :: ከዚህ በመቀጠል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ የእስራኤልም ሆነ አሁን ላይ ያለ የሐዲስ ኪዳን ሕዝብን አሳዛኝ ጩኸትና የመመለስ ልቅሶ እንዲህ በማለት አስደናቂ በሆነው የመዝሙር ስንኞቹ እና ዜማው ገልጾታልና እርሱን እጋብዛችኋለሁ ተከታተሉ ::

አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው

በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው

ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት

ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት

ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት

በመራራ ፡ ጩኸት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት

መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)



የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል

ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል

ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም

ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)


ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አሳፍሮ

በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ

ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን

ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን



አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን

ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን

መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)

አባ ዮናስ ጌታነህ

ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ


የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ከቪዲዮው መልዕክት በተጨማሪ ይህንን ጽሑፍ በማስተዋል እንድታነቡ እጋብዛለሁ ተባረኩልኝ
ከዳተኛይቱ ይሁዳ አንድ ቀን በሙሉ ልብዋ ተመልሳ እግዚአብሔርን እንደምትወድ ከጌታ ቤት በአንድም በሌላም መንገድ የከዱና የኮበለሉ ሰዎች እንደዚሁ አንድ ቀን ተመልሰው እግዚአብሔርን ይወዳሉ :: ይህም የሚሆነው በእኛ ቀን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቀን ነው :: ይህን ስል ግን እያንዳንዳችን ክርስቲያኖች ማድረግ የሚገባንን የበኩላችንን ነገር ሁሉ አናድርግ አንምከር አናስተምር አንገስጽ ማለቴ አይደለም ፣ ነገር ግን ያ ሁሉ እንዳለ ሆኖ እግዚአብሔር ደግሞ ብቻውን በሚያደርገው ነገር ከዳተኛይቱ ይሁዳ በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሰች ከመንግሥቱም ሆነ ከቤቱ የጠፉና የኮበለሉ ሰዎች ደግሞ እንዲሁ በእግዚአብሔር ክህሎት ወደ ቤቱ ይመለሳሉ :: ለዚህም ነው ጌታ እግዚአብሔር በትንቢተ ኤርምያስ 31 ፥ 22 ፤ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 14 – 22 ላይ ከዳተኛ ልጆች ሆይ እኔ ባለቤታችሁ ነኝና ተመለሱ ፣ በእውቀትና በማስተዋል የሚመሯችሁን እረኞች እሰጣችኋለሁ ያለው :: እንደገናም እኔም የተመረጠችውን ምድር የትኛውም ሕዝብ ያላገኘውን የተዋበች ርስት ልሰጥሽ እንደ ወንዶች ልጆቼ ምንኛ በደስታ ልቊጠርሽ አልሁ :: አባቴ ብለሽ የምትጠሪኝ እኔንም ከመከተል ዘወር የማትዪ መስሎኝ ነበር :: የእስራኤል ቤት ሆይ ለባልዋ ታማኝ እንዳልሆነች ሚስት ስታታልሉኝ ኖራችኋል ይላል እግዚአብሔር በማለት ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኤርምያስ ለከዳተኛዋ ይሁዳም ሆነ ለእስራኤል ቤት ተናገረ :: ታድያ ይህንን መልዕክት በነቢዩ በኩል ማምጣቱ እስራኤል ዘወትር አምላኩዋ ያደረገላትን ሁሉ ማስታወስ ነበረባት :: በእርሱ ብቻ በመታመን እርሱንም ማምለክ ነበረባት ፣ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ረስታዋለች ከልብዋም አውጥታ ጥላዋለች ከዚህ የተነሳ በትንቢተ ኤርምያስ 2 ፥ 32 ላይ ጌታ እግዚአብሔር በውኑ ለእስራኤል ምድረበዳ ወይስ የጨለመች ምድር ሆንሁበትን ? ሕዝቤስ ስለምን እኛ ፈርጥጠናል ከእንግዲህ ወዲህ ወደ አንተ አንመለስም ይላል ? በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን ? ሕዝቤ ግን የማይቆጠር ወራት ረስቶኛል በማለት ሲናገር እንመለከታለን :: እንግዲህ ሕዝቤ ተብላ ወደ አንተ አንመለስም ስትል የማይቆጠር ወራት አምላኳን የረሳች እስራኤል ናት በሙሉ ልብዋ ወደ እግዚአብሔር ተመልሳ በዚሁ በትንቢተ ኤርምያስ 3 ፥ 21 መሠረት እግዚአብሔር አምላካቸውን በመርሳት መንገዳቸውን አጣመዋልና የእስራኤል ሕዝብ ጩኸት አሳዛኝ ልቅሶ ባድማ ከሆኑት ኮረብታዎች ተሰማ የሚለን ::
ይህንን መልዕክት በተለቀቀው ቪዲዮ የሰማችሁም ሆነ ለማንበብ ፈቃደኛ ሆናችሁ መልዕክቱን የምታነቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥምና ለጠፉ ሰዎች በፍቅር ሆናችሁ የመናገርም ሆነ የመመስከር ፋይላችሁን አትዝጉ ደግሞም ፈራጁ እያለ እናንተንም ሆነ ሁላችንን ስላልተቀበሉን ፣ ስላልተቀበሏችሁ ፣ ስላላስተናገዱን ስላላስተናገዷችሁ መጸለይ አለበለዚያም እነርሱን በግል ሄዶ ማነጋገርና ማመካከር መጨረስ የሚገባንንም እዚያው በግል መጨረስ ነው እንጂ ከብስጭትም ሆነ ከመመረር የተነሳ እንዲሁ መድረኩ ስለተገኘ ብቻ እነዚሁኑ ሰዎች በየሶሻል ሚዲያው ገበናቸውን አውጥተን የውይይት አጀንዳ ባናድርጋቸው ፣ ደግሞም እንደ ጳውሎስና በርናባስም እስከ መከፋፋት ደርሰን ባንለያይባቸው እንደገናም ነገ የሚሆነውን አናውቅምና ከዚህም ሌላ ከጌታ ዘንድ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም እንባላለንና በችኮላ ተናደን የፍርድን ቃል በላያቸው ባንናገር የተሻለ ነው የሚሆነው :: እነዚህን ጥቅሶች በማስተዋል አንብቧቸው የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 51 – 56 ፤ የሐዋርያት ሥራ 15 ፥ 36 – 41 ፤ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥ 11 ፤ ፊልሞና ቊጥር 8 – 25 :: ዛሬ ላይ ሁላችንም ማለት ይቻላል ብለን ብለን ተስፋ የቆረጥንባቸውን ሰዎች በነገው ሕይወታቸው እግዚአብሔር ወደ ቤቱ በምን ዓይነት መንገድ ጠርቶና መልሶ እንደሚጠቀምባቸው ከአንዳንዶች በቀር አብዛኞቻችን ላናውቅ እንችላለን :: ይህ ሲባል ግን የተግሳጽም ሆነ የዘለፋ እንዲሁም የምክር መልዕክቶችን ጌታ እንደሰጠን መጠን አንናገር አናስተላልፍ እያልኩ አለመሆኔን በግልጽ ልትረዱልኝ ይገባል :: እንደውም መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር ነው የሚለን ትንቢተ ኢሳይያስ 58 ፥ 1 እንመልከት :: ከዚህ በመቀጠል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ የእስራኤልም ሆነ አሁን ላይ ያለ የሐዲስ ኪዳን ሕዝብን አሳዛኝ ጩኸትና የመመለስ ልቅሶ እንዲህ በማለት አስደናቂ በሆነው የመዝሙር ስንኞቹ እና ዜማው ገልጾታልና እርሱን እጋብዛችኋለሁ ተከታተሉ ::
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው
በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው
ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት
ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት
ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት
በመራራ ፡ ጩኸት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት
መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል
ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል
ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም
ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አሳፍሮ
በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ
ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን
ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
አባ ዮናስ ጌታነህ