Monday 31 December 2018

የኢየሱስ ደቀመዝሙር መሆን ክፍል አንድ ትምህርት የትምህርት ርዕስ ፦ የኢየሱስ ደቀመዝሙር መሆን ( ክፍል አንድ ) የተወደዳችሁ ቅዱሳን ወገኖችና የእግዚአብሔር ሕዝቦች በሙሉ ተባረኩ እንደሰማችሁትና እንደተከታተላችሁት ጌታ አጃቢዎች እንድንሆን ሳይሆን ትክክለኛ የራሱ ደቀመዛሙርት እንድንሆን ስለፈለገ ይህንን መሠረታዊ ትምህርት በትምህርቱ የመነሻ ክፍለጊዜያችን ላይ ሰጥቶናል :: ዓለምን እንደኖህ በጽድቅ የምንኮንን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንድንሆን ራሳችንን ለጸጋው ባለቤት ለእግዚአብሔር በማስገዛት ጸጋውን ተቀብለን ወደዚህ ሕይወት ልንመጣ እንደምንችል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር በመንፈሱ አማካኝነት በጽኑ ተናግሮናል :: ያገለገለንን የእግዚአብሔር ሰው መምህር ጌታቸው ምትኩን ጌታ እግዚአብሔር ይባርከው ለማለት እፈልጋለሁ ትምህርቱ እንግዲህ ሰኞ ሰኞ ሁልጊዜ በዚሁ ሰዓት ይቀጥላል :: ይህንንም ትምህርት ለሰዎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ :: ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ :: ጌታ እግዚአብሔር የሳምንት ሰው ይበለን ቸር እንሰንብት ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment