Thursday 20 December 2018

በመምህር ጌታቸው የተዘጋጀ ትምህርት ነበረ በኮኔክሽን ምክንያት ቢቁዋረጥም ጌታ በመንፈሱ ያካፈለን መልዕክት ነበረ ...የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን መምህር ጌታቸው ምትኩ የኢየሱስ ደቀመዝሙር መሆን በሚል ርዕስ ተከታታይ ትምህርት ለመስጠት በሰዓቱ ተገኝቶ ነበር ነገር ግን በኮኔክሽን ችግር ምክንያት በዕለቱ ሊያስተላልፍልን ይዞት የመጣውን ትምህርት ማስተላለፍ አልቻለም በሚቀጥለው ጊዜ ጌታ ረድቶን በሚኖረን ፕሮግራም ያለምንም ችግር ለተከታታይ ሳምንታት ሳይቋረጥ እናስተላልፋለን ብለን እናምናለን ወንድማችን እንደምታውቁት ለማስተማር ከኢትዮጵያ ነውና የሚገባው የሃገራችንን የኔት ወርክ ሁኔታ ደግሞ ታውቁታላችሁና በጣም አስቸጋሪ ነው ለወደፊቱም ያለምንም ችግር የተዘጋጁበትን ትምርቶች እንደሚገባ እንዲያስተላልፉ ከኢትዮጵያ ለሚገቡ አገልጋዮችም ሆነ እዚሁ ላለነው ለእኛም ጭምር አብዝታችሁ ጸልዩልን ለማለት እወዳለሁ ይሁን እንጂ ጌታ መልዕክት ስለነበረው በሚደንቅ ሁኔታ ቃሉን በመንፈስቅዱስ አማካኝነት አስተላልፎልናል መልዕክቱ የሚጠቅማችሁ ስለሆነ ደጋግማች በማስተዋል ስሙት ጌታ እግዚአብሔር ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment