Thursday 6 December 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 10 ) ለሁሉም ሰው ለማርያምም ጭምር የኢየሱስ ሞት አስደናቂ ነው ይሁን እንጂ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ይገኝበታል በተባለው መጽሐፈ ዚቅ ፦ « ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል » የሚል ሃሳብ ተጽፎ ብናገኝም 1ኛ ) የማርያም ሞት ግን አይደለም ለእኛ ፣ ለራስዋ ለማርያም እንኩዋ ያስፈራት እንጂ ያስደነቃት አልነበረም ለምን ስንል ፦ የሞት ጣር ያዘኝ፤ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድ ደረሰብኝ ( መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 22 : 5 - 6 ) የሞት ጣር ያዘኝ፥ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድም ደረሰብኝ ( መዝሙረ ዳዊት 18 : 4 - 5 ) ልቤ በላዬ ተናወጠብኝ፥ የሞት ድንጋጤም ወደቀብኝ ( መዝሙረ ዳዊት 55 : 4 ) የሞት ጣር ያዘኝ፥ የሲኦልም ሕማም አገኘኝ፤ ጭንቀትንና መከራን አገኘሁ ( መዝሙረ ዳዊት 116 : 3 ) ፊቴ ከልቅሶ የተነሣ ቀላ የሞት ጥላ በዓይኖቼ ቆብ ላይ አለ ( መጽሐፈ ኢዮብ 16 : 16 ) የጥዋት ብርሃን ለእነርሱ ሁሉ እንደ ሞት ጥላ ነው የሞትን ጥላ ድንጋጤ ያውቃሉና (መጽሐፈ ኢዮብ 24 : 17 ) 2ኛ ) በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ራሱ በሥጋው ወራት ፦ ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት ይለናል ዕብራውያን 5 : 7 ከዚያ በፊት ግን ፦———————————— ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም፦ አባት ሆይ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 41 - 42 ) ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 43 - 44 ) ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው ስለ ምን ትተኛላችሁ ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 45 - 46 ) 3ኛ ) ኢየሱስ በሥጋና በደም እንዲሁ በመካፈሉ የመጣ ለውጥ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ ይለናል ( ዕብራውያን 2 : 14 - 15 ) 4ኛ ) ይህ እንዲሆን ታድያ ኢየሱስ የተናገረው ፣ አባቱም እግዚአብሔር ያደረገው ወይም የሠራው ሥራ ነበረ እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች ይሰጣል፤ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል ( የማቴዎስ ወንጌል 20 : 18 ) እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች አልፎ ይሰጣል፥ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል፥ ለአሕዛብም አሳልፈው ይሰጡታል ( የማርቆስ ወንጌል 10 : 33 ) እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና ( የሐዋርያት ሥራ 2 : 24 ) ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ ( የዮሐንስ ራእይ 1 : 18 ) 5ኛ )ለሁሉም ሰው ለማርያምም ጭምር የኢየሱስ ሞት አስደናቂ መሆኑ በነቢዩም በኢሳይያስ፦ የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር፥ የባሕር መንገድ፥ በዮርዳኖስ ማዶ፥ የአሕዛብ ገሊላ፤ በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፥ በሞት አገርና ጥላ ለተቀመጡትም ብርሃን ወጣላቸው የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ ( የማቴዎስ ወንጌል 4 : 14 - 16 ) ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል ( የሉቃስ ወንጌል 1 : 79 ) እናንተንም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁና ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ፥ በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ ( ቆላስይስ 1 21 -22 ) የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ( 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ 15 : 56 ) ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን ( ሮሜ 6 : 7 -8 ) በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና ( ሮሜ 8 : 2 ) ቃሉ የታመነ ነው እንዲህ የሚለው፦ ከእርሱ ጋር ከሞትን፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንኖራለን ( 2ኛ ጢሞቴዎስ2 : 11 ) አዎን፥ ሙታንን በሚያነሣ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን፥ እኛ ራሳችን የሞትን ፍርድ በውስጣችን ሰምተን ነበር እርሱም ይህን ከሚያህል ሞት አዳነን፥ ያድነንማል ( 2ኛ ቆሮንቶስ 1 : 9 -10 ) ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው ? ( 2ኛ ቆሮንቶስ 2 : 16 ) ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ ተሻረው ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም ? የኵነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ፥ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና ( 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ 3 : 7 ) እኛ ወንድሞችን የምንወድ ስለ ሆንን ከሞት ወደ ሕይወት እንደ ተሻገርን እናውቃለን፤ ወንድሙን የማይወድ በሞት ይኖራል ( 1ኛ ዮሐንስ መልእክት 3 : 14 ) ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment