Tuesday 9 January 2018

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Cchallenges ) ክፍል አምስት በነቢያት አገልግሎት ዙርያ ( ቁጥር 15 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Cchallenges ) ክፍል አምስት በነቢያት አገልግሎት ዙርያ ( ቁጥር 15 ) ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ .............የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዘካርያስ ልጅ ወደ ዮሐንስ በምድረበዳ መጣ የማቴዎስ ወንጌል 3 : 4 ፤ የሉቃስ ወንጌል 3 ፥ 1 _ 6 የዮሐንስ መጥምቁ ሕይወቱ ገዳማዊ ሕይወትን ያመለክታልን ? ዮሐንስ መጥምቁስ ገዳማዊ ሕይወትን ያበረታታልን ? ገዳማዊ ሕይወትን የሚያበረታቱ የገድላትና የድርሳናት ጽሑፎች በእግዚአብሔር ቃል ሲፈተሹ የሚል መሪ ሃሳብ የያዘ ሲሆን ከዚህም ባሻገር ፦—————— ትምህርቱ ከመጽሐፍቅዱስ ሌላ የክርስቶስን ብቸኛ አዳኝነት የሚገልጹ ከመጽሐፍቅዱሳችንም ጋር በተያያዥነት አስረጅ ሆነው የቀረቡ የቤተክርስቲያኒቱ መጻሕፍት በትንታኔና በቤተክርስቲያኒቱ የግዕዝ ቋንቋ ታግዘው የተጠቀሱበት እውነት ይገኝበታል ከዚህም ሌላ አቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ በገድላቸው ላይ እግዚአብሔር የኢትዮጵያን ኃጢአት አሳይቶኝ በባሕር ውስጥ ለመቶ ዓመት ቁልቁል ተዘቅዝቄ ጸለይኩላት ላሉት ሃሳባቸው ዛሬም በኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን በወንጌላውያኑም አብያተክርስቲያናት ያሉ ነቢያትና አገልጋዮች ለታያቸው በደልና ኃጢአት ምላሽ ሊሰጡ ቊልቊል ተዘቅዝቀው ጸለዩ ባንልም ታየኝ ተገለጠልኝ በሚል ሰበብ ብቻ አብዛኛዎቹ ማለት ይቻላል ከአቡዬ ገብረ መንፈስቅዱስ ባልተናነሰ ሁኔታ እየፈጸሙት ስላለው ስሕተት ማስተካከያና እርማት በመስጠት ትምህርቱ ግልጽ የሆነ መጽሐፍቅዱሳዊ ትንታኔና መረጃን ያቀርባል ስለዚህ ቅዱሳን እንዲሁም የእግዚአብሔርን ቃል መማር የምትፈልጉ ወገኖች በሙሉ መልዕክቱን መስማታችሁ ለሕይወታችሁ ወሳኝ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ ተከታተሉ እላለሁኝ ተባረኩ

No comments:

Post a Comment