Thursday 11 January 2018

ስለ ሕግ በመጽሐፍቅዱስ ተጠቅሰው ስላሉ በዓላትና ኦርቶዶክሳዊ በዓላት አከባበር የተሰጠ በመረጃ የተደገፈ መጽ... ስለ ሕግ በመጽሐፍቅዱስ ተጠቅሰው ስላሉ በዓላትና ኦርቶዶክሳዊ በዓላት አከባበር የተሰጠ በመረጃ የተደገፈ መጽሐፍቅዱሳዊ ትምህርት ( ክፍል አንድ ) ፈጣን ተሃድሶ ለኦርቶዶክስ ተአምረ ማሪያም ከክርስቶስ ለይቶን የኖረ ወንጀለኛ መጽሐፍ እመቤታችን በዓላቶችዋ ሁሉ ሠላሳ ሦስት ( 33 ) ናቸው እነዚህን በዓላቶች እንደ እሁድ ሰንበት አድርገው ይቁጠሩዋቸው። ከዓመት እስከ ዓመት እስከዘ ለዓለም ምንም ስራ አይስሩባቸው፤ ( የተአምረ ማርያም መቅድም ቁ፡32_34 ) መጽሐፈ ሰዓታት ( የሰዓታት መጽሐፍ ) ስለ ምስጋና የተናገረው ትርጉም ፦ የዓለም ሁሉ ቤዛ የሆንሽ ቅድስት ማርያም ሆይ ጣፋጭ በሆነው በስምሽ መታሰብያ ያማረ በሆነው በደምሽ ፍሬም እንደሰታለን ( ኲሎሙ ዘእግዝእትነ ማርያም ከሚባል ክፍል _ ገጽ 105 ) መጽሐፍቅዱሳችን ስለ ቤዛነት የተናገረው እንዲሁ የሰው ልጅም ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም ( የማርቆስ ወንጌል 10 : 45 ) የዘላለምን ቤዛነት አግኝቶ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ እንጂ በፍየሎችና በጥጆች ደም አይደለም ( ዕብራውያን 9 : 12 ) በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ ( ሮሜ 3 : 24 ) መጽሐፍቅዱሳችን ስለ በዓላት የተናገረው እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2 : 16 ስለዚህ ማንን እንስማ ? ማንን እንቀበል ? የትኛውንስ እንመን ?መጽሐፍ ቅዱስን ? ወይንስ ተአምረ ማርያምንና የሰዓታት መጽሐፍን ?መልሱን ለአድማጮች ብለናል ተባረኩ

No comments:

Post a Comment