Friday 26 January 2018

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ፧ ( ቁጥር 4 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ፧ ( ቁጥር 4 ) በነቢያት አገልግሎት ዙርያ ያሉትን አምስት ስሕተቶች የምናይበት ትምህርት የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ተባረኩ ይህ ትምህርት በነቢያት አገልግሎት ዙርያ የተነገረ ቢሆንም በተለያዩ የአገልግሎት ኦፊሶችና ጥሪዎች ዙርያ የተነገረና የተብራራ ስለሆነ በማስተዋል እንድታዳምጡት በጌታ ፍቅር እጠይቃለሁ ከዚህ በመቀጠል አምስቱን ነጥቦች እዘረዝራለሁ 1ኛ ) ለነቢያት ( በልዩ ልዩ የአገልግሎት ዘርፍ ተጠርተው ለሚያገለግሉ ) ከፍ ያለ ደረጃ መስጠት ወይም እነርሱን የሁሉ የበላይና ቁንጮ ማድረግ ( 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፥ 14 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፥ 21 ) 2ኛ ) ከፍ ባለ ግርማ ሞገስ ወይንም እራስን ካራዝማቲክ በማድረግ ሕዝብን ማተራመስ መፈለግ ( 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 12 ) 3ኛ ) ሕዝብን አቢዩዝ የሚያደርግ ማለትም እውነታውን በማጣመመ የዘለፋና የስድብ ዓይነት ሻካራ የሆኑ የነቢያትን መልዕክት መፍቀድ ( 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 13 ፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፥ 2 ) 4ኛ ) ነቢያትም ሆነ ሌሎች አገልጋዮች መካሪና ተቆጪ ስለሌላቸው ሜንቶር የሚያደርጋቸውን ማዘጋጀት ( 2ኛ ነገሥት 6 ፥ 1 _ 6 ) 5ኛ ) ስጦታዎች ሰዎችን አቢዩዝ ያደርጋሉ ብሎ በማሰብ ትንቢታዊ ስጦታዎችንም ሆነ ሌሎችን ለመዝጋት መሞከር ( 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 1 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 39 ነጥቦቹ እነዚህ ናቸው ከዚህም ሌላ የተለቀቀውን ቪዲዮ በመስማት ተባረኩ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment