Wednesday 31 January 2018

በስድብና በቅንዓት ዙርያ የተዘጋጀ ተከታታይ ፣ ወቅታዊና ትምህርት አዘል የክፍል አንድ ውይይት ከተወደደው ወንድማች...በስድብና በቅንዓት ዙርያ የተዘጋጀ ተከታታይ ፣ ወቅታዊና ትምህርት አዘል የክፍል አንድ ውይይት ከተወደደው ወንድማችን ቢንያም ጋር የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዛሬው ትምህርታችን ያጠነጠነው በስድብ ዙርያ ላይ ሲሆን በክፍል ሁለት ትምህርታችን ደግሞ የቅንዓትን አላስፈላጊነት ይዘን እንቀርባለን እነዚህ ትምህርቶች ወቅታዊና ከሕዝባችን አመለካከት እንዲሁም አስተሳሰብ ጋር በተጓዳኝነት ተያይዘው የቀረቡ በመሆናችው ሕዝባችንን ከዚህ ዓይነቱ የጨለማ አሠራር ለመታደግና ለማዳን ሲባል የተዘጋጁ ትምህርቶች ናቸው ሕዝባችን በተገቢው መንገድ የእግዚአብሔርን ቃል ካለማጥናቱና ካለመማሩም የተነሳ ለሃይማኖቱ የቀናና እግዚአብሔርንም ያገለገለ እየመሰለው ለወንጌል እውነት ቆርጠው የተነሱ አባቶችንና ወጣት አገልጋዮችንም ጭምር ሃይማኖት አፍራሽ ፣ ጡት ነካሽ ፣ ሐራ ጥቃ ፣ ተሐድሶና የመሣሠሉትን ናችሁ እያለ ፣ ስምም እያጠፋ አጋጣሚዎችን ሲያገኝ ደግሞ መንገድ ጠብቆ ልብሳችንን አውልቁ ፣ አስረክቡን እያለ እያስፈራራና እየደበደበ ከዚህም ሌላ የቃሉን መመርያ ተከትሎ ወንጌል በገባቸው አባቶች የተጻፉ መጻሕፍቶችንም እያቃጠለ በተጨማሪም በየፌስቡክ ሚዲያውና በየዩቲዩቡም ሳይቀር ተመሣሣይ የሆኑ ስድቦችንና ማስፈራራቶችን እያካሄደ ስላለ እኛ የዚህ ዘመን የቃሉ አገልጋዮች ትውልዱ ለምን ይህን አደረገ ፣ ለምንስ ተሳደበ ፣ ተቆጣና ስማችንንም አጠፋ ስንል ለመብታችን ተቆርቁረን ፣ ራሳችንንም ለመከላከልና መልስ ለመስጠት ብለን ወይንም ማስፈራራቱም ሆነ ዱላው አስደንግጦን ስጋት ላይም ጥሎን እንዲህ ያልን ሳይሆን ትውልዱ ለሃይማኖት ከመቅናት አኳያ እየሄደበት ያለው የስድብና የማሳደድ መንገድ ውሎ አድሮ የሚያስከፍለውን ዋጋ መጽሐፍቅዱሳችን ግልጥ አድርጎ ስለነገረን ትውልዱም ይህንን የእውነት ቃል አውቆና ተረድቶ ከዚህ ዓይነቱ የዓመጻ መንገድ ራሱን እንዲለይ ለመርዳት ብለን ነው እኛን የቃሉ አገልጋዮችን በተመለከተ ግን ይሄ ጉዳይ ሰው እንደመሆናችን መጠን የሚያሳስበን እንኳ ቢሆን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መከራን የሚቀበሉ መልካምን እያደረጉ ነፍሳቸውን ለታመነ ፈጣሪ አደራ ይስጡ በማለት ቃሉ የነገረን በመሆኑ የመጣውን ነገር ሁሉ በምስጋና ለመቀበል እየተዘጋጀን ነፍሳችንን ለታመነ ፈጣሪ አደራ ሰጥተናል 1ኛ ጴጥሮስ 4 ፥ 19 ከዚህ የተነሳ ጌታ ባበዛልን ጸጋ መጠን ሐዋርያው እንደነገረን ሲሰድቡን እንመርቃለን ሲያሳድዱን እንታገሣለን ክፉ ሲናገሩን እንማልዳለን 1ኛ ቆሮንቶስ 4 ፥ 11 _ 13 የወንጌል ባሕርዩ ይሄ ስለሆነ ይህንኑ ልናደርግ ራሳችንን በማማጠን ላይ እንገኛለን 2ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 3 _ 13 ቅዱሳን ወገኖች ዛሬ የለቀቅነው ትምህርትም ሆነ የሚቀጥለው ዓርብ ይዘን የምንቀርበው ትምህርት ወሳኝና ሕይወታችንንም በብዙ የሚለውጥ ትምህርት በመሆኑ አያምልጣች ስል ላበረታታችሁ እወዳለሁ ዛሬ የተለቀቀውን ቪዲዮም ሆነ ዓርብ ዕለት የሚለቀቀውን ሼር ማድረግ አትርሱ አባ ዮናስ ጌታነህ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry

Tuesday 30 January 2018

የተሃድሶና የከፍታ ዘመን ለኦርቶዶክሳዊት ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የተሃድሶና የከፍታ ዘመን ለኦርቶዶክሳዊት ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ብትመለስ እመልስሃለሁ በፊቴም ትቆማለህ፤ የከበረውንም ከተዋረደው ብትለይ እንደ አፌ ትሆናለህ…. ትንቢተ ኤርምያስ  15 : 19 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች እንደምን ሰንብታችኋል ትምህርቶቻችን በጸጋው ጉልበት ተደግፈው ወደፊት እየሄዱ ስለሆነ የእግዚአብሔር ስም ይባረክ የተሐድሶ ተግዳሮቶች( Challenges ) የሚለውን ትምህርት አጠናቅቄ ወደ አዲስ ትምህርት የምገባበት ጊዜ ነው ሐሙስ February 2 / 2018 10 AM በኦታዋ ከተማ የሰዓት አቆጣጠር የምንጀምረው አዲሱን ትምህርት ይሆናል የትምህርቱ ርዕስ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አመሠራረት» የሚል ሲሆን በዚህ ርዕስ ላይ ተመሥርቼ ቤተክርስቲያኒቱ መቼ እንደተመሠረተችና መሠረቷም እንደ እግዚአብሔር ቃል ምን እንደሚመስል ? መቼ እንደተበላሸች ? ወደ ተረትና የስሕተት ትምህርቶች ደግሞ መቼ እንደገባች ? በአሁኑ ሰዓትም ከዚህ ስሕተቷና ተረትዋ እንድትመለስ ከዚህ በፊት የነበሩት አባቶች የቱን ያህል ዋጋ እንደከፈሉ ? ዛሬም ይህቺው ቤተክርስቲያን ታድሳና ተለወጣ ፣ ወደ ጥንተ መሠረትዋ ወደ እግዚአብሔር ቃልም ተመልሳ ፣ ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ሳይቀር በረከት መሆንዋን የሚያውቁ ሰዎች ዛሬም ድረስ ዋጋ እየከፈሉላት ያሉ መሆናቸውን የሚጠቁም ትምህርት ነው የሚተላለፈው ስለዚህ ወገኖች ትምህርቱ እንዳያመልጣችሁ በሰዓታችሁ በመገኘት የትምህርቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ ስል መልዕክቴን ማስተላለፍ እፈልጋለሁ በዛሬው ዕለት በዚሁ በዕለተ ሰኞ የለቀኩት ቪዲዮ ግን ሐሙስ ለምንጀምረው ለዚህ ትምህርት እንደመግቢያ የሚሆን ትምህርት ነው ተሃድሶ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ፣ እውነተኛ ተሃድሶም የሚመጣው በምን መንገድ እንደሆነ ፣ እውነተኛው የሕይወት ተሃድሶ እንዲመጣ ደግሞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ሕይወት መጋበዝ እንደሚያስፈልግ መልዕክቱ ይጠቁማል ይህንንም ለማግኘት ኢየሱስ በዚች ቤተክርስቲያን ውስጥ በግልጽነት ሊሰበክ እንደሚያስፈልገው ፣ ይሄ ጌታ ሲሰበክ ደግሞ በስሙ ንስሐና የኃጢአት ሥርየት እንደሚገኝ እንደገናም ሰው ሁሉ ይህንን ንስሐና የኃጢአቱን ሥርየት ለማግኘት ከዚህ በፊት እንደሚያደርገው ወደ ነፍስ አባቱና ለንስሐ ወደሚጠመቅበት ወደ ቄደሩ እንዲሁም ወደ ውሃ መረጨቱ መሄድ ሳይሆን ለኃጢአት ይቅርታ ባፈሰሰው ደሙ ወደሚረጨን ወደ ኢየሱስ በመምጣት ኃጢአትንም ተናዞና ሽክምን አውርዶ በዚህ ጌታ በደሙ በመታጠብ ፍጹም የሆነ ሥርየትና የእግዚአብሔርን ይቅርታ እንደሚያገኝ ፣ የዘላለም ሕይወት ባለቤትም እንደሚሆን ትምህርቱ ይጠቁማል ወገኖች በጣም አከብራችኋለሁ ወዳችኋለሁ ሐሙስ ለሚጀምረው አዲሱ ትምህርት ተዘጋጅታችሁ ኑ በማለት መልዕክቴን በድጋሜ ለማሳሰብ እወዳለሁ ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ በቀጠሮአችንንና በሰዓታችን እስክንገናኝ ተባረኩ የምላችሁ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

Friday 26 January 2018

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ፧ ( ቁጥር 4 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ፧ ( ቁጥር 4 ) በነቢያት አገልግሎት ዙርያ ያሉትን አምስት ስሕተቶች የምናይበት ትምህርት የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ተባረኩ ይህ ትምህርት በነቢያት አገልግሎት ዙርያ የተነገረ ቢሆንም በተለያዩ የአገልግሎት ኦፊሶችና ጥሪዎች ዙርያ የተነገረና የተብራራ ስለሆነ በማስተዋል እንድታዳምጡት በጌታ ፍቅር እጠይቃለሁ ከዚህ በመቀጠል አምስቱን ነጥቦች እዘረዝራለሁ 1ኛ ) ለነቢያት ( በልዩ ልዩ የአገልግሎት ዘርፍ ተጠርተው ለሚያገለግሉ ) ከፍ ያለ ደረጃ መስጠት ወይም እነርሱን የሁሉ የበላይና ቁንጮ ማድረግ ( 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፥ 14 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፥ 21 ) 2ኛ ) ከፍ ባለ ግርማ ሞገስ ወይንም እራስን ካራዝማቲክ በማድረግ ሕዝብን ማተራመስ መፈለግ ( 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 12 ) 3ኛ ) ሕዝብን አቢዩዝ የሚያደርግ ማለትም እውነታውን በማጣመመ የዘለፋና የስድብ ዓይነት ሻካራ የሆኑ የነቢያትን መልዕክት መፍቀድ ( 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 13 ፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 12 ፥ 2 ) 4ኛ ) ነቢያትም ሆነ ሌሎች አገልጋዮች መካሪና ተቆጪ ስለሌላቸው ሜንቶር የሚያደርጋቸውን ማዘጋጀት ( 2ኛ ነገሥት 6 ፥ 1 _ 6 ) 5ኛ ) ስጦታዎች ሰዎችን አቢዩዝ ያደርጋሉ ብሎ በማሰብ ትንቢታዊ ስጦታዎችንም ሆነ ሌሎችን ለመዝጋት መሞከር ( 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 1 ፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 14 ፥ 39 ነጥቦቹ እነዚህ ናቸው ከዚህም ሌላ የተለቀቀውን ቪዲዮ በመስማት ተባረኩ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

Friday 19 January 2018

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 3 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 3 ) የቤተክርስቲያን ሥልጣን የክርስቶስ እንጂ የነቢያት ወይም የፓስተሮች አይደለምና በማናለብኝነት የክርስቶስ የሆነችን ቤተክርስቲያን የኔ ሲሉ የራሳቸው እና የቢጤዎቻቸው ሊያደርጉ የሚሯሯጡ የዘመናችን የነቢያቱ ፣ የፓስተሮቹ……. እሩጫና የኲራቱ ጒዞ እስከ መቼ ? ( ቊጥር 3 ) ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ ጓዛቸውን ጠቅልለው የገቡና ለወንጌሉ ሥራ ቆርጠው የዘመቱ ደገኛው ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የወንጌል ዘማች ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለሰሚዎቻቸው ያስተላለፉትን አንኳር የሆነውን አስተማሪ መልዕክት በአጭሩ ቀንጨብ አድርጌ እነሆ ብያለሁ እና ተከታተሉ ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? በሚለው በክፍል ስድስት ቊጥር ሦስት ትምህርታችን ላይ በጥምረት አያይዘን የምናነሳቸው ዓበይት ጉዳዮች ከዚህ እንደሚከተሉት ናቸው ትምህርታችንን ጠቅለል አድርገን በአጭሩ ስንመለከተው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመኑ ከሐዋርያቱ ይልቅ ፈጥኖ መልስ በመስጠት ለሚታወቀው ለጴጥሮስ የሰጠው መልስ ነበረ በዚህ የክርስቶስ ለቀረበ የማን ትሉኛላችሁ ጥያቄ ጴጥሮስ አንታማ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ሲል አስደናቂ መልስ ሰጠ በዚህን ጊዜ ነው ጌታችን የዮና ልጅ ስምኦን ሆይ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ እኔም እልሃለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ያለው እናንተ ምዕራፉን አውጥታችሁ የተጻፈበትን ክፍል ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 13 _ 20 የተወደዳችሁ ወገኖች እንግዲህ ይህንን የመጽሐፍቅዱስ ክፍል በማስተዋል ስናነበው ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን የራሱ አድርጎ ያያትና የቆጠራትም በመሆኑ ቤተክርስቲያኔ ብሎአታል ስለዚህ ቤተክርስቲያን የእርሱና የእርሱ ብቻ ስለሆነች እርሱም በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ስላለ በራሱ ቤተክርስቲያን ላይ ዋናው ሠራተኛ እርሱ ራሱ ነው እኛ ባሮቹ ግን ልዩ ልዩ ዓይነት የአገልግሎት ስም ቢኖረንና ስማችንም በሰዎች ዘንድ ሳይቀር ገዝፎና ከብሮ ቢጠራም ቤተክርስቲያን ግን አንዴ የእርሱና ለእርሱ ብቻ ስለሆለች የእኛ አይደለችም የእኛም ልትሆን አትችልም የእኛ የምንለው ምንአልባትም እግዚአብሔር ቤትን ካልሰራ ሠራተኛ በከንቱ ይተጋል ይላልና እግዚአብሔር በቸርነቱ የሠራልን ዞረንና አገልግለን ገብተን የምናርፍበት ቤት ሊሆን ይችላል መዝሙር 126 ( 127 ) ፥ 1 ፤ 2ኛ ሳሙኤል 7 ፥ 11 _ 18 ከዚያ ውጪ ግን የእኛ ያልሆነችዋን ቤተክርስቲያን የእኛ ልናደርግ በገዛ አዕምሮአችን ሰንፈን ከሰዎች ጋር በተጋጨንበት ፣ ከሌሎች አገልጋይ ባሮችም ጋር በተማታንበት ፣ ልንበላ ፣ ልንጠጣ ልንሰክርም በጀመርንበት ነገር ሁሉ አሁኑኑ ፈጥነን ንስሐ ልንገባ የበደልናቸውንም ሰዎች እግራቸው ላይ ወድቀን ይቅርታ ልንጠይቅ ይገባል እላለሁኝ አለበለዚያ ግን በፍጻሜው ከአምላካችን ዘንድ የሚመጣብን ቅጣት የከፋ ይሆናል የሉቃስ ወንጌል 12 ፥ 41 _ 48 ነገር ግን ከዚህ ይልቅ እምቢ አሻፈረኝ ስንል ቤተክርስቲያንን የራሳችን ልናደርጋት ብንሞክር ስንላላጥ እንኖራታለን እንጂ በምንም መልኩ ቤተክርስቲያን የእኛ ልትሆን አትችልም ደግሞም ሊቆይ ይችል ይሆናል እንጂ በጊዜ ውስጥ እግዚአብሔር ከእጃችን ወስዶ ሃላፊነታቸውን ለተገነዘቡና የቤተክርስቲያንን ማንነትም ሆነ የራሳቸውን ማንነት በውል አውቀው የማልጠቅም ባርያ ነኝ ሲሉ በትሕትና ለሚያገለግሉ ባሮች በባላደራነት ይሰጣል የሉቃስ ወንጌል 17 ፥ 10 ቤተክርስቲያን ግን ለሁልጊዜም እስከ ዘላለም የክርስቶስ ነች ኤፌሶን 1 ፥ 22 እና 23 ፣ ራዕይ 11 ፥ 15 ውድ ወገኖቼ ሆይ እንግዲህ ይህንን የቃሉን እውነት እንድናገር ግድ ያለኝ ከለቀኩት ቪዲዮ ተነስቼ ነው ትምህርቱም እንዲህ በማለት የሚናገር ነው በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ነቢያት የቤተክርስቲያን መሪዎች ነበሩ ይህ ማለት የሐዲስ ኪዳን ነቢያት በአዲሱ የኪዳን ሥርዓት መካከል የቤተክርስቲያን ጒበኞችና አቅጣጫንም ጠቋሚዎች ስለሆኑ የተለዩ መሪዎች ናቸው ኤፌሶን 4 ፥ 11 እንደገናም መጽሐፍቅዱሳችን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል ብሎናልና ቤተክርስቲያን የተገነባችው በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ነው ኤፌሶን 2 ፥ 20 ይህ ማለት ግን መጽሐፍቅዱሳችን አሁንም ቤተክርስቲያን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታነጸች አለን እንጂ ሐዋርያትና ነቢያት በቤተክርስቲያን ላይ ተመሠረቱ አላለንም ከዚህ የተነሣ ቤተክርስቲያን ለጥቂት ሕዝቦች ፍላጎትና ስኬት ሲባል ለሐዋርያትና ለነቢያት ፣ ለፓስተሮች ሥልጣን የበላይነት የተሰጠች አይደለችም እንደገናም ቤተክርስቲያን የነቢያቱም ሆነ የሐዋርያቱ እንዲሁም የመጋቢዎች ስልጣን አይደለችም ቤተክርስቲያን የክርስቶስ ሥልጣን ናት ባለ ሥልጣኗና አዛዥዋ አስተዳዳሪዋም ክርስቶስ ነው ቤተክርስቲያን ግን ራስ ከሆናት ከክርስቶስ ሥልጣን የተነሳ ለእነዚህ አገልጋዮች እውቅና እየሰጠች እንዲያገለግሉ ታደርጋለች ይህንን እውነታ ባለማወቅና አውቆም የሕይወትን ለውጥ ባለማግኘት ነው እንግዲህ ዛሬ ላይ የምናየውን ትርምስ እስካሁን የምናየው የተወደዳችሁ ወገኖች ፦ ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ በማለት የብፁዕ አባታችን አቡነ ፊልጶስን ምስክርነት በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ካሉ ነቢያትና ፓስተሮች ጋር አያይዤ ማቅረብ የፈለኩት እንግዲህ ከዚህ የተነሳ ነው ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ መልዕክታቸው በዩቲዩብ ስለተለቀቀ አቡነ ፊልጶስ ብላችሁ በመጻፍ ዩቲዩብ ውስጥ ገብታችሁ ምስክርነታቸውን ማዳመጥ ትችላላችሁ ታድያ እኚህ አባት በጠያቂያቸው በሊቀ ማዕምራን ዓባይ አማካኝነት ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ ወደ ጵጵስና ማዕረግ ከመምጣታቸው በፊት በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ብዙ ጊዜያቸውን ተቀምጠው በትምህርት ዓለም ያሳለፉ በመሆናቸው የሊቀ ጵጵስናቸውን ማዕረግ እንደተቀበሉ ለአገልግሎት የተመደቡት ጅንካ ነበርና ይህንን የሥራ ዝውውር በአሜንታ ነበር ተቀብለው ጉዞአቸውን ወደ ጂንካ ያደረጉት ታድያ ጠያቂው ሊቀ ማዕምራን ከአሜሪካ ወደ ጂንካ ሄደው ሊያገለግሉ የወሰኑበትን ጉዳይ ሊያውቅ ብሎ የጠየቀውን ጥያቄ ብፁዕነታቸው ሲመልሱ መልሳቸው ትሕትናንና መንፈሳዊነትን አዋቂነትንም ጭምር የተላበሰ በመሆኑ እጅግ ማራኪ ነበር ብፁዕነታቸው እንዲ ሲሉ ዛሬ ላይ በፓስተሮችና ነቢያቶቻችን ጭምር እግራችን እስኪነቃ ድረስ ብንፈልግ የማናገኘውን ነገር ፍንትው አድርጎ በመግለጽ መልሳቸውን አዥጎደጎዱት ከዚህም ሌላ ማን ያርዳ የነበር ማን ይናገር የቀበር እንደሚባለው እኚህ አባት አሁን ላይ እየኖሩ ያሉትን የጂንካን ሕይወት ከአሜሪካውና ከአውሮፓው ሕይወት ጋር ጎን ለጎን በማስተያየት በውስጣቸው አላባራ ብሎ እየነደደ ያለውን እውነታ ከተጻፈልን ቃል ጋር እያያያዙ አቀጣጠሉት እኔም ደገኛው ሐዋርያ እንዲህ ነው ይበል ብዬ ማስታወሻ ደብተሬንና ብዕሬን ይዤ ቀረብኩ እርሳቸውም ነገራቸውን በመቀጠል ወደ ተረሱት ወደተጣሉት መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ መጥቷል እኔም እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በእርሱ ሳይገባኝ እንዲገባኝ አድርጎ በአባቶች ወንበር ላይ እንድቀመጥ ካደረገበት ጀምሮ መንገዴን ወደ ደቡብ ኦሞ አድርጌያለሁ ብዙ ስለ ሀገሩ የተነገረኝ ነገር ነበረ እንዴት ይኖሩ ይሆን ?ተብዬም በስልክ ሳይቀር ብዙ ተወርቶልኛል ተነግሮኛልም እንግዲህ ስላልገባንና ስላላወቅን ነው እንጂ መቼም ደቡብ ኦሞ ሀገራችን ነው አንድ ዓይነት ጫካ ፣ አንድ ዓይነት ሕዝብ ነው ያለን ደግሞም ያሳደገን ጫካ ፣ ያሳደገን ወንዝ ፣ ያሳደገን ውሃ ፣ ያሳደገን አፈር ላይ ነው ተመልሰን የገባነው የማናውቀው ቋንቋ ላይ ፣ የማናውቀው ሀገር ላይ ፣ የማናውቀው አየር ላይ እኮ መጥተን ለምደን እየኖርን አይደለም እንዴ የነበርነው በምዕራቡ ዓለም ? የሚገርመው እኮ ያ ነው የምናውቀው ሀገራችንማ እንዴት ? የምናውቀው ሕዝባችን ያሳደገን እኮ ነው እንጨት እኮ ሰብረንበት የኖርነው ነው ይሄ አያስገርመኝም ( ይበል አሜን ብያለው ከጸሐፊው ) ቀጥለውም እንዲህ አሉ እንደውም እኔ ሕሊናዬ ያረፈው እዚያ ተመድቤ ስኖር ነው ምቾትም ቢሆን እኮ ከዚያ የበለጠ ምቾት አይኖርም ምክንያቱም የጠፋ ሰው ተመልሶ የእግዚአብሔር ልጅ ሲሆን ማየት በእውነት ትልቅ ነገር ነው ይህን ከማየት በላይ ለእኔ ምንም ደስታ የለም ብለዋል ይህ እንግዲህ ሐዋርያዊ የነ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ጉዞና ቀጣይነትም ኖሮት ለወንጌል ሥራ ወደፊት የተራመደ በ14ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ተነስቶ ያለ የነ አባ እስጢፋኖስ ንቅናቄ ብዬዋለሁ በዚህ አጋጣሚ ለብፁዕ አባት አቡነ ፊልጶስ እድሜና ጤናን እመኝላቸዋለሁ መልዕክቴን አልጨረስኩም የሚቀጥለውን የብፁዕነታቸውን ሃሳብ በክፍል ሁለት ትምህርቴ ላይ አቀርበዋለሁ አስተውላችሁ አንብቡት ቪዲዮውንም ስሙት ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 3 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 3 ) የቤተክርስቲያን ሥልጣን የክርስቶስ እንጂ የነቢያት ወይም የፓስተሮች አይደለምና በማናለብኝነት የክርስቶስ የሆነችን ቤተክርስቲያን የኔ ሲሉ የራሳቸው እና የቢጤዎቻቸው ሊያደርጉ የሚሯሯጡ የዘመናችን የነቢያቱ ፣ የፓስተሮቹ……. እሩጫና የኲራቱ ጒዞ እስከ መቼ ? ( ቊጥር 3 ) ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ ጓዛቸውን ጠቅልለው የገቡና ለወንጌሉ ሥራ ቆርጠው የዘመቱ ደገኛው ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የወንጌል ዘማች ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለሰሚዎቻቸው ያስተላለፉትን አንኳር የሆነውን አስተማሪ መልዕክት በአጭሩ ቀንጨብ አድርጌ እነሆ ብያለሁ እና ተከታተሉ ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? በሚለው በክፍል ስድስት ቊጥር ሦስት ትምህርታችን ላይ በጥምረት አያይዘን የምናነሳቸው ዓበይት ጉዳዮች ከዚህ እንደሚከተሉት ናቸው ትምህርታችንን ጠቅለል አድርገን በአጭሩ ስንመለከተው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመኑ ከሐዋርያቱ ይልቅ ፈጥኖ መልስ በመስጠት ለሚታወቀው ለጴጥሮስ የሰጠው መልስ ነበረ በዚህ የክርስቶስ ለቀረበ የማን ትሉኛላችሁ ጥያቄ ጴጥሮስ አንታማ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ሲል አስደናቂ መልስ ሰጠ በዚህን ጊዜ ነው ጌታችን የዮና ልጅ ስምኦን ሆይ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ እኔም እልሃለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ያለው እናንተ ምዕራፉን አውጥታችሁ የተጻፈበትን ክፍል ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 13 _ 20 የተወደዳችሁ ወገኖች እንግዲህ ይህንን የመጽሐፍቅዱስ ክፍል በማስተዋል ስናነበው ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን የራሱ አድርጎ ያያትና የቆጠራትም በመሆኑ ቤተክርስቲያኔ ብሎአታል ስለዚህ ቤተክርስቲያን የእርሱና የእርሱ ብቻ ስለሆነች እርሱም በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ስላለ በራሱ ቤተክርስቲያን ላይ ዋናው ሠራተኛ እርሱ ራሱ ነው እኛ ባሮቹ ግን ልዩ ልዩ ዓይነት የአገልግሎት ስም ቢኖረንና ስማችንም በሰዎች ዘንድ ሳይቀር ገዝፎና ከብሮ ቢጠራም ቤተክርስቲያን ግን አንዴ የእርሱና ለእርሱ ብቻ ስለሆለች የእኛ አይደለችም የእኛም ልትሆን አትችልም የእኛ የምንለው ምንአልባትም እግዚአብሔር ቤትን ካልሰራ ሠራተኛ በከንቱ ይተጋል ይላልና እግዚአብሔር በቸርነቱ የሠራልን ዞረንና አገልግለን ገብተን የምናርፍበት ቤት ሊሆን ይችላል መዝሙር 126 ( 127 ) ፥ 1 ፤ 2ኛ ሳሙኤል 7 ፥ 11 _ 18 ከዚያ ውጪ ግን የእኛ ያልሆነችዋን ቤተክርስቲያን የእኛ ልናደርግ በገዛ አዕምሮአችን ሰንፈን ከሰዎች ጋር በተጋጨንበት ፣ ከሌሎች አገልጋይ ባሮችም ጋር በተማታንበት ፣ ልንበላ ፣ ልንጠጣ ልንሰክርም በጀመርንበት ነገር ሁሉ አሁኑኑ ፈጥነን ንስሐ ልንገባ የበደልናቸውንም ሰዎች እግራቸው ላይ ወድቀን ይቅርታ ልንጠይቅ ይገባል እላለሁኝ አለበለዚያ ግን በፍጻሜው ከአምላካችን ዘንድ የሚመጣብን ቅጣት የከፋ ይሆናል የሉቃስ ወንጌል 12 ፥ 41 _ 48 ነገር ግን ከዚህ ይልቅ እምቢ አሻፈረኝ ስንል ቤተክርስቲያንን የራሳችን ልናደርጋት ብንሞክር ስንላላጥ እንኖራታለን እንጂ በምንም መልኩ ቤተክርስቲያን የእኛ ልትሆን አትችልም ደግሞም ሊቆይ ይችል ይሆናል እንጂ በጊዜ ውስጥ እግዚአብሔር ከእጃችን ወስዶ ሃላፊነታቸውን ለተገነዘቡና የቤተክርስቲያንን ማንነትም ሆነ የራሳቸውን ማንነት በውል አውቀው የማልጠቅም ባርያ ነኝ ሲሉ በትሕትና ለሚያገለግሉ ባሮች በባላደራነት ይሰጣል የሉቃስ ወንጌል 17 ፥ 10 ቤተክርስቲያን ግን ለሁልጊዜም እስከ ዘላለም የክርስቶስ ነች ኤፌሶን 1 ፥ 22 እና 23 ፣ ራዕይ 11 ፥ 15 ውድ ወገኖቼ ሆይ እንግዲህ ይህንን የቃሉን እውነት እንድናገር ግድ ያለኝ ከለቀኩት ቪዲዮ ተነስቼ ነው ትምህርቱም እንዲህ በማለት የሚናገር ነው በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ነቢያት የቤተክርስቲያን መሪዎች ነበሩ ይህ ማለት የሐዲስ ኪዳን ነቢያት በአዲሱ የኪዳን ሥርዓት መካከል የቤተክርስቲያን ጒበኞችና አቅጣጫንም ጠቋሚዎች ስለሆኑ የተለዩ መሪዎች ናቸው ኤፌሶን 4 ፥ 11 እንደገናም መጽሐፍቅዱሳችን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል ብሎናልና ቤተክርስቲያን የተገነባችው በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ነው ኤፌሶን 2 ፥ 20 ይህ ማለት ግን መጽሐፍቅዱሳችን አሁንም ቤተክርስቲያን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታነጸች አለን እንጂ ሐዋርያትና ነቢያት በቤተክርስቲያን ላይ ተመሠረቱ አላለንም ከዚህ የተነሣ ቤተክርስቲያን ለጥቂት ሕዝቦች ፍላጎትና ስኬት ሲባል ለሐዋርያትና ለነቢያት ፣ ለፓስተሮች ሥልጣን የበላይነት የተሰጠች አይደለችም እንደገናም ቤተክርስቲያን የነቢያቱም ሆነ የሐዋርያቱ እንዲሁም የመጋቢዎች ስልጣን አይደለችም ቤተክርስቲያን የክርስቶስ ሥልጣን ናት ባለ ሥልጣኗና አዛዥዋ አስተዳዳሪዋም ክርስቶስ ነው ቤተክርስቲያን ግን ራስ ከሆናት ከክርስቶስ ሥልጣን የተነሳ ለእነዚህ አገልጋዮች እውቅና እየሰጠች እንዲያገለግሉ ታደርጋለች ይህንን እውነታ ባለማወቅና አውቆም የሕይወትን ለውጥ ባለማግኘት ነው እንግዲህ ዛሬ ላይ የምናየውን ትርምስ እስካሁን የምናየው የተወደዳችሁ ወገኖች ፦ ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ በማለት የብፁዕ አባታችን አቡነ ፊልጶስን ምስክርነት በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ካሉ ነቢያትና ፓስተሮች ጋር አያይዤ ማቅረብ የፈለኩት እንግዲህ ከዚህ የተነሳ ነው ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ መልዕክታቸው በዩቲዩብ ስለተለቀቀ አቡነ ፊልጶስ ብላችሁ በመጻፍ ዩቲዩብ ውስጥ ገብታችሁ ምስክርነታቸውን ማዳመጥ ትችላላችሁ ታድያ እኚህ አባት በጠያቂያቸው በሊቀ ማዕምራን ዓባይ አማካኝነት ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ ወደ ጵጵስና ማዕረግ ከመምጣታቸው በፊት በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ብዙ ጊዜያቸውን ተቀምጠው በትምህርት ዓለም ያሳለፉ በመሆናቸው የሊቀ ጵጵስናቸውን ማዕረግ እንደተቀበሉ ለአገልግሎት የተመደቡት ጅንካ ነበርና ይህንን የሥራ ዝውውር በአሜንታ ነበር ተቀብለው ጉዞአቸውን ወደ ጂንካ ያደረጉት ታድያ ጠያቂው ሊቀ ማዕምራን ከአሜሪካ ወደ ጂንካ ሄደው ሊያገለግሉ የወሰኑበትን ጉዳይ ሊያውቅ ብሎ የጠየቀውን ጥያቄ ብፁዕነታቸው ሲመልሱ መልሳቸው ትሕትናንና መንፈሳዊነትን አዋቂነትንም ጭምር የተላበሰ በመሆኑ እጅግ ማራኪ ነበር ብፁዕነታቸው እንዲ ሲሉ ዛሬ ላይ በፓስተሮችና ነቢያቶቻችን ጭምር እግራችን እስኪነቃ ድረስ ብንፈልግ የማናገኘውን ነገር ፍንትው አድርጎ በመግለጽ መልሳቸውን አዥጎደጎዱት ከዚህም ሌላ ማን ያርዳ የነበር ማን ይናገር የቀበር እንደሚባለው እኚህ አባት አሁን ላይ እየኖሩ ያሉትን የጂንካን ሕይወት ከአሜሪካውና ከአውሮፓው ሕይወት ጋር ጎን ለጎን በማስተያየት በውስጣቸው አላባራ ብሎ እየነደደ ያለውን እውነታ ከተጻፈልን ቃል ጋር እያያያዙ አቀጣጠሉት እኔም ደገኛው ሐዋርያ እንዲህ ነው ይበል ብዬ ማስታወሻ ደብተሬንና ብዕሬን ይዤ ቀረብኩ እርሳቸውም ነገራቸውን በመቀጠል ወደ ተረሱት ወደተጣሉት መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ መጥቷል እኔም እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በእርሱ ሳይገባኝ እንዲገባኝ አድርጎ በአባቶች ወንበር ላይ እንድቀመጥ ካደረገበት ጀምሮ መንገዴን ወደ ደቡብ ኦሞ አድርጌያለሁ ብዙ ስለ ሀገሩ የተነገረኝ ነገር ነበረ እንዴት ይኖሩ ይሆን ?ተብዬም በስልክ ሳይቀር ብዙ ተወርቶልኛል ተነግሮኛልም እንግዲህ ስላልገባንና ስላላወቅን ነው እንጂ መቼም ደቡብ ኦሞ ሀገራችን ነው አንድ ዓይነት ጫካ ፣ አንድ ዓይነት ሕዝብ ነው ያለን ደግሞም ያሳደገን ጫካ ፣ ያሳደገን ወንዝ ፣ ያሳደገን ውሃ ፣ ያሳደገን አፈር ላይ ነው ተመልሰን የገባነው የማናውቀው ቋንቋ ላይ ፣ የማናውቀው ሀገር ላይ ፣ የማናውቀው አየር ላይ እኮ መጥተን ለምደን እየኖርን አይደለም እንዴ የነበርነው በምዕራቡ ዓለም ? የሚገርመው እኮ ያ ነው የምናውቀው ሀገራችንማ እንዴት ? የምናውቀው ሕዝባችን ያሳደገን እኮ ነው እንጨት እኮ ሰብረንበት የኖርነው ነው ይሄ አያስገርመኝም ( ይበል አሜን ብያለው ከጸሐፊው ) ቀጥለውም እንዲህ አሉ እንደውም እኔ ሕሊናዬ ያረፈው እዚያ ተመድቤ ስኖር ነው ምቾትም ቢሆን እኮ ከዚያ የበለጠ ምቾት አይኖርም ምክንያቱም የጠፋ ሰው ተመልሶ የእግዚአብሔር ልጅ ሲሆን ማየት በእውነት ትልቅ ነገር ነው ይህን ከማየት በላይ ለእኔ ምንም ደስታ የለም ብለዋል ይህ እንግዲህ ሐዋርያዊ የነ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ጉዞና ቀጣይነትም ኖሮት ለወንጌል ሥራ ወደፊት የተራመደ በ14ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ተነስቶ ያለ የነ አባ እስጢፋኖስ ንቅናቄ ብዬዋለሁ በዚህ አጋጣሚ ለብፁዕ አባት አቡነ ፊልጶስ እድሜና ጤናን እመኝላቸዋለሁ መልዕክቴን አልጨረስኩም የሚቀጥለውን የብፁዕነታቸውን ሃሳብ በክፍል ሁለት ትምህርቴ ላይ አቀርበዋለሁ አስተውላችሁ አንብቡት ቪዲዮውንም ስሙት ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 3 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 3 ) የቤተክርስቲያን ሥልጣን የክርስቶስ እንጂ የነቢያት ወይም የፓስተሮች አይደለምና በማናለብኝነት የክርስቶስ የሆነችን ቤተክርስቲያን የኔ ሲሉ የራሳቸው እና የቢጤዎቻቸው ሊያደርጉ የሚሯሯጡ የዘመናችን የነቢያቱ ፣ የፓስተሮቹ……. እሩጫና የኲራቱ ጒዞ እስከ መቼ ? ( ቊጥር 3 ) ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ ጓዛቸውን ጠቅልለው የገቡና ለወንጌሉ ሥራ ቆርጠው የዘመቱ ደገኛው ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የወንጌል ዘማች ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለሰሚዎቻቸው ያስተላለፉትን አንኳር የሆነውን አስተማሪ መልዕክት በአጭሩ ቀንጨብ አድርጌ እነሆ ብያለሁ እና ተከታተሉ ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? በሚለው በክፍል ስድስት ቊጥር ሦስት ትምህርታችን ላይ በጥምረት አያይዘን የምናነሳቸው ዓበይት ጉዳዮች ከዚህ እንደሚከተሉት ናቸው ትምህርታችንን ጠቅለል አድርገን በአጭሩ ስንመለከተው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመኑ ከሐዋርያቱ ይልቅ ፈጥኖ መልስ በመስጠት ለሚታወቀው ለጴጥሮስ የሰጠው መልስ ነበረ በዚህ የክርስቶስ ለቀረበ የማን ትሉኛላችሁ ጥያቄ ጴጥሮስ አንታማ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ሲል አስደናቂ መልስ ሰጠ በዚህን ጊዜ ነው ጌታችን የዮና ልጅ ስምኦን ሆይ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ እኔም እልሃለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ያለው እናንተ ምዕራፉን አውጥታችሁ የተጻፈበትን ክፍል ሙሉውን ማንበብ ትችላላችሁ የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 13 _ 20 የተወደዳችሁ ወገኖች እንግዲህ ይህንን የመጽሐፍቅዱስ ክፍል በማስተዋል ስናነበው ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን የራሱ አድርጎ ያያትና የቆጠራትም በመሆኑ ቤተክርስቲያኔ ብሎአታል ስለዚህ ቤተክርስቲያን የእርሱና የእርሱ ብቻ ስለሆነች እርሱም በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሉአትም ስላለ በራሱ ቤተክርስቲያን ላይ ዋናው ሠራተኛ እርሱ ራሱ ነው እኛ ባሮቹ ግን ልዩ ልዩ ዓይነት የአገልግሎት ስም ቢኖረንና ስማችንም በሰዎች ዘንድ ሳይቀር ገዝፎና ከብሮ ቢጠራም ቤተክርስቲያን ግን አንዴ የእርሱና ለእርሱ ብቻ ስለሆለች የእኛ አይደለችም የእኛም ልትሆን አትችልም የእኛ የምንለው ምንአልባትም እግዚአብሔር ቤትን ካልሰራ ሠራተኛ በከንቱ ይተጋል ይላልና እግዚአብሔር በቸርነቱ የሠራልን ዞረንና አገልግለን ገብተን የምናርፍበት ቤት ሊሆን ይችላል መዝሙር 126 ( 127 ) ፥ 1 ፤ 2ኛ ሳሙኤል 7 ፥ 11 _ 18 ከዚያ ውጪ ግን የእኛ ያልሆነችዋን ቤተክርስቲያን የእኛ ልናደርግ በገዛ አዕምሮአችን ሰንፈን ከሰዎች ጋር በተጋጨንበት ፣ ከሌሎች አገልጋይ ባሮችም ጋር በተማታንበት ፣ ልንበላ ፣ ልንጠጣ ልንሰክርም በጀመርንበት ነገር ሁሉ አሁኑኑ ፈጥነን ንስሐ ልንገባ የበደልናቸውንም ሰዎች እግራቸው ላይ ወድቀን ይቅርታ ልንጠይቅ ይገባል እላለሁኝ አለበለዚያ ግን በፍጻሜው ከአምላካችን ዘንድ የሚመጣብን ቅጣት የከፋ ይሆናል የሉቃስ ወንጌል 12 ፥ 41 _ 48 ነገር ግን ከዚህ ይልቅ እምቢ አሻፈረኝ ስንል ቤተክርስቲያንን የራሳችን ልናደርጋት ብንሞክር ስንላላጥ እንኖራታለን እንጂ በምንም መልኩ ቤተክርስቲያን የእኛ ልትሆን አትችልም ደግሞም ሊቆይ ይችል ይሆናል እንጂ በጊዜ ውስጥ እግዚአብሔር ከእጃችን ወስዶ ሃላፊነታቸውን ለተገነዘቡና የቤተክርስቲያንን ማንነትም ሆነ የራሳቸውን ማንነት በውል አውቀው የማልጠቅም ባርያ ነኝ ሲሉ በትሕትና ለሚያገለግሉ ባሮች በባላደራነት ይሰጣል የሉቃስ ወንጌል 17 ፥ 10 ቤተክርስቲያን ግን ለሁልጊዜም እስከ ዘላለም የክርስቶስ ነች ኤፌሶን 1 ፥ 22 እና 23 ፣ ራዕይ 11 ፥ 15 ውድ ወገኖቼ ሆይ እንግዲህ ይህንን የቃሉን እውነት እንድናገር ግድ ያለኝ ከለቀኩት ቪዲዮ ተነስቼ ነው ትምህርቱም እንዲህ በማለት የሚናገር ነው በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ነቢያት የቤተክርስቲያን መሪዎች ነበሩ ይህ ማለት የሐዲስ ኪዳን ነቢያት በአዲሱ የኪዳን ሥርዓት መካከል የቤተክርስቲያን ጒበኞችና አቅጣጫንም ጠቋሚዎች ስለሆኑ የተለዩ መሪዎች ናቸው ኤፌሶን 4 ፥ 11 እንደገናም መጽሐፍቅዱሳችን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል ብሎናልና ቤተክርስቲያን የተገነባችው በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ነው ኤፌሶን 2 ፥ 20 ይህ ማለት ግን መጽሐፍቅዱሳችን አሁንም ቤተክርስቲያን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታነጸች አለን እንጂ ሐዋርያትና ነቢያት በቤተክርስቲያን ላይ ተመሠረቱ አላለንም ከዚህ የተነሣ ቤተክርስቲያን ለጥቂት ሕዝቦች ፍላጎትና ስኬት ሲባል ለሐዋርያትና ለነቢያት ፣ ለፓስተሮች ሥልጣን የበላይነት የተሰጠች አይደለችም እንደገናም ቤተክርስቲያን የነቢያቱም ሆነ የሐዋርያቱ እንዲሁም የመጋቢዎች ስልጣን አይደለችም ቤተክርስቲያን የክርስቶስ ሥልጣን ናት ባለ ሥልጣኗና አዛዥዋ አስተዳዳሪዋም ክርስቶስ ነው ቤተክርስቲያን ግን ራስ ከሆናት ከክርስቶስ ሥልጣን የተነሳ ለእነዚህ አገልጋዮች እውቅና እየሰጠች እንዲያገለግሉ ታደርጋለች ይህንን እውነታ ባለማወቅና አውቆም የሕይወትን ለውጥ ባለማግኘት ነው እንግዲህ ዛሬ ላይ የምናየውን ትርምስ እስካሁን የምናየው የተወደዳችሁ ወገኖች ፦ ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ በማለት የብፁዕ አባታችን አቡነ ፊልጶስን ምስክርነት በወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ካሉ ነቢያትና ፓስተሮች ጋር አያይዤ ማቅረብ የፈለኩት እንግዲህ ከዚህ የተነሳ ነው ከአሜሪካ ____________________ ጂንካ መልዕክታቸው በዩቲዩብ ስለተለቀቀ አቡነ ፊልጶስ ብላችሁ በመጻፍ ዩቲዩብ ውስጥ ገብታችሁ ምስክርነታቸውን ማዳመጥ ትችላላችሁ ታድያ እኚህ አባት በጠያቂያቸው በሊቀ ማዕምራን ዓባይ አማካኝነት ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ ወደ ጵጵስና ማዕረግ ከመምጣታቸው በፊት በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ብዙ ጊዜያቸውን ተቀምጠው በትምህርት ዓለም ያሳለፉ በመሆናቸው የሊቀ ጵጵስናቸውን ማዕረግ እንደተቀበሉ ለአገልግሎት የተመደቡት ጅንካ ነበርና ይህንን የሥራ ዝውውር በአሜንታ ነበር ተቀብለው ጉዞአቸውን ወደ ጂንካ ያደረጉት ታድያ ጠያቂው ሊቀ ማዕምራን ከአሜሪካ ወደ ጂንካ ሄደው ሊያገለግሉ የወሰኑበትን ጉዳይ ሊያውቅ ብሎ የጠየቀውን ጥያቄ ብፁዕነታቸው ሲመልሱ መልሳቸው ትሕትናንና መንፈሳዊነትን አዋቂነትንም ጭምር የተላበሰ በመሆኑ እጅግ ማራኪ ነበር ብፁዕነታቸው እንዲ ሲሉ ዛሬ ላይ በፓስተሮችና ነቢያቶቻችን ጭምር እግራችን እስኪነቃ ድረስ ብንፈልግ የማናገኘውን ነገር ፍንትው አድርጎ በመግለጽ መልሳቸውን አዥጎደጎዱት ከዚህም ሌላ ማን ያርዳ የነበር ማን ይናገር የቀበር እንደሚባለው እኚህ አባት አሁን ላይ እየኖሩ ያሉትን የጂንካን ሕይወት ከአሜሪካውና ከአውሮፓው ሕይወት ጋር ጎን ለጎን በማስተያየት በውስጣቸው አላባራ ብሎ እየነደደ ያለውን እውነታ ከተጻፈልን ቃል ጋር እያያያዙ አቀጣጠሉት እኔም ደገኛው ሐዋርያ እንዲህ ነው ይበል ብዬ ማስታወሻ ደብተሬንና ብዕሬን ይዤ ቀረብኩ እርሳቸውም ነገራቸውን በመቀጠል ወደ ተረሱት ወደተጣሉት መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ መጥቷል እኔም እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በእርሱ ሳይገባኝ እንዲገባኝ አድርጎ በአባቶች ወንበር ላይ እንድቀመጥ ካደረገበት ጀምሮ መንገዴን ወደ ደቡብ ኦሞ አድርጌያለሁ ብዙ ስለ ሀገሩ የተነገረኝ ነገር ነበረ እንዴት ይኖሩ ይሆን ?ተብዬም በስልክ ሳይቀር ብዙ ተወርቶልኛል ተነግሮኛልም እንግዲህ ስላልገባንና ስላላወቅን ነው እንጂ መቼም ደቡብ ኦሞ ሀገራችን ነው አንድ ዓይነት ጫካ ፣ አንድ ዓይነት ሕዝብ ነው ያለን ደግሞም ያሳደገን ጫካ ፣ ያሳደገን ወንዝ ፣ ያሳደገን ውሃ ፣ ያሳደገን አፈር ላይ ነው ተመልሰን የገባነው የማናውቀው ቋንቋ ላይ ፣ የማናውቀው ሀገር ላይ ፣ የማናውቀው አየር ላይ እኮ መጥተን ለምደን እየኖርን አይደለም እንዴ የነበርነው በምዕራቡ ዓለም ? የሚገርመው እኮ ያ ነው የምናውቀው ሀገራችንማ እንዴት ? የምናውቀው ሕዝባችን ያሳደገን እኮ ነው እንጨት እኮ ሰብረንበት የኖርነው ነው ይሄ አያስገርመኝም ( ይበል አሜን ብያለው ከጸሐፊው ) ቀጥለውም እንዲህ አሉ እንደውም እኔ ሕሊናዬ ያረፈው እዚያ ተመድቤ ስኖር ነው ምቾትም ቢሆን እኮ ከዚያ የበለጠ ምቾት አይኖርም ምክንያቱም የጠፋ ሰው ተመልሶ የእግዚአብሔር ልጅ ሲሆን ማየት በእውነት ትልቅ ነገር ነው ይህን ከማየት በላይ ለእኔ ምንም ደስታ የለም ብለዋል ይህ እንግዲህ ሐዋርያዊ የነ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ጉዞና ቀጣይነትም ኖሮት ለወንጌል ሥራ ወደፊት የተራመደ በ14ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ ተነስቶ ያለ የነ አባ እስጢፋኖስ ንቅናቄ ብዬዋለሁ በዚህ አጋጣሚ ለብፁዕ አባት አቡነ ፊልጶስ እድሜና ጤናን እመኝላቸዋለሁ መልዕክቴን አልጨረስኩም የሚቀጥለውን የብፁዕነታቸውን ሃሳብ በክፍል ሁለት ትምህርቴ ላይ አቀርበዋለሁ አስተውላችሁ አንብቡት ቪዲዮውንም ስሙት ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን

Thursday 18 January 2018

የእንጨቱ መስቀል ከአምላክ ጋር በእኩል ዓይን ታይቶ የተፈለገበትና የተመለከበት አሳፋሪ ታሪክ እና የደብረ ታቦር የ...የእንጨቱ መስቀል ከአምላክ ጋር በእኩል ዓይን ታይቶ የተፈለገበትና የተመለከበት አሳፋሪ ታሪክ እና የደብረ ታቦር የበዓል ትረካ አኮ ከመ ይትረዓይ አላ ከመ ይትሐለይ ውእቱ ዝንቱ መስቀል የሚታሰብ እንጂ የሚታይ መስቀል ለእኛ የለንም ( ምንጭ ትምህርተ ኅቡዓት መጽሐፍ ) እሰግድ ለአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐተ ስግደተ …………. እሰግድ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ እሰግድ ለመስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስቅዱስ ስብሐት ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ስብሐት ለመስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ለአብ ለወልድ ለመንፈስቅዱስ አንዲት ስግደት እሰግዳለሁ አምላክን ለወለደች ለድንግል ማርያም እሰግዳለሁ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እሰግዳለሁ ለአብ ምስጋና ለወልድ ምስጋና ለመንፈስቅዱስ ምስጋና ይገባል አምላክን ለወለደች ለድንግል ማርያም ምስጋና ይገባል ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምስጋና ይገባል ለእነዚህ ሁሉ በቅደም ተከተል ለተቀመጡት ምስጋናና ስግደቶች የዘወትር ጸሎት የተባለው መጽሐፍ ፦ ይደልዎሙ ለአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ ይደልዋ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ይደልዎ ለመስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲል ሕዝባዊ መልስ ይሰጣል ሕዝቡ ለዚሁ ስግደትና ምስጋና እንዲሁ ሲል መልስ ሰጥቶአልና ወደ አማርኛ ስተረጉመው ይደልዎሙ ፣ ይደልዋ ፣ ይደልዎ የሚሉት የግዕዙ ቃላት ለአብ ለወልድ ለመንፈስቅዱስ ፣ ለወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የተቀጸሉ ናቸውና ለአብ ለወልድ ለመንፈስቅዱስ ስግደትም ሆነ ምስጋና ይገባቸዋል አምላክን ለወለደች ለድንግል ማርያም ይገባታል ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ይገባዋል እያለን ነው ያለው ( ምንጭ የቤተክርስቲያኒቱ መጽሐፍ ጸሎት ዘዘወትርን ይመልከቱ ) ታድያ የጸሎት መጽሐፉ ይህን ካለ እኛስ ይደልዎሙ፦ ይገባቸዋል ፤ ይደልዎ ፦ ይገባዋል ፤ ይደልዋ ፦ ይገባታል ስንል ማንን አምላክና ጌታ ብለን እርሱን እናምልክ ? ለማንስ እንስገድ ? ደግሞስ የሚታሰብ እንጂ የሚታይ መስቀል ከሌለን ከሥላሴ እኩል ቦታ ተሰጥቶአቸውና ሊመለኩ ተወስነው የቀረቡ እነዚሁ ግዙፋን መስቀሎች እንዴት ወደ መታየት መጥተው ሊመለኩ ጊዜ ሆነላቸው ? እንዴትስ ተፈቀደላቸው ? መልሱን ለእናንተ ኢየሱስም መልሶ፦ ለጌታ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአል አለው የሉቃስ ወንጌል 4 : 8 ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክትአይሁኑልህ…………….. ኦሪት ዘጸአት 20 : 3 - 6 ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክትአይሁኑልህ……………… ኦሪት ዘዳግም 5 : 7 - 10 እኔ እግዚአብሔር ነኝ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም ( ትንቢተ ኢሳይያስ 42 : 8 ) ስለ እኔ፥ ስለ ራሴ አደርገዋለሁ ስሜ ተነቅፎአልና፤ ክብሬንም ለሌላ አልሰጥም ( ትንቢተ ኢሳይያስ 42 : 11 )

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል አስራ ሰባት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ( ቊጥር 2 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል አስራ ሰባት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? የብሉይ ኪዳን ነቢያትን አስመልክቶ የተነገረ ሲሆን በዚህ ውስጥ የነቢያት አገልግሎት እንዴት መሆንና ምን መምሰል አለበት የሚለውን ዋና ዋና ሃሳብ የያዘ ትምህርት ነው ብትችሉ ሼር አድርጉት ደግሞም ተባረኩበት ( ቊጥር 2 )

Thursday 11 January 2018

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ?የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Challenges ) ክፍል ስድስት ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ? ነቢይ ማለት ከእግዚአብሔር የተላከ ማለት ሲሆን መልዕክተኛ እንደመሆኑ መጠን ከዚሁ ከእግዚአብሔር ቃልን ተቀብሎ ለሕዝብ የሚናገር ማለት ነው ( ዘጸአት 7 ፥ 1 እና 2 ፣ ሆሴዕ 12 ፥ 14 ) በነቢይነትም ሆነ በልዩ ልዩ የአገልግሎት ጥሪ ውስጥ ገብተው ማገልገል ለሚፈልጉ የወንጌላውያን አማኞችም ሆነ ለኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን የተላለፈ ትምህርት ( ቊጥር 1 ) የተወደዳችሁ ወገኖች እንግዲህ በቀጥታ ወደ ትምህርቱ ፍሬ ሃሳብ ስንሄድ በዚሁ ቃል መሠረት ትምህርቱ በነቢያቱ ላይ የሚያጠነጥን ይምሰል እንጂ መላክን በተመለከተ የተላኩም ሆኑ ወደፊትም የሚላኩ ነቢያቱ ብቻ ሳይሆኑ የእግዚአብሔርን ቃል ወደሰዎች የሚያመጡ የቃሉ አገልጋዮችም ልዑካን ናቸው ( ሮሜ 10 ፥ 14 _ 17 ) ይሁን እንጂ ታድያ አሁን ላይ በነቢያቱም ሆነ በቃሉ አገልጋዮች በኩል እየተሰጠ ያለ አገልግሎት ቃሉን የተከተለና መልኩን የጠበቀ ካለመሆኑ የተነሳ በእግዚአብሔር ስም እየተተነበየ ያለው ትንቢቱም ሆነ ስብከቱ መታነጽያ መሆኑ ቀርቶ የመድረክ ላይ መደባደብያና ማደባደብያ ፣ ትዳርን ሳይቀር መፍቻና ማፋቻ በአጠቃላይ ቤተሰብን መበተኛና ጓደኛንም ከጓደኛ መለያያ ማለያያም እየሆነ ከመጣ ውሎ አድሮአል ከዚህ የተነሳ ሕዝባችንም ሚዛኑን የጠበቀና መጽሐፍቅዱስን ያማከለ ትንቢትም ሆነ ትክክለኛ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ካለማግኘቱ የተነሳ የመጡትን ትንቢቶችም ሆነ መልዕክቶች ሰምቶ ተጠቃሚ ከሚሆን ይልቅ ለሌላው የሰማና የሚሰማ ሆኖ በመቅረብ ስማልኝማ ፣ ስሚልኝማ ልክ ልኩን ፣ ልክ ልኳን ነገረልኝ እኮ ሴትም ከሆነች አገልጋይዋ ነገረችልኝ እኮ በማለት አብዛኛው ምዕመናችንም ሆነ የቃሉ አገልጋዮችና ነቢያቱም ጭምር በአገልግሎትና በመልዕክተኝነት ስም መስሎ በታየን ፣ ይሆናል ብለን ባመንበትም ነገር ሁሉ ላይ ቊጭታችንን ልንወጣ የልባችንንም ምኞት ልንፈጽም እየተውተረተርን ያለንና እንቅልፋችንን አጥተን የምናድርም ብዙዎች ነን የእግዚአብሔር አገልግሎት ግን መደባደብያና ሌላውንም ማጥቂያ ፣ የግል ጉዳዮቻችንንም ማስፈጸምያ እና ማሟያ አይደለም ውድ ወገኖቼ ሆይ ለዚሁ ሃሳቤ ድጋፍ የሚሆነኝን በነህምያ 6 ፥ 10 _ 14 ላይ ነህምያን፣ ለነህምያም ትንቢት እንዲያመጣ በሰንባላጥና በጦቢያ ተገዝቶ ትንቢት የተናገረውን የሐሰተኛውን ነቢይ የሸማያን ትንቢትም ሆነ ነህምያ የሰጠውን ምላሽ ፣ የወሰደውንም የሕይወት አቋም ከክፍሉ በሰፊው ተመልክተናል ታድያ ይህንን አስመልክቶ የዛሬዎቹ አገልጋዮቻችን ምን ሊሆኑ እንደሚገባ ፣ ለሕዝባችንም የሚሰጡት ትምህርት ምንና እንዴት መሆን እንዳለበት ትምህርቱ ይጠቁማል ቅዱሳን እንግዲህ ጊዜ ወስዳችሁ የተለቀቀውን ቪዲዮ ተከታተሉ እኔም እርግጠኛ በመሆን በዚህ ትምህርት ብዙዎቻችን ተጠቃሚዎች እንደምንሆን አምናለሁ ትምህርቱ ይቀጥላል ተባረኩልኝ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com

ስለ ሕግ በመጽሐፍቅዱስ ተጠቅሰው ስላሉ በዓላትና ኦርቶዶክሳዊ በዓላት አከባበር የተሰጠ በመረጃ የተደገፈ መጽ... ስለ ሕግ በመጽሐፍቅዱስ ተጠቅሰው ስላሉ በዓላትና ኦርቶዶክሳዊ በዓላት አከባበር የተሰጠ በመረጃ የተደገፈ መጽሐፍቅዱሳዊ ትምህርት ( ክፍል አንድ ) ፈጣን ተሃድሶ ለኦርቶዶክስ ተአምረ ማሪያም ከክርስቶስ ለይቶን የኖረ ወንጀለኛ መጽሐፍ እመቤታችን በዓላቶችዋ ሁሉ ሠላሳ ሦስት ( 33 ) ናቸው እነዚህን በዓላቶች እንደ እሁድ ሰንበት አድርገው ይቁጠሩዋቸው። ከዓመት እስከ ዓመት እስከዘ ለዓለም ምንም ስራ አይስሩባቸው፤ ( የተአምረ ማርያም መቅድም ቁ፡32_34 ) መጽሐፈ ሰዓታት ( የሰዓታት መጽሐፍ ) ስለ ምስጋና የተናገረው ትርጉም ፦ የዓለም ሁሉ ቤዛ የሆንሽ ቅድስት ማርያም ሆይ ጣፋጭ በሆነው በስምሽ መታሰብያ ያማረ በሆነው በደምሽ ፍሬም እንደሰታለን ( ኲሎሙ ዘእግዝእትነ ማርያም ከሚባል ክፍል _ ገጽ 105 ) መጽሐፍቅዱሳችን ስለ ቤዛነት የተናገረው እንዲሁ የሰው ልጅም ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም ( የማርቆስ ወንጌል 10 : 45 ) የዘላለምን ቤዛነት አግኝቶ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ እንጂ በፍየሎችና በጥጆች ደም አይደለም ( ዕብራውያን 9 : 12 ) በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ ( ሮሜ 3 : 24 ) መጽሐፍቅዱሳችን ስለ በዓላት የተናገረው እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2 : 16 ስለዚህ ማንን እንስማ ? ማንን እንቀበል ? የትኛውንስ እንመን ?መጽሐፍ ቅዱስን ? ወይንስ ተአምረ ማርያምንና የሰዓታት መጽሐፍን ?መልሱን ለአድማጮች ብለናል ተባረኩ

Tuesday 9 January 2018

የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Cchallenges ) ክፍል አምስት በነቢያት አገልግሎት ዙርያ ( ቁጥር 15 )የተሃድሶ ተግዳሮቶች ( Cchallenges ) ክፍል አምስት በነቢያት አገልግሎት ዙርያ ( ቁጥር 15 ) ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ .............የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዘካርያስ ልጅ ወደ ዮሐንስ በምድረበዳ መጣ የማቴዎስ ወንጌል 3 : 4 ፤ የሉቃስ ወንጌል 3 ፥ 1 _ 6 የዮሐንስ መጥምቁ ሕይወቱ ገዳማዊ ሕይወትን ያመለክታልን ? ዮሐንስ መጥምቁስ ገዳማዊ ሕይወትን ያበረታታልን ? ገዳማዊ ሕይወትን የሚያበረታቱ የገድላትና የድርሳናት ጽሑፎች በእግዚአብሔር ቃል ሲፈተሹ የሚል መሪ ሃሳብ የያዘ ሲሆን ከዚህም ባሻገር ፦—————— ትምህርቱ ከመጽሐፍቅዱስ ሌላ የክርስቶስን ብቸኛ አዳኝነት የሚገልጹ ከመጽሐፍቅዱሳችንም ጋር በተያያዥነት አስረጅ ሆነው የቀረቡ የቤተክርስቲያኒቱ መጻሕፍት በትንታኔና በቤተክርስቲያኒቱ የግዕዝ ቋንቋ ታግዘው የተጠቀሱበት እውነት ይገኝበታል ከዚህም ሌላ አቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ በገድላቸው ላይ እግዚአብሔር የኢትዮጵያን ኃጢአት አሳይቶኝ በባሕር ውስጥ ለመቶ ዓመት ቁልቁል ተዘቅዝቄ ጸለይኩላት ላሉት ሃሳባቸው ዛሬም በኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን በወንጌላውያኑም አብያተክርስቲያናት ያሉ ነቢያትና አገልጋዮች ለታያቸው በደልና ኃጢአት ምላሽ ሊሰጡ ቊልቊል ተዘቅዝቀው ጸለዩ ባንልም ታየኝ ተገለጠልኝ በሚል ሰበብ ብቻ አብዛኛዎቹ ማለት ይቻላል ከአቡዬ ገብረ መንፈስቅዱስ ባልተናነሰ ሁኔታ እየፈጸሙት ስላለው ስሕተት ማስተካከያና እርማት በመስጠት ትምህርቱ ግልጽ የሆነ መጽሐፍቅዱሳዊ ትንታኔና መረጃን ያቀርባል ስለዚህ ቅዱሳን እንዲሁም የእግዚአብሔርን ቃል መማር የምትፈልጉ ወገኖች በሙሉ መልዕክቱን መስማታችሁ ለሕይወታችሁ ወሳኝ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ ተከታተሉ እላለሁኝ ተባረኩ