Tuesday 29 January 2019

የመልዕክት ርዕስ : - ፈርሶ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠዊያ አበጀ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 18 : 30 - 46የመልዕክት ርዕስ : - ፈርሶ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠዊያ አበጀ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 18 : 30 - 46 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን ተባረኩ መልዕክቱ በቪዲዮ ተለቆአል ተከታተሉ በዚህ መልዕክት ውስጥ ግን አስተውለን እንድንረዳው የምፈልገው ጥያቄያችን ፈርሶ የነበረውን መሠዊያ ማበጀት ከሆነ ጊዜ ሊቆይ ይችል ይሆናል እንጂ ማበጀታችን አይቀርም ለእኔ ኤልያስ የፈረሰ መሠውያ ማበጀቱ አይደለም የሚደንቀኝ መሠውያው ከዚህ በፊት በሥራ ላይ እንደነበረና አሁን ደግሞ እንደፈረሰ ማወቁና ለማበጀት መነሳቱ ነው የገረመኝ ስለዚህ ኤልያስ ዝም ብሎ መሠውያ ሊሰራ የተነሳና መሠውያውንም የሰራ አይደለም ከዚህ ጋር በተዛማጅነት ነህምያ 2 : 9 - ፍጻሜ የተጻፈውን እንመልከት ውድ ወገኖቼ ሆይ ብዙ ሰዎች በዚህ ዘመን መሠውያ ብቻ አይደለም ብዙ ነገር ሊሰሩ ተነስተውና ሊደመድሙ አቅቶአቸው አይተናል የሉቃስ ወንጌል 14 : 25 - 33 እንመልከት እንደገናም ብዙ ሰዎች እሄዳለሁ ካለ ጋር ሁሉ ሄደው ሆ ካለ ጋርም ሆ ብለው ተነስተው ጨለማና ጥፋት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሳይቀር የገቡ ብዙዎች ናቸው የዮሐንስ ወንጌል 21 : 1 - 14 ይመልከቱ ታድያ መጽሐፍ ቅዱሳችን የዘሩባቤል እጆች ይህን ቤት መሠረቱ የእርሱም እጆች ይፈጽሙታል እንደሚል በእኛ የተጀመሩ ሥራዎች በእኛው እንዲፈጸሙ በእኛም የጀመረው እግዚአብሔር ጊዜውን ጠብቆ በእኛው ሥራውን እንዲፈጽም እኛም ከእግዚአብሔር ሥራ ጋር ተስማምተን መውጣትና እግዚአብሔርም አድርጉ ያለንን ብቻ ማድረግ እንዳለብን ይሄ መልዕክት በጽኑእ ያስታውሰናል ይመክረናል ( ዘካርያስ 4 : 6 - 10 / ፊልጵስዩስ 1 : 6 / የሉቃስ ወንጌል 17 : 10 ) የተጻፈውን እንመልከት እግዚአብሔር በዚህ የቃል እውነት ይገናኘን ይባርከን ተባረኩ አባ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment