Tuesday 24 July 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል አምስት ) ( ቊ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል አምስት ) ( ቊጥር 1 ) ተፈስሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ ወማዕዶታ ለሔዋን እንተ ይእቲ አፅመ ገቦሁ ትርጉም ፦ የአዳም ፋሲካ የሆንሽ ከጎኑም ለወጣችዋ ለሔዋን መሻገርያዋ የሆንሽ ማርያም ደስ ይበልሽ ( መጽሐፈ ሰዓታት ገጽ 79 ) እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና ስለዚህ በቅንነትና በእውነት ቂጣ በዓልን እናድርግ እንጂ በአሮጌ እርሾ በክፋትና በግፍ እርሾም አይደለም 1ኛ ቆሮንቶስ 5 : 7 እና 8 1ኛ ) ፋሲካ የእግዚአብሔር ነው ወገቦቻችሁን ታጥቃችሁ፥ ጫማችሁን በእግራችሁ፥ በትራችሁንም በእጃችሁ አድርጋችሁ እንዲህ ብሉት፥ ፈጥናችሁም ትበሉታላችሁ፤ እርሱ የእግዚአብሔር ፋሲካ ነው ኦሪት ዘጸአት 12 : 11 ፋሲካ የእግዚአብሔር ነው :: በመሆኑም ማርያምን ፋሲካዬ ሊላት ፣ ፋሲካውም ሊያደርጋት እግዚአብሔር ፕሮግራም አላደረጋትም :: የእግዚአብሔር የፋሲካው ፕሮግራምና ፋሲካው ፣ ፋሲካችን የሆነው ፣ የታረደልንም ክርስቶስ ኢየሱስ ነው :: ይሁን እንጂ ማርያምም የእግዚአብሔር የፋሲካው ፕሮግራም ልሁን ብትልና የአዳምም ሆነ የሰው ልጆች ሁሉ ፋሲካ መሆንዋን ብትናገር የአዳም በደል እርስዋንም ስለሚመለከት የእግዚአብሔር ፕሮግራምም ሆነ የእግዚአብሔር ፋሲካ ልትሆን አትችልም :: ይልቁንም ማርያም የእግዚአብሔር ፋሲካ የሚያስፈልጋት ስለሆነች ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች የባርያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና ስትል ፋሲካዋ ክርስቶስ እንደሆነ ተናገረች ( የሉቃስ ወንጌል 1 ፥ 47 ) :: የተወደዳችሁ ወገኖቼ ፋሲካ የእግዚአብሔር ነው :: በመሆኑም ፋሲካ የእግዚአብሔር መሆኑን አውቀን እዚህ የእግዚአብሔር ፋሲካ ውስጥ ስንገባ እንደ ሙሴ ፋሲካንና ደምን መርጨት በእምነት እናደርጋለን:: ከዚህም ሌላ አምላካችን ስሙ በእኛ ላይ ይጠራል :: እንደገናም በዚህ በእግዚአብሔር ፋሲካ ከፍ ባለ እጅ እንወጣለ :: ለዚህም ነው ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፥ ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም በማለት አምላካችን በራዕይ መጽሐፍ ላይ የነገረን :: ትምህርቱ እንግዲህ እነዚህን ሃሳቦች ሁሉ አካቶ የያዘ ነው በይበልጥ ቪዲዮውን ብትሰሙ ደግሞ ትባረኩበታላችሁ :: ዘመናችሁ ይባረክ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል አምስት ) ( ቊ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል አምስት ) ( ቊጥር 1 ) ተፈስሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ ወማዕዶታ ለሔዋን እንተ ይእቲ አፅመ ገቦሁ ትርጉም ፦ የአዳም ፋሲካ የሆንሽ ከጎኑም ለወጣችዋ ለሔዋን መሻገርያዋ የሆንሽ ማርያም ደስ ይበልሽ ( መጽሐፈ ሰዓታት ገጽ 79 ) እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና ስለዚህ በቅንነትና በእውነት ቂጣ በዓልን እናድርግ እንጂ በአሮጌ እርሾ በክፋትና በግፍ እርሾም አይደለም 1ኛ ቆሮንቶስ 5 : 7 እና 8 1ኛ ) ፋሲካ የእግዚአብሔር ነው ወገቦቻችሁን ታጥቃችሁ፥ ጫማችሁን በእግራችሁ፥ በትራችሁንም በእጃችሁ አድርጋችሁ እንዲህ ብሉት፥ ፈጥናችሁም ትበሉታላችሁ፤ እርሱ የእግዚአብሔር ፋሲካ ነው ኦሪት ዘጸአት 12 : 11 ፋሲካ የእግዚአብሔር ነው :: በመሆኑም ማርያምን ፋሲካዬ ሊላት ፣ ፋሲካውም ሊያደርጋት እግዚአብሔር ፕሮግራም አላደረጋትም :: የእግዚአብሔር የፋሲካው ፕሮግራምና ፋሲካው ፣ ፋሲካችን የሆነው ፣ የታረደልንም ክርስቶስ ኢየሱስ ነው :: ይሁን እንጂ ማርያምም የእግዚአብሔር የፋሲካው ፕሮግራም ልሁን ብትልና የአዳምም ሆነ የሰው ልጆች ሁሉ ፋሲካ መሆንዋን ብትናገር የአዳም በደል እርስዋንም ስለሚመለከት የእግዚአብሔር ፕሮግራምም ሆነ የእግዚአብሔር ፋሲካ ልትሆን አትችልም :: ይልቁንም ማርያም የእግዚአብሔር ፋሲካ የሚያስፈልጋት ስለሆነች ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች የባርያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና ስትል ፋሲካዋ ክርስቶስ እንደሆነ ተናገረች ( የሉቃስ ወንጌል 1 ፥ 47 ) :: የተወደዳችሁ ወገኖቼ ፋሲካ የእግዚአብሔር ነው :: በመሆኑም ፋሲካ የእግዚአብሔር መሆኑን አውቀን እዚህ የእግዚአብሔር ፋሲካ ውስጥ ስንገባ እንደ ሙሴ ፋሲካንና ደምን መርጨት በእምነት እናደርጋለን:: ከዚህም ሌላ አምላካችን ስሙ በእኛ ላይ ይጠራል :: እንደገናም በዚህ በእግዚአብሔር ፋሲካ ከፍ ባለ እጅ እንወጣለ :: ለዚህም ነው ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፥ ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም በማለት አምላካችን በራዕይ መጽሐፍ ላይ የነገረን :: ትምህርቱ እንግዲህ እነዚህን ሃሳቦች ሁሉ አካቶ የያዘ ነው በይበልጥ ቪዲዮውን ብትሰሙ ደግሞ ትባረኩበታላችሁ :: ዘመናችሁ ይባረክ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry

Friday 20 July 2018

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ (...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 15 ) ክፍል አራት አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን ( 1ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 15 ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ተስፋን በተመለከተ ይህ የመጨረሻና የማጠቃለያ ትምህርት ነው ከላይ በመግቢያ ጥቅሴ ላይ እንዳነሳሁት በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ ይለናልና በእኛ በእያንዳንዳችን ያለ ተስፋ ከተማርነው ትምህርት አንጻር ክርስቶስ እንጂ የቅዳሴ ማርያም ጸሐፊ እንደተናገረው ማርያም አይደለችምና ተስፋችን ስለሆነው ክርስቶስ ለሚጠይቁን ሁሉ መልስ ልንሰጥ ዘወትር የተዘጋጀን ልንሆን ይገባል በመሆኑም በዚህ ትምህርት ውስጥ የተካተቱ ሃሳቦች አሉ 1ኛ ) የመምጣቱን ተስፋ አስመልክቶ በእኛ ስላለው ተስፋ ምክንያት ጥያቄ ከሚያነሱ ሰዎች መካከል ጥቂቶቹን በዝርዝር የምንመለከታቸው ይሆናል ሀ ) የመምጣቱ ተስፋ ወዴት ነው ? የሚሉና አባቶች ከሞቱበት ጊዜ ከፍጥረት መጀመርያ ይዞ ሁሉ እንዳለ ይኖራል የሚሉ ፣ እንደራሳቸው ምኞት የሚመላለሱ ዘባቾች በመዘበትም የሚመጡ ናቸው ( 2ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 4 ) ለ ) በጌታ የመምጣቱ ጉዳይም ጌታ ከመምጣት የሚዘገይ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ ( 2ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 9 ፣ ዕብራውያን 10 ፥ 37 _ 39 ) ሐ ) ጌታን በመጠበቅ ደግሞ የታከቱ ሰዎች አሉ ( 2ኛ ጴጥሮስ 3 _ 11 _ 15 ፣ የማቴዎስ ወንጌል 25 በሙሉ ፣ የሉቃስ ወንጌል 12 ፥ 35 _ 48 ) ታድያ በእኛ ስላለ ተስፋ ምክንያትን የሚጠይቁ ሰዎች እነዚህንና እነዚህን የመሣሠሉ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም ስላሉ እነርሱ ለሚያነሱት ጥያቄዎች ሁሉ በእኛ በኩል መልስ ልንሰጥ ዘወትር የተዘጋጀን መሆን አለብን 2ኛ ) ቃሉ እንደነገረን በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን ይላልና በእኛ ያለው ተስፋ ምንድነው ? ብለን ስንጠይቅ ደግሞ ትምህርቱ በክለሣ መልክም ቢሆን በእኛ ያለውን ተስፋ በዝርዝርና በቅደም ተከተል ያቀርባል ሀ ) በእኛ ያለው ተስፋ ከዘላለም ዘመናት በፊት የተሰጠ ተስፋ ነው ( ቲቶ 1 ፥ 1 እና 2 ) ለ ) የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋ ነው ( 2ኛ ጴጥሮስ 1 ፥ 4 ) ሐ ) ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት የሚሻል ተስፋ ነው ( ዕብራውያን 7 ፥ 18 እና 19 ) መ ) ለአባቶች የተሰጠ ተስፋና በመጨረሻም እግዚአብሔር ኢየሱስን አስነስቶ ለእኛና ለልጆቻቸው የፈጸመው ተስፋ ነው ( የሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 32 እና 33 ) ሠ ) የዘላለም ሕይወት ተስፋ ነው ( 1ኛ ዮሐንስ 2 ፥ 25 ) ረ ) እርግጠኝነት ያለበትና እንደ ነፍስ መልሕቅ የሆነ ተስፋ ነው ( ዕብራውያን 6 ፥ 19 ) ሰ ) የምንደፍርበት ፣ የምንመካበት እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ ቤቱ የምንሆንበት ተስፋ ነው ( ዕብራውያን 3 ፥ 6 ) ሸ ) ለእግዚአብሔር ወንጌል የተለየንበት ተስፋ ነው ( ሮሜ 1 ፥ 1 እና 2 ፣ 3 _ 5 ) ቀ ) የሕይወትን አክሊል የምናገኝበት ተስፋ ነው ( ያዕቆብ 1 ፥ 12 ) በ ) የተስፋችንን ምስክርነት የምንጠብቅበት ተስፋ ነው ( ዕብራውያን 10 ፥ 13 ) የትምህርቱ ዋና ዋና ነጥቦች እነዚህ ናቸው ለበለጠ መረጃ በቪዲዮ የተለቀቀውን ትምህርት ይከታተሉ የተወደዳችሁ ወገኖች እንግዲህ የቅዳሴ ማርያም ጸሐፊ አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት በማለት አዳም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ሲል በወቅቱ ለሆነው ነገር ማርያምን የተሰደደው የአዳም ተስፋ ናት ቢላትም መጽሐፍቅዱሳችን ግን ከዚህ በተቃራኒው የአዳም ተስፋው ክርስቶስ እንደሆነ በሰፊው ያትታል ታድያ እኛም ልናይ የሞከርነው ይህንኑ እውነት ነው ስለዚህ የአዳም ተስፋው ማርያም ሳትሆን ክርስቶስ መሆኑን መጽሐፍቅዱሳዊ አስረጂ በመስጠት በሰፊው አብራርቼ ተናግሬያለሁ ቀጣዩ ትምህርታችን የሚሆነው ግን ተፈስሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ የአዳም ፋሲካው የሆንሽ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ የሚል በኦርቶዶክስ መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈ ስላለ በቀጣዩ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን የአዳም ፋሲካው ማን እንደሆነ ከመጽሐፍቅዱሳችን አስረጂ በማቅረብ የምንመለከተው ይሆናል እስከዚያው ጌታ ሁላችንንም የዚያ ሰው ይበለን ቸር እንሰንብት አሜን ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry

Tuesday 17 July 2018

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ (...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 14 ) ክፍል አራት አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) 1ኛ ) ምንም እንኳ የቅዳሴ ማርያም መጽሐፍ አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ቢለንም ለተከታታይ ሳምንት ከተማርናቸው የእግዚአብሔር ቃል እውነቶችና ትምህርቶች የተነሳ ወደ ዕረፍቱ ለመግባት የተሰጠው ተስፋ አንድና አንድ ኢየሱስ ስለሆነ መቼም ማርያም ናት እንደማትሉኝ እርግጠኛ ነኝ 2ኛ ) እንግዲህ ወደ ዕረፍቱ ለመግባት የተሰጠው ተስፋ ( ኢየሱስ ) አሁንም የተጠበቀ ስለሆነ ከእናንተ ማንም ለዚያ ሳይበቃ እንዳይቀር እንጠንቀቅ ይለናል ( ዕብራውያን 4 ፥ 1 _ 4 ) 3ኛ ) ለዚህ መፍትሔው ወደ ዕረፍቱ እንድንገባ የተሰጠንንና የተጠበቀልንን ተስፋ ( ኢየሱስን ) እንደሚገባ መስማት ፣ ማመንና መታዘዝ ነው ( ዕብራውያን 2 ፥ 1 _ 4 ) 4ኛ ) እኛ ያመነው ግን ወደ ወደዚያ ዕረፍት እንገባለን ተብሎ ተጽፎልናል ( ዕብራውያን 4 ፥ 3 ) 5ኛ ) በዕብራውያን 12 ፥ 15 መሠረት ከእናንተ ማንም የእግዚአብሔር ጸጋ እንዳይጎድልበት ደግሞም መራራ ሥር በቅሎ ችግር እንዳያስከትልና ብዙዎችን እንዳይበክል ተጠንቀቁ ይለናል በመሆኑም ከእናንተ ማንም የእግዚአብሔር ጸጋ እንዳይጎድልበት ማለቱ የእግዚአብሔርን ጸጋ ሳይዝ እንዳይቀር ማለቱ ነው 6ኛ ) ከዚህ እውነት የተነሳ የምንድነው በሥራችን ሳይሆን በእግዚአብሔር ጸጋ ስለሆነ የእግዚአብሔርን ጸጋ መጣል የለብንም ( ኤፌሶን 2 ፥ 8 ፣ ቲቶ 2 ፥ 11 ፣ ገላትያ 2 ፥ 21 ) 7ኛ ) የእግዚአብሔርን ጸጋ የሚያስጥሉን ወይንም ሳንይዝ እንዳንቀር የሚያደርጉንና ወደ አለመታዘዝ ሊወስዱን መራራ ሥር ሆነው በውስጣችን የበቀሉ ቁጣ አድመኝነትና የመሣሠሉት ናቸው ( ዕብራውያን 12 ፥ 15 ) 8ኛ ) እግዚአብሔር የራሱን ዕረፍት እንድንካፈል ጋበዘን 9ኛ ) ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት መግባት የሚቻለው በልጁ በማመን ነው ( ዕብራውያን 4 ፥ 8 _ 10 ) ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry

Saturday 14 July 2018

ገድላትና ድርሳናት መጽሐፍቅዱስን ተንታኞች እንጂ ተኪዎች አይደሉም ያሉት መጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለማየሁ የስሕተት አስ...ገድላትና ድርሳናት…………መጽሐፍቅዱስን ተንታኞች እንጂ ተኪዎች አይደሉም ሲሉ የተደመጡት የመጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለማየሁ የስሕተት አስተምህሮ በእግዚአብሔር ቃል ተጋለጠ የቅኔውና የመጽሐፉ መምህር መጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለማየሁ ገድላት፣ ድርሳናት የተአምራት መጻሕፍትና የመልካ መልክ ድርሰቶችም ጭምር የመጽሐፍቅዱስ ማብራርያዎች ናቸው ሊሉን የተጠቀሙበትን ዘዴ እንደሚከተለው አቀርባለሁ ስለ ድንግል ማርያም ብፅዕና እና ስለ ሌሎችም የመጽሐፍቅዱስ ሃሳቦች ሊናገሩ ፈልገው ማርያምን ዋና ተጠቃሽ በማድረግ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል ስትል ማርያም ተናገረች ርዕሰ ዜናውን ሉቃስ አቀረበ እነ ኤፍሬም ሶርያዊ ፣ ነገረ ማርያም ፣ ተአምረ ማርያም ፣ ዮሐንስ አፈወርቅና የመሣሠሉት ደግሞ ማብራርያውን ወይም ትንታኔውን ሰጡ ሲሉ ሊያስረዱን ሞከሩ እኔ ግን በጣም የሚደንቀኝ 1ኛ ) እነዚህ አባት የለሽ የገድልና የድርሳን መጻሕፍት 2ኛ ) ተደራሽነታቸው ለማን እንደሆነ እንኳ የማይታወቁ መጻሕፍት እንዴት ሆነው ነው የትልቁ የእግዚአብሔር መጽሐፍና የእኛም መጽሐፍ የሆነው የመጽሐፍቅዱስ ማብራርያ ሊሆኑ የሚችሉት የመጽሐፍቅዱስን ስነ አፈታትና ትርጓሜን የተማረ ሰው መቼም አዋልድ መጻሕፍትም ሆኑ ገድላትና ድርሳናት የመጽሐፍቅዱስ ማብራርያ ናቸው ሲል እንዲህ ይላል ፣ ይህንንም ያስባል ብለን አንገምትም የመጽሐፍ ቅዱስን አተረጓጐም ማብራርያቸውን የምናገኘው አዋልድ መጻሕፍት ፣ ገድልና ድርሳናት ውስጥ ነው ሊል ቀርቶ መጽሐፍቅዱሱን ሲተረጉም እንኳ አውዱን በጠበቀ መልኩ አንቀጹንና ሙሉውን ምዕራፍ ተመልክቶ በቁርኝት ጥቅሶችና በማመሳከርያ ምንባቦች ሃሳቡን በመረዳት ነው አልፎም ሄዶ ከጠቅላላው የመጽሐፍቅዱስ ሃሳብ ጋር አስተያይቶ ሊገነዘብ ይወዳል ከዚህም ሌላ የተጻፈበትን ክፍለ ዘመን ፣ ለምንና ለማን እንደተጻፈ ፣ መቼ እንደተጻፈና የት እንደ ተጻፈ እነዚህን ሁሉ እና የመሣሠሉትን በማድረግ የተጻፈበትን ዋና ሃሳብ ያገኛል ይህንንም የሚያደርገው ማንም ሰው መጽሐፍቅዱስን ለገዛ ራሱ መተርጎም ባለመቻሉ ትክክለኛውንና መጻሕፍት የመሠከሩለትን የእግዚአብሔርን እውነት ለማግኘት ነው 2ኛ ጴጥሮስ 1 ፥ 16 _ 21 ስለዚህ የቅኔውና የመጽሐፉ መምህር መጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለማየሁ ይህቺን አጭር መልዕክትና የቪዲዮ ትምህርት ተመልክተው ትምህርቶትን በእነዚህ እውነቶች እንዲቃኙ ፣ እንዲያስተካክሉም በማሰብ ይህቺን አጭር ማሳሰብያ ከታላቅ ትሕትና ጋር ልተውሎት እወዳለሁ ወዳጅ ፣ ዘመድ ፣ ጓደኛ ፣ የቅርብ ሰዎችም ካላችሁ ይህ ትምህርት እንዳያመልጣቸው መልዕክታችንንም ሆነ ቪዲዮአችንን ለመጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለማየሁ አድርሱአቸው የክፍል ሁለት ትምህርት ይቀጥላል ተባረኩ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከተሃድሶ ለኦርቶዶክስ

Thursday 12 July 2018

ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች የሚለው ለማን ነው ? ( መዝሙር 45 ፥ 9 ) ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች የሚለው ለማን ነው ? ( መዝሙር 45 ፥ 9 ) ወትቀውም ንግሥት በየማንከ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምኢ ዕዝነኪ ርስዒ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ እስመ ፈተወ ንጉሥ ስነኪ እስመ ውእቱ እግዚእኪ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና መዝሙረ ዳዊት  45 : 9 - 11 የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ለእናንተ ይሁን ዛሬ በዚህ ትምህርት ውስጥ መዝሙረ ዳዊትንና ቅዳሴ ማርያምን በንጽጽር ወደ እናንተ በማቅረብ ፍርዱን ለእናንተ እተዋለሁ :: በቅዳሴ ማርያም መጽሐፍ ላይ ቅዳሴ ማርያምን ደረሰ ስለተባለው አባ ሕርያቆስ የቅዳሴ ማርያም መጽሐፍ እንዲህ ይለናል :: የብህንሳ ኤጲስቆጶስ አባ ሕርያቆስ አምላክን ስለወለደች ስለ እመቤታችን ድንግል ማርያም በመንፈስቅዱስ የደረሰው የቊርባን ቅዳሴ ይህ ነው ይለንና ልመናዋና በረከትዋ ከአገልጋይዋ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ይለናል :: አያይዞም ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሰናየ ፣ ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሰናየ ፣ ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሰናየ ወአነ አየድዕ ቅዳሴሃ ለማርያም አኮ በአብዝኆ አላ በአውሕዶ ወአነ አየድዕ ውዳሴሃ ለድንግል አኮ በአንኆ በቃለ ዝንጋዔ አላ በአኅድሮ ወአነ አየድዕ ዕበያቲሃ ለድንግል:: ወደ አማርኛው ስተረጉመው ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ፣ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ፣ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ እኔም የማርያምን ቅዳሴ እናገራለሁ በማብዛት አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ እኔም የድንግልን ውዳሴ እናገራለሁ መዘንጋት ባለበት ቃል በማስረዘም አይደለም በማሳጠር ነው :: እኔም የድንግልን ገናንነትዋን እናገራለሁ እያለ ይናገራል ( ምንጭ የቅዳሴ ማርያም መጽሐፍ ) ከዚሁ ጋር በንጽጽር መዝሙረኛው ዳዊት የተናገረውን እንመልከት:: ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሠናየ ወአነ አየድዕ ግብርየ ለንጉሥ ከመ ቀለመ ጸሐፊ ዘጠበጠበ ይጽሕፍ ልሳንየ ይሴኒ ላህዩ እምውሉደ እጓለ እመሕያው ተክዕወ ሞገስ እምከናፍሪከ በእንተ ዝ ባረከከ እግዚአብሔር ለዓለም ወደ አማርኛው ስተረጉመው ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ አንደበቴ እንደ ፈጣን ጸሐፊ ብርዕ ነው ውበትሕ ከሰው ልጆች ይልቅ ያምራል ሞገስ በከንፈሮችሕ ፈሰሰ ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ባረከህ እያለ ይቀጥላል ( መዝሙር ( 45 ) በሙሉ ተመልከቱት ) የተወደዳችሁ ወገኖች ንጽጽሩን በማስተዋል ሆናችሁ ስትመለከቱት መዝሙረኛው ዳዊት ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ እያለ ስለ ንጉሡ ውበት እግዚአብሔርን እየባረከ ይቀኛል ይዘምራል :: አባ ሕርያቆስ የቅዳሴ ማርያም ደራሲ ነኝ የሚለው ደግሞ በመንፈስቅዱስ የደረስኩት ነው በማለት ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ፣ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ፣ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ እኔም የማርያምን ቅዳሴ እናገራለሁ በማለት ማርያምን ከፍ ባለ ምስጋና ማወደስ ጀመረ :: ስለዚህ ልቡናችን መልካም ነገር ማፍለቅም ሆነ ማመስገን ያለበት መዝሙረኛው ዳዊት እንዳለው ለንጉሡ ለጌታችን ነው ? ወይስ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ እንደተናገረው ለማርያም ነው ? ለማን ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሠናየ እንበል ? ማርያምን ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ወይም አፈለቀ ስንል እንድናወድሳት መጽሐፍቅዱስ ያስተምረናል ? መጽሐፍቅዱሳችን አሁንም እንደነገረን በዚህ ነገር ምስጋና መስጠት ያለብን ለእግዚአብሔር ብቻ ነው :: ማርያምንም ከእግዚአብሔር ጋር በእኩልነት አወድሱአት ሲል ግን አልጻፈልንም :: እንደገናም በውኑ አባ ሕርያቆስ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ሲል በመንፈስቅዱስ ማርያምን እንዲያመሰግን መንፈስቅዱስ መርቶታልን ?ይህንን ያልኩበት ከላይ በገለጽኩት መሠረት መዝሙረኛው ዳዊት ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ በማለት ሲያወድስ የተመለከትነው በትንቢታዊ ቃል ሳይቀር የተነገረለትን ንጉሣችንን ኢየሱስን ነው :: ታድያ አባ ሕርያቆስ እንዳለን የማርያምን ቅዳሴ በመንፈስቅዱስ ነውና የደረስኩት ፤ በተደረሰው በመንፈስቅዱስ አማካኝነት ጌታ መሆኑ ቆርቶ ማርያምን ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሰናየ ማለትም ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ ስትባል ነው መመስገን ያለባት ይለናል :: ይህንን ማለቱ ደግሞ መዝሙረኛው ዳዊት ጐሥዓ ልብየ ቃለ ሠናየ ወአነ አየድዕ ግብርየ ለንጉሥ ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ እኔ ሥራዬን ለንጉሥ እነግራለሁ እያለ ማመስገኑ ተሳስቶ ነውና ለማርያም ውዳሴ በመስጠት ደረጃ ትክክለኛው የመንፈስቅዱስ ደራሲ እኔ አባ ሕርያቆስ ነኝ እያለን ነው :: እኛ ግን የምናምነው ትክክለኛው እኔ ነኝና ልቡናችን በጎ ነገርን አፍልቆ ማርያምን እናመስግን ያለንን ሕርያቆስን ሳይሆን መጽሐፍቅዱሳችን በመሰከረልን ቃል መሠረት ምስጋና ፣ ቅዳሴም ሆነ ውዳሴ የሚሰጠው ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ የምንቀበለውም ሆነ ተቀብለን የምናመሰግነው የዳዊትን ምስጋና ምስጋናችን በማድረግ ነው :: እንደገናም ሕርያቆስ ማርያምን ሊያመሰግን በመንፈስቅዱስ ቢያላክክም የተሳሳተው ሕርያቆስ እንጂ መንፈስቅዱስ አይደለምና የዳዊትን ምስጋና ምስጋናችን አድርገን ልቤ መልካም ነገርን አፈለቀ በማለት ንጉሥ ዳዊት በትንቢታዊ ቃል ለንጉሡ ለኢየሱስ በሰጠው መሠረት እኛም ለንጉሣችን ለኢየሱስ ከፍ ያለ ምስጋናን እንሰጣለን :: ወገኖች ጽሑፉን አንብቡት ተጠቀሙበት ደግሞም ተባረኩበት ሰላም ሁኑ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39
 Primary: yonasasfaw8@gmail.com

Friday 6 July 2018

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ (...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 11 ) ክፍል አራት ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት እርሱም ኢየሱስን አመጣ ( የሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 23 ) አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) ምንጭ ፦ ቅዳሴ ማርያም የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዚህን የቪዲዮ ትምህርት አንኳር አንኳር ሃሳብ እንደሚከተለው አቀርባለሁና ተከታተሉ የቅዳሴ ማርያም ደራሲ አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ በማለት ተናገረ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) እንዲህ ማለቱ ታድያ የቅዳሴ ማርያምን ሃሳብ በሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 23 ከተጻፈው ሃሳብ ጋር በትክክል አስተያይተን ከመረመርነው እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት እርሱም ኢየሱስን ያመጣ አይደለም ወደሚለው የሚወስድ ነው ለምን ስንል እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት እርሱም ኢየሱስን አመጣ ብሎ ያመነ ሰው በመድኃኒቱ በኢየሱስ ላይ ብቻ ሕይወቱ ያረፈ ነው ነገር ግን ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ሲል የቅዳሴ ማርያምን መጽሐፍ ያመነ ሆኖ ሳይቀር ከዚህ በተጨማሪ ይህንኑ ቃል እንዲሁ ተስፋው አድርጎ እየቀደሰና እያስቀደሰ የሚኖር አማኒ ከሆነ ግን ለአዳም ብቻ ሳይሆን ዛሬም ላይ ለእኔ የገነት በር መግቢያ ተስፋዬ ማርያም አንቺ ነሽ ብሎ የሚያስብ ነውና እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት ሆኖ የመጣበትን የኢየሱስ መምጣትና እግዚአብሔርም በዚሁ በተስፋው ቃል መሠረት መድኃኒት አድርጎ ኢየሱስን ያመጣበት ምሥጢር አይገባውም ከዚህ በመቀጠል ጌታ እግዚአብሔር ኢየሱስ የተባለውን መድኃኒት የሆነውን እውነት ያመጣበትን ወደ ሰባት የሚደርሱ ነጥቦችን እንደሚከተለው በዝርዝር አቀርባለሁ 1ኛ ) ጌታ እግዚአብሔር ኢየሱስ የተባለውን መድኃኒት ሲያመጣ በቅድሚያ ለሰው ዘር በሙሉ የሚሆንን ተስፋ ሰጥቶ ነው 2ኛ ) እርሱ የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው 3ኛ ) ይህንን ተስፋ ያረጋገጥነው በእምነት ነው 4ኛ ) ይህ በእምነት ያረጋገጥነው ተስፋ እርሱ ንጹሕ እንደሆነ እኛንም ንጹሐን ያደርገናል 5ኛ ) ይህ ተስፋ ታድያ በቅድምና ለአባቶችም የተሰጠ ተስፋ ነው 6ኛ ) እግዚአብሔር የሰጠን ተስፋ የታመነውንና የተፈጸመውን የዳዊትን ተስፋ ነው 7ኛ ) ይህ ተስፋ በአብርሃም በዳዊትና በእስራኤል ሕዝብ ሳይቀር አሕዛብም ሁሉ ተስፋ ያደረጉት ነው የተወደዳችሁ ወገኖች በተራ ቁጥር የተዘረዘሩት ነጥቦች አስረጂ ጥቅሶች አሏቸው እነዚህን አስረጂ ጥቅሶች የምታገኙት በቪዲዮ ከተለቀቀው ትምህርት ነው ስለዚህ ለበለጠ መረጃ ቪዲዮውን ተከታተሉ ጌታ እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39
 Primary: yonasasfaw8@gmail.com

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ (...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 11 ) ክፍል አራት ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት እርሱም ኢየሱስን አመጣ ( የሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 23 ) አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) ምንጭ ፦ ቅዳሴ ማርያም የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዚህን የቪዲዮ ትምህርት አንኳር አንኳር ሃሳብ እንደሚከተለው አቀርባለሁና ተከታተሉ የቅዳሴ ማርያም ደራሲ አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ በማለት ተናገረ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) እንዲህ ማለቱ ታድያ የቅዳሴ ማርያምን ሃሳብ በሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 23 ከተጻፈው ሃሳብ ጋር በትክክል አስተያይተን ከመረመርነው እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት እርሱም ኢየሱስን ያመጣ አይደለም ወደሚለው የሚወስድ ነው ለምን ስንል እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት እርሱም ኢየሱስን አመጣ ብሎ ያመነ ሰው በመድኃኒቱ በኢየሱስ ላይ ብቻ ሕይወቱ ያረፈ ነው ነገር ግን ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ሲል የቅዳሴ ማርያምን መጽሐፍ ያመነ ሆኖ ሳይቀር ከዚህ በተጨማሪ ይህንኑ ቃል እንዲሁ ተስፋው አድርጎ እየቀደሰና እያስቀደሰ የሚኖር አማኒ ከሆነ ግን ለአዳም ብቻ ሳይሆን ዛሬም ላይ ለእኔ የገነት በር መግቢያ ተስፋዬ ማርያም አንቺ ነሽ ብሎ የሚያስብ ነውና እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒት ሆኖ የመጣበትን የኢየሱስ መምጣትና እግዚአብሔርም በዚሁ በተስፋው ቃል መሠረት መድኃኒት አድርጎ ኢየሱስን ያመጣበት ምሥጢር አይገባውም ከዚህ በመቀጠል ጌታ እግዚአብሔር ኢየሱስ የተባለውን መድኃኒት የሆነውን እውነት ያመጣበትን ወደ ሰባት የሚደርሱ ነጥቦችን እንደሚከተለው በዝርዝር አቀርባለሁ 1ኛ ) ጌታ እግዚአብሔር ኢየሱስ የተባለውን መድኃኒት ሲያመጣ በቅድሚያ ለሰው ዘር በሙሉ የሚሆንን ተስፋ ሰጥቶ ነው 2ኛ ) እርሱ የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው 3ኛ ) ይህንን ተስፋ ያረጋገጥነው በእምነት ነው 4ኛ ) ይህ በእምነት ያረጋገጥነው ተስፋ እርሱ ንጹሕ እንደሆነ እኛንም ንጹሐን ያደርገናል 5ኛ ) ይህ ተስፋ ታድያ በቅድምና ለአባቶችም የተሰጠ ተስፋ ነው 6ኛ ) እግዚአብሔር የሰጠን ተስፋ የታመነውንና የተፈጸመውን የዳዊትን ተስፋ ነው 7ኛ ) ይህ ተስፋ በአብርሃም በዳዊትና በእስራኤል ሕዝብ ሳይቀር አሕዛብም ሁሉ ተስፋ ያደረጉት ነው የተወደዳችሁ ወገኖች በተራ ቁጥር የተዘረዘሩት ነጥቦች አስረጂ ጥቅሶች አሏቸው እነዚህን አስረጂ ጥቅሶች የምታገኙት በቪዲዮ ከተለቀቀው ትምህርት ነው ስለዚህ ለበለጠ መረጃ ቪዲዮውን ተከታተሉ ጌታ እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39
 Primary: yonasasfaw8@gmail.com

Monday 2 July 2018

የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ (...የተቋቋመች ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ከአዳኟ ከኢየሱስ የተፋታችበት የቁልቁለቱ መንገድ ( ቊጥር 10 ) ክፍል አራት ተስፋችን ማነው ? ድንግል ማርያም ወይስ ክርስቶስ ? የቅዳሴ ማርያም ደራሲ እንዲህ አለን ፦ አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት ትርጉም ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ( ምንጭ ቅዳሴ ማርያም ) መጽሐፍቅዱሳችንስ ምን አለን ፦ «እግዚአብሔር አምላክም ለአዳምና ለሚስቱ የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው፥ አለበሳቸውም »… አዳምንም አስወጣው፥ «ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ » ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በዔድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ ( ኦሪት ዘፍጥረት 3 ፥ 21 ፣ 24 ) ነገር ግን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ ( ሮሜ 13 ፥ 14 ) ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና ( ገላትያ 3 ፥ 27 ) የተወደዳችሁ ወገኖች ከነዚህ ጥቅሶች በመነሳት እንግዲህ በዚህ ዓለም ተስፋ ያጣና ያለክርስቶስ በመሆኑ ምክንያት ከእግዚአብሔር እንደተለየ የተገነዘበና የሚሰማው ሁሉ በክርስቶስ ደም ሰላም የተመሠረተ ከመሆኑ የተነሳ አንድን አዲስ ሰው በመፍጠር ሰላም ይደረግ ዘንድ የጥሉ ግድግዳ ፈርሶ ሁለታቸው በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀዋል ስለዚህ አይሁድ አለበለዚያም አሕዛብ ብቻ ሳይሆኑ ዛሬም ላይ ወደዚህ እውነት ያልመጣን ሁላችን በክርስቶስ ኢየሱስ ተስፋ ወደሚገኝበት ፣ ከእግዚአብሔርም ጋር አንድ ወደምንሆንበት ወደዚህ ወደተባረከው ሕይወት እንምጣ ኤፌሶን 2 ፥ 11 _ 18 ማርያምም የሰው ዘር ስለሆነች ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው እኔ ነኝ አላለችንም ይልቁንም ተስፋዋም ሆነ መድኃኒትዋ ክርስቶስ መሆኑን ተናገረች የሉቃስ ወንጌል 1 ፥ 47 ለበለጠ መረጃ ቪዲዮውን ይመልከቱ ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን Contact https://www.facebook.com/yonas.asfaw.39
 Primary: yonasasfaw8@gmail.com