Thursday 1 June 2017

የጸምና የጸሎት ጥሪ የመልዕክት ርዕስ ፦ የከበረውን ከተዋረደው ብትለይ….. ( ኤርምያስ 15 ፥ 19 _ 21 )የጸምና የጸሎት ጥሪ የመልዕክት ርዕስ ፦ የከበረውን ከተዋረደው ብትለይ….. ( ኤርምያስ 15 ፥ 19 _ 21 ) አቤቱ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ ( ሰቆቃወ ኤርምያስ 5 ፥ 21 ) የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን እግዚአብሔር አምላክ በዛሬው የጸሎት ክፍለ ጊዜ በብዙ ረድቶን ነበር የጸለይነውም እስከዛሬ በተማማርንባቸው የትምህርት አርዕስቶች ላይ ተመስርተን ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክስ እናት ቤተክርስቲያናችን በእነዚህ እውነቶች ልክ ወደ ጥንተ መሠረቷ ወደ እግዚአብሔር ቃል እውነት ተመልሳ ይህንኑ እንድትሰብክና እንድታስተምር ለመርዳት ነው ታድያ በዚህ ሁሉ የረዳንን ጌታ በቅድሚያ ላመሰግነው እወዳለሁ ከዚህ በተጨማሪም በዚህ የጸሎት ፕሮግራም ላይ የዚሁ ራዕይ ሸክም ኖሯችሁና ለመጸለይ የመጣችሁ ፣ አብራችሁን የጸለያችሁ ቅዱሳን ወገኖች በሙሉ እግዚአብሔር በብዙ ኃይል ይባርካችሁ ብድራታችሁንም ይክፈል በማለት ላመሰግናችሁና ልባርካችሁም እወዳለሁ ዘመናችሁ ይባረክ ከዚህ በመቀጠል ግን እንደተለመደው የሰኞና የሐሙሱ የፌስ ቡክ ላይቭ አገልግሎት ይቀጥላል ሰኞ ላይ የሚጀምር አዲስ ትምህርት ሥዕል በመጽሐፍቅዱስ እንዴት ይታያል ፣ ሥዕል በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን መቼ ተጀመረና የመሣሠሉትን ሃሳቦች በማንሳት መጽሐፍቅዱሳዊ እውነቶችን የምንማማርበት ጊዜ ይሆናል አሁንም መቅረት በብዙ የተከለከለና የማይፈቀድም በመሆኑ አትቅሩ ለማለት እወዳለሁ በተረፈ በሰኞ ፕሮግራማችን እስከምንገናኝ የጌታ ሰላም ይብዛላችሁ በማለት የምሰናበታችሁ ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 yonasasfaw8@gmail.com

No comments:

Post a Comment