Thursday 23 February 2017



የግጥም መነባንብ 




የግጥሙ ርዕስ   መብራቱ አይጠፋም










Image result for the lamp of god had not yet gone out and samuel was



የግጥም መነባንብ 




የግጥሙ ርዕስ   መብራቱ አይጠፋም



የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ነገ ማለዳ  በካናዳ ኦታዋ የሰዓት አቆጣጠር 10 ሰዓት 10:00 In the morning ላይ የሚጀምር እግዚአብሔርን መከተል በሚል ርዕስ 15 የትምህርት ክፍለ ጊዜ ላይ ደርሰናልና ይህንን ትምህርት ይዤላችሁ በሰዓቴ እቀርባለሁ አምናለሁ ጌታ መንፈስቅዱስ ጥሩ ጊዜ ሰጥቶን በቃሉ ይገነባናል ትምህርቱ በፌስቡክ ላይቭ ነውና የሚተላለፈው ሳያመልጣችሁ በመስመሩ ላይ ገብታችሁ እንድትከታተሉ ላበረታታችሁ በጌታ ፍቅር እወዳለሁ ተባረኩልኝ ደግሞም በጌታ ወገኖቼ የሆናችሁትን የፕሮግራሜ ታዳሚዎችና ተከታታዮች ሁላችሁንም እወዳችኋለሁ አከብራችኋለሁ ደግሞም እጸልይላችኋለሁ እናንተም ለዚህ አገልግሎት ጸልዩ ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ከዚህ በመቀጠል ግን ለነገው የትምህርት ክፍለ ጊዜ እንደ መሰናዶ ወይንም እንደ ማነቃቂያ የምትሆን እኔ ጋር ምሽት ስለሆነ ከሽ ከሽ የምታረጓትንና የምታጣጥሟትን እንደ እስናክ የእራት መክሰስ ዓይነት የሆነች አጠር ብላ እየጣፈጠች ወደ ውስጥ የምትገባ ግጥም  እነሆ ብያለሁ አንብቧት _________________

የግጥሙ ርዕስ መብራቱ አይጠፋም የሚል ነው 



 መብራቱ አይጠፋም 



ይለኮሳል እንጂ መብራቱ አይጠፋም 

የሚቀሰቀሰው ሳሙኤል አልተኛም 

የነኤሊ ዓይኖች ማየት ሲሳናቸው 

በኃጢአት በድካም የፈዘዙ ሆነው 

አጥርቶ የሚያይን ጌታ ያዘጋጃል 

መቅደስ የተኛውን ሳሙኤልን አይቷል 

ብርቅ የሆነውም ቃል የእግዚአብሔሩ 

ሊገለጥ ሊነገር በሀገር በምድሩ 

ጊዜው ደረሰና ሳሙኤል ተጠርቶ 

እነሆኝ እያለ ከተኛበት ነቅቶ 

ቃሉ በቤርሳቤህ በዳን ሲደርስለት 

ሳሙኤል ሆይ አንተ ነቢይ ነህ አሉት 

አውቀውት አምነውት ተስማምተውም ጠሩት 

ከስማችን በፊት መልዕክቱ ሲደርስ

የተላከ ሆኖ በመንፈስቅዱስ 

ተብለን ልንጠራ ለሰዎች ሳይቸግር 

ሐዋርያ ነቢይ መጋቢ አምባሳደር 

ሊጠሩን ሲነሱ በሙሉ አፋቸው 

ያለማስታወቅያ ፈቃደኛ ሆነው 

ጸጋችን ተገልጦ ለሰው የሚታየው 

ያን ጊዜ ጌታችን ከፍ ብሎ ይከብራል 

ምስጋናን ሊቀበል በምድር ይነግሣል 

ከዕንቅብ በታች ሆኖ የጋን ውስጥ መብራት 

መሆን ይቀርና ለሰው የሚያታክት

አይቀር ተደብቆ ሆኖ በልባችን 

የዓለም መድኃኒት የዓለም ብርሃን 

ይበራል ይደምቃል የጌታችን መብራት 

በእኛ ላይ ሲመጣ የመንፈሱ እሳት 

ይበራል ይደምቃል የጌታችን መብራት 

በእኛ ላይ ሲመጣ የመንፈሱ እሳት 








ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን 




Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry 



ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ 

Tuesday 21 February 2017

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም   .............

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry:
ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ 

አታውቁም



   


.............
: ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ  አታውቁም      .......... ለመሠል   ባልንጀሮ ች   የተሰጠ  የክፍል ሁለት መልስ   ……….. ለመሠል  ባልንጀሮች  የ...

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም   ..........ለ...

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ 

አታውቁም



   


..........ለ...
: ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ  አታውቁም      .......... ለመሠል   ባልንጀሮ ች   የተሰጠ  የክፍል ሁለት መልስ   ……….. ለመሠል  ባልንጀሮች  የተሰጠ...

ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ 

አታውቁም



   


..........ለመሠል ባልንጀሮ  የተሰጠ የክፍል ሁለት መልስ 




Image result for do u want us to call  fire to come

Image result for do you want us to call fire down from heaven







……….. ለመሠል  ባልንጀሮች  የተሰጠ የክፍል ሁለት መልስ




የመልዕክቱ ዋና ኃይለ ቃል 




ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም







ወይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ አግበኣ ለመጥባሕትከ ውስተ ቤታ 
እስመ ኲሉ ዘይቀትል በመጥባሕት ይመውት በመጥባሕት
ወንጌል ዘማቴዎስ ምዕራፍ ፳፮ ቊጥር ፶፪




በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አለው ፦ ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና
ሰይፍህን ወደ ሥፍራው መልስ
የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 26 ቊጥር 52





ወወድቀ ዲበ ምድር ወሰምዐ ቃለ ዘይቤሎ ፦——
ሳውል ሳውል ለምንት ትሰድደኒ ይብእስከ ረጊጽ ውስተ ቀኖት በሊሕ ( ግብረ ሐዋርያት ምዕራፍ ፱  ቊጥር ፬ )
የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 9 ቊጥር 4




Image result for the son of man came to seek and save the lost





እርሱ ግን ዘወር ብሎ ገሠጻቸውና ፦ ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም የሰው ልጅ የሰውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም አለ ወደ ሌላ መንደርም ሄዱ የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 55 እና 56 




የተወደዳችሁ ወገኖቼ በቅድሚያ የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ እያልኩኝ ለዛሬ ለእናንተ ለአንባቢዎች ወዳዘጋጀሁት መልዕክት አልፋለሁ በመምሕር ምሕረተ አብ ጉዳይ ላይ ወንድሜ ባለመረዳት ባዘጋጀውና ተነሣ ሕዝቤ ተነሣ የጥንቱ እንዳይረሳ ሲል በቪዲዮ በለቀቀው የክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት የአዋጅ መልዕክቱ ከእኔም ሆነ እኔን ከመሠሉ ወንድሞቼ ተገቢ የሆነ መልስ መሰጠቱ ይታወሳል ይሁን እንጂ  ምሕረተአብን  ቊርጥ  የሆኑ ናቸው ባንልም ምሕረተ አብን የመሠሉ ፣ ምሕረተ አብ መሠል  ፣ መሣዮች ፣ ተመሣሣዮች ወይንም  ልዩነት የሌላቸው ባልደረቦች  ልንላቸው እንችላለን  በየቤተ እምነቱ አይጠፉምና ብዕሬን በምሕረተ አብ ላይ ብቻ ለበጐ በሆነ እውነትና ለመመለስ በሆነ ቃል ሳላሳርፍ እርሱን ለመሠሉ ባልንጀሮቹና  ተመሳሳዮቹ ሁሉ መልዕክቴ አንድ ብላ እንድትደርስ ለእናንተ ለአንባቢዎች  እነሆ ብያለሁ እና ተከታተሉ  ተመሣሣዮችን ወይም ልዩነት የሌላቸው ቢጤዎችን የግድ በአንድ  ክልል ፣ መንደርና ሠፈር ውስጥ   ማየት እንደገናም እንፈልግ ብለን ስንነሳ ደግሞ   በዚሁ ሠፈርና መንደር  ውስጥ መፈለግም ሆነ ፈልገን ማግኘት አይጠበቅብንም  ተመሣሣዮችን ከሚመሣሠሉበት ነገር ተነስተን በአንድ ካታጐሪ ውስጥ ካታጐራይዝድ አድርገን ብንመድባቸውና ብናስቀምጣቸውም መገኛቸው ግን በልዩ ልዩ ቦታ ስለሆነ አንዳንድ ጊዜ በተለያዩ ቦታዎችና ሀገሮች እንደገናም በተለያዩ የቤተ እምነት  ተቋሞች ፣ ድርጅቶች ፣ በየሰፈሩ  በየመንደሩ ውስጥ ሳይቀር ልናገኛቸው እንችላለን ለዚህ አባባሌ በዮሐንስ ወንጌል 9 ፥ 8 _ 12 ላይ  ጥሩ ምሳሌ ይሆናል ብዬ ያሰብኩትን የዚህን ዓይነ ሥውር ሰው ታሪክ ወደ እናንተ ማቅረብ ወደድኩኝ  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምራቁ ጭቃ አድርጎ በጭቃው የዕውሩን ዓይኖች ቀባና ሂድና በሰሊሆም መጠመቅያ ታጠብ አለው ትርጓሜው የተላከ ነው ስለዚህ ሄዶ ታጠበ እያየም መጣ ይለናል ወገኖቼ የሚፈለገው ግን የዚህ ዓይነ ሥውር ማየቱ ነውና በማየቱ ማለትም እያየ ስለመጣ ደስ ይበለን  ይሁን እንጂ አንዳንዶች ጐረቤቶቹ የዚህን ሰው ማየት ያልሰሙና ያላወቁ በመሆናቸው መልኩ ሳይቀር ጠፍቶባቸው የከረመ ሆኖባቸዋል ነገር ግን አንዳንዶቹ ደግሞ ቀድሞ ሲለምን አይተውት የነበሩ  በመሆናቸው ይህ ተቀምጦ ይለምን የነበረ አይደለምን ? አሉ ሌሎች ደግሞ አይደለም እርሱን ይመስላል እንጂ አሉ ያንጊዜ እርሱም እኔ ነኝ አለ እነርሱም ታድያ ዓይኖችህ እንዴት ተከፈቱ ?ቢሉት የሆነለትን ነገር ተራ በተራ ዘርዝሮ መናገር ጀመረ ይህ ሰው ታድያ ከፊተኛው ማንነቱ  ይልቅ ዛሬ ላይ ባለ ሕይወቱ ጐረቤቶቹን ሳይቀር ማደናገር የቻለው ዓይን በማግኘቱ ብቻ ሳይሆን ባገኘው ዓይን ለማየት  በመቻሉም ጭምር ነው  ወገኖቼ ቢደናገር ቢደናገር ሌላ ይደናገር እንጂ ጐረቤት ግን ይደናገራል ፣ ይጠፋዋል ብለን ልንገምት አንችልም ጐረቤት ማለት የውስጥ ገበናን እንኳ ሙሉ ለሙሉ ያውቃል ባንልም ቢያንስ የቅርብ ሰው  እና ጐረቤታችንም ስለሆነ  ስለ እኛ የሚያውቃቸው አንዳንድ የውስጥ ጉዳዮች ሊኖሩ ይችላሉ መጽሐፍቅዱሳችን በ1ኛ ጴጥሮስ 2 ፥  12  ላይ ስለሚመለከቱት ስለ መልካም ሥራችሁ፥ ክፉ እንደምታደርጉ በዚያ እናንተን በሚያሙበት ነገር፥ በሚጎበኝበት ቀን እግዚአብሔርን ያከብሩት ዘንድ በአሕዛብ መካከል ኑሮአችሁ መልካም ይሁን ይለናል ታድያ አብርሃም በኬጢ ሰዎች መካከል ሲኖር ኑሮው መልካም ስለነበረ ሚስቱ ሣራ በሞተችበት ጊዜ እኔ በእናንተ ዘንድ ስደተኛ እና መጻተኛ ሰው ነኝ በእናንተ ዘንድ የመቃብር ርስት ስጡኝ ሬሳዬንም ከፊቴ ልቅበር ሲል በጠየቀ ጊዜ የኬጢ ልጆችም ለአርብሃምም መለሱ አሉትም ፦ ጌታ ሆይ ስማን አንተ በእኛ መካከል ከእግዚአብሔር አለቃ ነህ ከመቃብር ሥፍራችን በመልካሙ ቦታ ሬሳህን ትቀብር ዘንድ ከእኛ መቃብሩን የሚከለክልህ የለም አሉት ይለናል ዘፍጥረት ምዕራፍ 23 ፥ 3 _ 7 እና ዘፍጥረት ምዕራፍ 23 ን በሙሉ አንብቡት ታድያ አብርሃምን ለኬጢ ሰዎች ማን አለቃ አደረገው ? ስንል መልሳችን ባጭሩ የኑሮው መልካምነት አለቃ አደረገው ነው ስለዚህ አብርሃም ከኬጢ ሰዎች ጋር አብሮ ሲኖር ዝም ብሎ ዓይነት በሆነ የተመሣሣይ  ጉርብትና ቡና ጠጡ ሲል እየጠራ፣ እየተጠራና እየተጠራራ እየጠጣ ፣ እያጣጣና  እየተጣጣ አልነበረም የኖረው ስለዚህ አብርሃም ከኬጢ ሰዎች ጋር በአንድ ዓይነት የኑሮ ሁኔታ የተመላለሰ ስላልነበረ የሰዶም ሰዎች የአጐቱን ልጅ ሎጥን በርህን ክፈት ሲሉት እንደተጋፉት አብርሃምን ግን  የተጋፋ  አንድም  የኬጢ ሰው አልነበረም እነዚህ የኬጢ ሰዎች አብርሃምን ያሉት አንድና አንድ ነገር ቢኖር  አሁንም ጌታ ሆይ ስማን አንተ በእኛ መካከል ከእግዚአብሔር አለቃ ነህ ከመቃብር ሥፍራችን በመልካሙ ቦታ ሬሳህን ትቀብር ዘንድ ከእኛ መቃብሩን የሚከለክልህ የለም ነው ለእኛም እንደ ሎጥ ሳይሆን እንዲሁ እንደ አብርሃም ባለ የከፍታ ሕይወት ምልልሳችን ምክንያት ለሌሎች መልካም ሆነን መልካም በሆነው የበረከት ቃል ወደ እኛ መጥተው የሚባርኩንንና እኛም የምንባረክባቸውን ሰዎች ይስጠን  የኑሮ መልካምነት መልካም ጉርብትናንና ጥሩ ስምን ብቻ  የሚያተርፍልን አይደለም የሚያዩን ሰዎች ከዚያ ባሻገር ባለ ነገር ሁሉ ሰላማቸውን የሚያስጠብቅ በጎ ነገር በእኛ በእያንዳንዳችን ሕይወት ከማየታቸው የተነሣ  ለአብርሃም የሰጡትን ከእግዚአብሔር የሆነ አለቅነትና የመቃብር ሥፍራ ዓይነት ለእኛም በእኛ ዘመን ያሉ የኬጢ ዓይነት ሰዎች ልዩ ልዩ ስጦታዎቻቸውን በምንፈልገው መጠን ሊሰጡን ዝግጁዎች ናቸው በእርግጠኝነትም ሳይከለክሉን ይሰጡናል የመንፈሳዊ ሕይወት ለውጥ ትርጉሙና ከሌላውም ጋር   በልዩነት የሚያስቀምጠን ምስጢሩም ሆነ መንገዱ እንግዲህ ይሄ ነው  ያው አንድ ዓይነት ሆነን ልዩነት ያላሳየን ጎረቤቶች ከሆንን ግን የሎጥ በሰዶም ሰዎች ፊት ያጋጠመው ዕጣ ፈንታ ሳንጠራጠር በእርግጠኝነት የእኛም  ይሆናል ዘፍጥረት 19 ፥ 1 _ 11 ይህም ሁኔታ ያለጥርጥር በሕይወታችን ይደርስብናል  ከዚህ ውጪ ወይንም ከዚያ ያለፈ ሌላ ምንም መሆን አንችልም  ከዚህ በመቀጠል   መጀመርያ ላይ ወዳነሳሁት ዕውር ሆኖ ወደ ተወለደው ሰው ታሪክ ስመልሳችሁ የዚህ ሰው ዓይን ማግኘትና ማየት ታድያ ለቅርቦቹ ማለትም ለአንዳንዶች ጐረቤቶች ሳይቀር እርሱ ነው አይደለም እርሱን ይመስላል በሚሉ አወዛጋቢ ቃላት ግራ ያጋባ ነበር እኛም ወገኖቼ ታድያ እንደዚህ ዓይነ ሥውር ዓይናችን በርቶ ማየት ስንችልና ለውጥ በሕይወታችን ሲመጣ አይደለም በሩቅ ለሚያውቀን ሰው  የቅርብ ሰዋችን ለሆነው ፣ ቡና ለሚያጣጣንና የቤታችን ጓዳ ድረስ ገብቶ ገበናችንን ሳይቀር ለሚያውቀው ሰው ሁሉ ለውጣችን እርሱ ነው እርሱ አይደለም እርሱን ይመስላል እርሷ ነች እርስዋ አይደለችም እርስዋን ትመስላለች እርሳቸው ናቸው እርሳቸው አይደሉም እርሳቸውን ይመስላሉ እነርሱ ናቸው እነርሱ አይደሉም እነርሱን ይመስላሉ እያስባለ   በማያደናግርና ግራም በማያጋባ መልኩ ትክክለኛውን እኛነታችንን እና የተለወጠውን ማንነታችን  ሊያሳያቸው ይገባል እላለሁ   በተለይ የቅርቡ ሰው ማለትም ጐረቤቱ ለውጡን ያወቀለት ሰው እንዴት ጌታ የረዳውና የታደለ ሰው  መሠላችሁ የእኛ ትክክለኛ  የሆነው ለውጣችን የሚታወቀው ደግሞ አጠገባችን ባለ ሰውና ጐረቤታችንም በሆነው ሰው ምስክርነት ነው ስለዚህ ስለሕይወታችን የመለወጥ ጉዳይ ዛሬ ታድያ ጐረቤቱም ሆነ በቅርቡ የሚያውቀን ምን ይል ይሆን ? ለአብርሃም ከኬጢ ሰዎች የተሰጠው መልስ ዛሬ ላይ ለእኛ ሆኖና እኛም ለዚህ በቅተን ከእግዚአብሔር ስለሆናችሁ የምትከለከሉትም ሆነ የምታጡት ነገር የለም እንባላለን ? ወይስ በተቃራኒው እናንተስ ከእግዚአብሔር አይደላችሑም ስንባል ሎጥን ሊገፉት ከደጅና ከበር ውጪ ባሉ ሰዎች መግፋትና መጋፋት የእኔ ፣ የአንተ ፣ የአንቺ ፣ የእኛ ፣ የእናንተ የሁላችን የምንለውን በር ለመስበር በሆነ የመገፋፋት ሕይወት ውስጥ እንኖራለን ? መልሱን እንግዲህ ለእኔ ለጻፍኩትም ሆነ ለእናንተ ለአንባቢዎች የምተወው ይሆናል ይሁን እንጂ  ለብዙዎቻችን የሕይወት መለወጥ ጐረቤት የሚሰጠው ምላሽ ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው  እርሱ ነው እርሱ አይደለም እርሱን ይመስላል የሚል ሳይሆን   ትላንትናና ከዚያ በፊት ከድሮም ጀምሮ የምናውቀው ያው እርሱ ነው ምንም የተለወጠ ነገር አላየንበትም ፣ አልተሻሻለም ፣ አልተቀየረም ለምን እንዲሁ ትዳክማላችሁ ? እርሱ እንደሆነ ክርስቶስ ቢመጣም እንኳ የሚቀየር ዓይነት ሰው አይደለምና ባወጣው ያውጣው ተዉት  የሚል መልስ  ነው ሲሰጥ  የምንሰማው እንደው እንበልና ሀገር ቀይረን፣ ዓመታት ቆይተን ተመልሰን እዚያው የድሮው ቦታችን ብንሄድ እንኳ ግልጽ የሆነና ይሉኝታም የማያውቅ አንዳንዱ ሲያገኘን ኡኡኡ መሻሻል የለም እንዴ ? ያው ነህ እኮ እንደውም ብሶብህ ነው የመጣኸው ነው  የሚለንና ስለዚህ ለውጥ የሌለው ሕይወትም ሆነ ክርስትና እንዲሁም በመድረክ የሆነ የአገልግሎት ግርታ  በአብዛኛው በእኛም ሆነ በሌሎች   ሕይወት እጅግ በጣም አጠያያቂ እየሆነ ከመጣ ሰነባብቷል ከዚህም ሌላ ጉድለት የሞላበት ሕይወታችንንና ያልተለወጠው እኛነታችንን ያዩ አንዳንንድ ሰዎች አምላካችን እግዚአብሔር በሁሉም ዘንድ የተከበረ ሆኖ  ሳለ እነዚህ ሰዎች ግን በእኛ ያለውን እግዚአብሔርን አያከብሩትም  ሮሜ 2 ፥ 17 _ 24  ለዚህም ነው እንግዲህ አብዛኞቹ ሊቀበሉን ይቸገሩና እናንተ ከእኛ በምን ትሻላላችሁ ? የሚሉን እነርሱ ጋር የሚታየው ነገር በሙሉ እኛም ጋ አለና አንድ ስሙን መጥቀስ የማያስፈልገኝ ወንጌላዊ ሥፍራ ቀየርክ እንጂ ሕይወትህ አልተቀየረም  በፊት በቀድሞ ሕይወትህ እዚያ ታጭበረብር ነበረ አሁን ደግሞ አመንኩ ሕይወቴ ተቀየረና   የመሣሠሉትን ሆንኩ ትላለህ ብሶብህ ግን ታጭበረብራለህ ሲል ተናገረ ስለዚህ ወገኖቼ ዛሬ ለእኛም የሚያስፈልገን የስፍራ ለውጥ ሳይሆን የሕይወት ለውጥ ነው ሕይወታችን ሊለወጥ ያስፈልጋል ሕይወታችን ሲለወጥ አገልግሎታችን ይለወጣል ከዛ ውጪ ግን ሁሉም ነገር  ድካም ነው  አንዳንዶቻችንማ ዓይን ያወጣ ጥፋት ላይ ስላለን ክፋታችንን የሚገልጥብንና እውነቱንም የሚነግረንን ሰው አንወድም ከዚህ የተነሣ መምህር የሚለውን ስም ለብሶ  የሀገሬ ሰው ምሕረተአብ በግላጭ እንዳደረገው እኛም ለይቶልን እንደ ምሕረተ አብ መምህሩ ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት ስንል በየቪዲዮዎችና የማሰራጫ አውታሮች አንናገር እንጂ ልዩ ልዩ ትላልቅና ጃይንት የሆኑ የአገልግሎት ስሞችን ለብሰን በስማችን እያስፈራራንና ሥልጣናችንንም ተገን አድርገን ውስጥ ውስጡን ጓዳ ለጓዳ ሾተላችንና ስለታችንን የምንስል እንደገናም እኔን አይመስልም ፣ የኔን ሃሳብ አይቀበልም ፣ ስለኔም መልካም አይናገርም ስንል የምናስባቸውን ሰዎች ስም በማጥፋት አብዝተን የምናሳዽድ ፣ የምንጠላ ፣ የምንነድፍ ፣ የምንወጋ  ጥቂቶች አይደለንም  ሰይፋችንም ወደ ሥፍራው አልተመለሰም መጽሐፍ ያልተቀበልከውስ ምን አለህ የተቀበልክ ከሆንክ ግን እንዳልተቀበልክ የምትመካ ስለ ምንድነው ይለናልና 1ኛ ቆሮንቶስ 4 ፥ 7 ከዘለዓለም ሕይወት ጀምሮ እስከ አገልግሎት የጸጋ ስጦታ ድረስ ያሉት ስጦታዎችና ሌሎች የበረከት  ስጦታዎች በሙሉ የእኛ ሳይሆኑ የጌታ ናቸው ታድያ የእኛ ባልሆኑ በእነዚህ ነገሮች ሁሉ ጌታ ወደ እኛ መጥቶ እኛ ግን ምንም እንዳልተቀበልን በመሆን  በተራ ማንነትና በዓለማዊ ኑሮ ተጠላልፈን አይደለም የእግዚአብሔር ሰዎች ተብለን ልንጠራ አሁን ላይ ባለማወቅ ሕይወትና በሃይማኖት ቅነት ተይዘው ከሚያሳድዹት  ከነምሕረተአብ ባልተለየና ባልተናነሰ ሁኔታ ውስጥ አለን  በጥቂቱ ምናልባትም የቦታና የአለባበስ ልዩነት ሊኖረን ይችል ይሆናል ምክያቱም እርሱ እዚያ ነው እኛ እዚህ ነን እርሱ ያማረች መልክ ያላት ቀሚስና ባለዘለበት መስቀል እያለዋወጠ አንገቱ ላይ ያንጠለጥላል  እኛ ደግሞ ያማሩ ሱቶችን ከነከረባቶች እየለዋወጥን ሽቶአችንንም ተነስንሰን በየሰንበቱ  ልንሰብክና ልናስተምር በሕዝብ ፊት ተሰይመን እንቀርባለን  ይሁን እንጂ በቦታና በሁኔታ የተወሰንን ነንና ከሰሚዎቻችን መረዳትና የእምነት ልዩነት የተነሣ  ምንም እንኳ ስብከቶቻችን ልዩ ልዩ ዓይነት ቢሆኑም ከስብከቱና ከአገልግሎቱ መልስ ያለው ሾተላችንና ጎመዳችን ግን ፍጹም አንድ ዓይነት ነው እንደውም በየዋሕነትና በሃይማኖተኝነት ቅናት ውስጥ ተኲኖ  ከተመዘዘው ከምሕረተአብ ሰይፍ ይልቅ የእኛ ሰይፍ የባሰ ነው  አንዳንዴ እኮ እነ ምሕረተአብ ምን ያድርጉ ? እኛ በተመዘዘውና ወደ ሥፍራውም ባልተመለሰው በጴጥሮስ ሰይፍ ስለሆነ አገልግሎታችንን የምናካሂደው እነ ምሕረተአብም ከነ ሰይፋቸው ነው ያሉት ስለዚህ ማንን አይተው ሰይፋቸውን ይጣሉ ይህንኑ ሰይፋቸውን የራሴና የእኔ ብለው የያዙት ስለሆነ የራሳቸው ፣ የየግል መለያቸውና መታወቅያቸው አድርገውት   ከእኛ በተቃራኒው ቆመዋል   ወገኖቼ አገልጋዮችና የሐዲስኪዳን አማኞች በሙሉ የጴጥሮስ ሰይፍ እኮ በራሱ በጴጥሮስ ፈቃደኝነት ወደ ሥፍራው ተመለሰ እንጂ የእኛ ሰይፍማ ገና ወደ ሥፍራው ያልተመለሰ ስለሆነ ስንቱን ሰው በልቷል ፣ ስንቱን አወራርዷል ፣ የስንቱንስ ሰው ጆሮ ቆርጧል መሰላችሁ ሕዝባችን ሁሉ እኮ በእኛ ሰይፍ ተወግቶ ተቀልቶና ተቆርጦ ደምቷል ገናም እንደሚገባ ታክሞ ያላገገመ ስለሆነ  ብርቱ ቁስለኛ ነው በዚሁ በእኛው በተመዘዘበት ሰይፍ ምክንያትም በምሬት ሆኖ በልቅሶ በዋይታና በአቤቱታ ውስጥ ነው ያለው ይህ መቅላትና መቁረጥ ደግሞ ለአንዳንዶች የብሉኪዳን ሰባኪዎችና የጴጥሮስ ዘመን ሰዎች ልክ እንደ ጴጥሮስ ድንገተኛ ከሆነ የእንቅልፍ መባነን ውስጥ ወጥተው ስለሆነ የሚያገለግሉት  ጆሮ ቆራጮች ናቸው ስለሆነም በኢያሱ ዘመን ሳይቀር የተፈቀደ የሥጋ ግርዛት መስሏቸው ማገልገል ያለብን ከነ ሰይፋችን ሕዝብን እየቀለጠምንና እየቆረጥን ነው ብለው ከነሰይፋቸው ሊቀጥሉ ቢሞክሩም ታድያ  እኛ ግን ከወዲሁ ሳንፈቅድላቸውና ፋታም ሳንሰጣቸው ልናስቆማቸው ይገባል  ዛሬ ላይ ባለ የሐዲስኪዳን ዘመን ላይ ነውና ያለነው ግርዛቱ የሥጋ ሳይሆን ጌታ የሰጠን የመንፈስን ግርዛት ነው  ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3 : 3  ፣ 1ኛ ጢሞቴዎስ 3 ፥ 14 _ 16   ፣ ቆላስያስ 2 ፥ 11 _ 15 ፤ ሮሜ 2 ፥ 29  መግረዣውም የኢያሱ ዘመን ባልጩት ወይም ስለት ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ በጽኑ ልንነግራቸውና ይህንኑ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረን ልናስታጥቃቸው ይገባል ዕብራውያን 4 ፥ 12 ፤ ኤፌሶን 6 ፥ 13 እነርሱም እንዲህ የሚሉት ይህንንም የሚያደርጉት የሥጋን ሰይፍና የመንፈስን ሰይፍ ጠቀሜታ ለሕይወታቸው በውል ለይተው  ስላላወቁ  ነው  ወገኖቼ ! የእግዚአብሔር ቃል በሌለበት ቦታ ሁሉ ያለው  የሥጋ ሰይፍ  ስለሆነ የእግዚአብሔር ቃል የሌላቸው ሰዎች  ሁልጊዜ የሚመዙት ጴጥሮስ የመዘዘውን የሥጋ ሰይፍ ነው በመሆኑም በዚህ ምክንያት ሁልጊዜ በቤተ ክርስቲያን ብጥብጥ ይሆናል የተመዘዘው ሰይፍ ደግሞ የሥጋ ስለሆነ ገላጋይ እንኳ መሐል ሊገባ ችግር ነው በዚህም ሁኔታ ፖሊስ ሳይቀር ደርሶ የዘጋቸውን ያለጊዜያቸው የተከፈቱ ኪዮስክ ወይም ቡቲክ መሠል ቤተክርስቲያኖችን  በዘመኔ አውቃለሁ ሲከፈቱ በተጠሩ የክብር እንግዶች ሪቫኖቻቸው በመቀስ እየተቆረጡ በብዙ የሕዝብ ጭብጨባ ነው የተከፈቱት ሲዘጉ ግን  በሚያሳዝን ሁኔታ በሮቹ በፖሊስ ከማስጠንቀቅያ ጋር በሆነ መታሸግ ታሽገውና ሕዝብም ተበትኖ ተዘጉ በሆነውም ነገር በጊዜው ዓይኔ ያየና ጆሮዬም የሰማ በመሆኑ  ሃዘኔ እጅግ ጥልቅ ነበረ ውድ ወገኖቼ  ሆይ ለዚህ አሳፋሪና አስነዋሪ ጉዳይ የሚባለው ጌታ እግዚአብሔር ይቅር ይበለን  ይታደገን  ነው  ቤተክርስቲያንን እንደፈለግን እየሆንን ለግል ጥቅማችን የምንከፍታት የመገበያያ ጉሊታችን ወይም ሱቅ በደረቴ አይደለችም ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር መንግሥት ወኪል ስለሆነች የምትቋቋመው ለሥጋዊ ጥቅምና ፍላጎታቸው ባደሩ አገልጋዮች ምኞት ሳይሆን በእግዚአብሔር ዓላማና ፈቃድ ነው መንጋው ደግሞ ታናሽም ቢሆን መንግሥትን ሊሰጠው የአባቱ ፈቃድ የሆነለት ስለሆነ ሁሉም ሰው እንደ መጠራቱ መጠን በነፍስ ወከፍ የመንግሥት ልጅ ተብሎ የተሰበሰበ የእግዚአብሔር መንጋ ነውና አገልጋዮች እንዲሁ ከሜዳ ተነስተው በዘልማድ እንደ ጠፍ ከብት የሚነዱት አይደለም ፣ ሊሆንም አይገባም የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 16 _ 20 ፤ የሉቃስ ወንጌል 12  ፥ 32 እና 33 ፤ ቆላስያስ 1 ፥ 13 እና 14  ቤተክርስቲያን ደግሞ የእውነት ዓምድና መሠረት ስለሆነች የሕያው እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ናት ቅዱሳንም  በዚህ ቤት ውስጥ እንዴት መኖር እንደሚገባቸው ያውቁ ዘንድ ተጽፎላቸዋል 1ኛ ጢሞቴዎስ 3 ፥ 14 እና 15 ታድያ እኛ ቅዱሳን በተጻፈው በዚህ እውነት ልክ ስንኖር ነገሮች ሁሉ መልክ ይይዛሉ የተዛቡ ነገሮችም  ይስተካከላሉ ቤተክርስቲያንም እንደገና ወደ ትክክለኛ መንፈሳዊ ይዘትዋና መሠረትዋ ወደ ቀደመ ክብርዋና ማንነትዋም   ትመለሳለች እንደገናም ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቊጣም የዘገየ ይሁን የሰው ቊጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራምና ተብሎ የተጻፈልን በመሆኑ ያዕቆብ 1 ፥ 20 እና 21  እውቀት በጐደለውና ባዶ በሆነው ቅንዓት ተሞልተው የሚነሱ ሰዎች በትክክለኛው የአገልግሎት ሕይወት ሊማሩ ፣ ሊለወጡ ሊስተካከሉና ሊቀረጹ ራሳቸውን ይሰጣሉ እንጂ ከዚህ በኋላ ባለና በሚመጣ ትውልድ መካከል እየደነፉ ፣ እየተቆጡ ፣ ጆሮም እየቆረጡ አገልግሎት ስለሌለ አያገለግሉም እያልኩ ነው አለበለዚያም ደግሞ ይሄ ሁሉ ቀርቶባቸው  ይሰናበታሉ ማለትም እንዳያገለግሉ ይሆናሉ  ለምን ስንል መንፈሳዊ ግልጋሎት የቃልና የኑሮ ምሳሌነት የታከለበት እንጂ ድንፋታና ቊጣ በተሞላበት የክተት ሠራዊት  በመጣልህና በወዮልህ መንፈስ ተሞልቶ ለጆሮ ቆረጣ የሆነ መነሣሣት አይደለም ያለፈው ዘመን ይብቃችሁ ተብለናልና ሮሜ 10 ፥ 1 _ 4 ፤ 1ኛ ጴጥሮስ 4 ፥ 1 _ 4 ቤተክርስቲያንን ወደ ቀደመ መንፈሳዊ ይዘትዋና መሠረትዋ የሚመልሳት የሰዎች ቊጣና በእውቀትም ያልሆነ  የቅንዓት እርምጃ ሳይሆን መሠረታዊ የሆነ የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት ነው ስለዚህ ልዩነት ሳይኖር ሁላችንም ድንፋታውንና ቀረርቶውን እኔ እበልጥ ባይነቱንና ምታ ነጋሪቱን ትተን  ሊገነባን ወደሚችለው ወደ እግዚአብሔር ቃል ትምህርትእንድንመለስ እግዚአብሔር ይርዳን መልዕክቴን ጨርሻለሁ ሰላም ሁኑ ተባረኩ

ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry 



ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ 

Friday 17 February 2017

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: የግጥም መነባንብ የግጥሙ ርዕስ ፦ እስመ ተዐረዩ ፣ እስመ ተዐረዩከእኔ ...

Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: የግጥም መነባንብ 
የግጥሙ ርዕስ ፦ እስመ ተዐረዩ ፣ እስመ ተዐረዩ



ከእኔ ...
: የግጥም መነባንብ   የግጥሙ ርዕስ ፦ እስመ ተዐረዩ ፣ እስመ ተዐረዩ ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በ...

የግጥም መነባንብ 


የግጥሙ ርዕስ እስመ ተዐረዩ እስመ ተዐረዩ


Related image


ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም.............. እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና  ይለናል  ( ዘጸአት 20 3 _ 6  )






እስመ ተዐረዩ  እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ አሉ ግነዩ ግነዩ 

የተመረጡ ግን የተለዩ የሉም 

ኃጢአት ነግሦበታል ፍጥረታዊው ዓለም 

በጨለማው ገዢ ፍጥረት ተንከራቶ 

ከፍርድ በታች ሆኖ ምላሱ ተዘግቶ 

ሁሉ ኃጢአት ሠርቷል የእግዜር ክብርም ጎድሏል 

ኃያሉ አምላካችን በቃሉ ተናግሯል 

እስመ ተዐረዩ ከወዴት ይመጣል ?

በክብሮሙም ብንል ሐሰት ያስብለናል 

ስብሐተ ፈጣሪስ የሚገባው ማነው ?

ከአምላካችን በቀር ያለ የሚኖረው 

ፍጹም የለምና ለእርሱ የተሳነው 

መጽሐፉ ያላለውን ለምን እንላለን ?

ላንጨምር ላንቀንስ ቃሉ ወስኖብን 

ላልተገባ ነገር ተላልፎ ያሰጠናል 

ዕድል ፈንታችንም ከቅድስቷ ሀገር ከጽዮን ይጎላል 

ከመጽሐፉ ውጪ የከንቱ ነው ከንቱ 

ፍጹም አታንብቡ እንዳትሳሳቱ 

ያልተጻፈ ሲያነብ በለመደው ሰይጣን 

ሔዋን ተታለለች ሃሳቡን በማመን 

እውነት የሚመስል ውሸት ነገር አለው 

መጀመርያም ሰይጣን የሐሰት አባት ነው 



Image result for you shall not make for yourself a carved image


ወእምዝ ይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ ሑር እምድኅሬየ ሰይጣን ጽሑፍ ለእግዚአብሔር አምላክከ ትስግድ ወኪያሁ ባሕቲቶ ታምልክ 

ወንጌል ዘማቴዎስ ምዕራፍ ቊጥር  



ያን ጊዜ ኢየሱስ ሂድ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እር ሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና አለው 


የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 4 10 







የተወደዳችሁ ወገኖች የፌስቡክ ጽሑፎቼንና የመነባንብ ግጥሞቼን እንዲሁም በቪዲዮ የሚለቀቁትን መልዕክቶችና ትምህርቶችን ሁሉ የምትከታተሉ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ሕዝቦች በሙሉ የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ በዛሬው ዕለት እስመ ተአረዩ  እስመ ተዐረዩ ትርጉም  ተመርጠዋልና ፣  ተመርጠዋልና የሚለውን የግጥም መነባንብ ያቀረብኩት ለኦርቶዶክሳውያን አማኞች ትምህርት ለመስጠት ቢሆንም መልዕክቱ ግን ሁላችሁንም አንባቢዎች የሚመለከት ስለሆነ በማስተዋል እንድትከታተሉ በጌታ ፍቅር ሆኜ ለማሳሰብ እወዳለሁ 

ይሄ ግጥም የተዘጋጀው በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መስከረም 17 ዕለት በሚከበረው የመስቀልና የደመራ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከሚጸለየው የመስተብቊዕ ጸሎት በከፊል  ተወስዶ ነው  ይህ የመስተብቊዕ ጸሎት ይህንን በዓል ምክንያት በማድረግ ከፍ ባለ ድምጽና ዜማ የበዓሉ ተረኛ ቄስ ሆኖ በተሰየመው ገባሬ ሰናይ ቄስና ገባሬ ሰናይ ዲያቆን የሚዜም ቢሆንም ከዚህ በዓል ባሻገር በሌሎች ጊዜያቶችም ከበዓሉ ጋር የተገናኙ ማለትም መስቀል ተኮር በዓላት ሲኖሩም ይህ የመስተብቊዕ ጸሎት በጸሎትና በዜማም መልክ ሆኖ ይጸለያል ይዜማል ጸሎቱም መስተብቊዕ ዘመስቀል በመባል ይታወቃል መስተብቊዕ የግዕዝ ቃል ሲሆን መስተብቊዕ ማለት መማለድ መለመን ማለት ነው አስተበቁአ ማለደ ለመነ ከሚለው የግዕዝ ግሥ ወይንም አረባብ  የመጣ ነው ሃሳቡን ስጠቀልለው መስተብቊዕ ዘመስቀል ማለት የመስቀል የምልጃ ወይንም የልመና ጸሎት ማለት ነው ታዽያ በዚህ የመስቀል የልመና ጸሎት ውስጥ በእንተ ዝንቱ አዘዙ መምህራነ ቅዱስ ወንጌል አምሳለ ፈጣሪ ልዑል ንስግድ ለመስቀል ወለማርያም ድንግል የሚለው ቃል ተጽፎ እናገኝበታለን ወደ አማርኛው ስተረጉመው የልዑል ፈጣሪ ምሳሌ ለሆኑት ለማርያምና ለመስቀል እንስገድ የሚል ነው ለምን ስንል የቅዱስ ወንጌል መምህራን አዘውናልና ይለናል እንደገናም በመቀጠል የጸሎት መጽሐፉን እንደዚሁ ወረድ ብለን ስናነበው  እነዚሁ የቅዱስ ወንጌል መምህራን የተባሉት የልዑል  ፈጣሪ ምሳሌ ለሆኑት ለማርያምና ለመስቀል እንስገድ ሲሉ ያዘዙበትን ምክንያት ይናገራል ውድ ወገኖቼ ሆይ ታድያ እኔም በግጥሙ መነባንቤ ላይ ይህንን ምክንያት መነሻ በማድረግ ነው እስመ ተአረዩ  እስመ ተአረዩ ትርጉም  ተመርጠዋልና ተመርጠዋልና  የሚለውን የግጥሙ ዋነኛ አርዕስ አድርጌ  ሃሳቤን በግጥም መልክ ላቀርብላችሁ የወደድኩት  ታድያ እነዚሁ የቅዱስ ወንጌል መምህራን የልዑል የፈጣሪ ምሳሌ ለሆኑት ለማርያምና ለመስቀል እንስገድ ሲሉ ያዘዙበትን ምክንያት መጽሐፉ ሲዘረዝርልን እንዲህ አለ ለእሉ ክልዔቱ ( ፪ቱ ) ፍጡራን ስብሐተ ፈጣሪ ይደልዎሙ እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለመ ዓለም አሜን ይለናል ወደ አማርኛው ስተረጉመው ለሁለቱ ፍጡራን ማለትም ለማርያም እና ለመስቀል የፈጣሪ ምሥጋና ይገባቸዋል በክብራቸው ተመርጠዋልና ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ አሜን ይላል የጸሎት መጽሐፉ እንግዲህ እነዚህ የቅዱስ ወንጌል መምህራን የልዑል ፈጣሪ ምሳሌ ለሆኑት ለመስቀልና ለማርያም እንድንሰግድ ያዘዙት በክብራቸው ስለተመረጡ ነውና የፈጣሪ ምሥጋና ከዛሬ ጀምሮ እስከ ለዘላለሙ ይገባቸዋል ስለዚህ ስግደቱንም ሆነ ምሥጋናውን ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ጋር በእኩልነት ስጡአቸው እንጂ እንዳታሳንሱአቸው እያሉን ነው በመሆኑም ታድያ የእነዚህ የቅዱስ ወንጌል መምህራን ትዕዛዝ ትክክለኛ ከወንጌል ቃልና ከቅዱስ መጽሐፍ የወጣ  ትዕዛዝ ነው ወይ ? እነዚህስ የቅዱስ ወንጌል መምህራን የተባሉት ትክክለኛ የወንጌል መምህራን ናቸው ? ወይስ የሌላ ? ስንል መልሱን መጽሐፍቅዱሳችን በተገቢው መንገድ ግልጽ አድርጎ ይመልስልናል  ለምን ስንል እምነት ከመስማት  መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ ከእግዚአብሔር ቃል የወጣ እምነት ለእኛ በፍጹም  የለንምና ነው ሮሜ 10 17 እንመልከት በዚህ የጸሎት መጽሐፍ ውስጥ እነዚህ የቅዱስ ወንጌል መምህራን በተናገሩት መሠረት ማርያምና መስቀል የልዑል ፈጣሪ ምሳሌ ናቸውና ስግደትም ሆነ የፈጣሪ ምሥጋና  ይገባቸዋል የሚል በመጽሐፍቅዱሳችን ውስጥ የተጻፈ አንድም ቦታ የለም ፈጣሪ አምላካችንንም የሚመስለው በምድርም ሆነ በሰማይ ምንም ዓይነት ፍጥረት የለም እንደገናም ፍጥረት ፍጥረት ነው ፈጣሪ ደግሞ ፈጣሪ ነውና በምንም መልኩ አመሳስለን ምስጋናም ሆነ ስግደት የምናቀርብለት ፍጥረት በምድርም ሆነ ከምድር በታች እንዲሁም በሰማይ ባሉ ፍጥረታት መካከል የለም ጌታም በትንቢተ ኢሳይያስ 46 : 5 ላይ በማን ትመስሉኛላችሁከማንስ ጋር ታስተካክሉኛላችሁእንመሳሰል ዘንድ ከማን ጋር ታስተያዩኛላችሁ?ብሎናል መቼም አንዳንዴ አይታወቅምና ድንገት አንዱ ሾጥ  ያረገው   ሾልኮና ሞቅም ብሎት ይህንን የፈጣሪ ምሥጋና እና ስግደት እኔም ያስፈልገኛልና  ልቀበል  ብሎ ቢነሳ ክብሩን ለሌላ ምሥጋናውንም ለተቀረጹ ምስሎች መስጠት የማይፈልግ ጌታ ወዲያው በቅጽበት ያዋርደዋል እርምጃንም ይወስድበታል እንጂ ፍጹም አይተወውም ይህንንም  እኔ እግዚአብሔር ነኝ  ስሜ ይህ ነው ክብሬን ለሌላ ምሥጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም ሲል በቃሉ ተናግሯል ትንቢተ ኢሳይያስ 42  8 ደግሞም በክብሩ የሚመጣበትን አይወድምና ይህ አይሆንልኝም ብሏል 1ኛ ሳሙኤል 2 ፥ 30  እንደገናም በዘጸአት 20  3 _ 6 ላይ ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም፤ በሚጠሉኝ እስከ ሦስተኛና እስከ አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና  ይለናል በዘዳግም  4  15 _ 24  ላይ እግዚአብሔር በኮሬብ በእሳት ውስጥ ሆኖ በተናገራችሁ ጊዜ መልክ ከቶ አላያችሁምና እጅግ ተጠንቀቁ እንዳትረክሱ፥ የተቀረጸውን ምስል የማናቸውንም ነገር ምሳሌ፥ በወንድ ወይም በሴት መልክ የተሠራውን……… አለን በዮሐንስ ወንጌል  4  22 _ 24 ላይ ደግሞ እናንተስ ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ ፤ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና ለምናውቀው እንሰግዳለን ነገር ግን በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አሁንም ሆኖአል፤ አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል ይለናል ከእነዚህ እና ከመሣሠሉት ቃሎች የተነሳ ታድያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለምና  ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ ስለተባልን ከእርሱ በቀር ሌሎች አማልክት የሉንም አይሆኑልንምም  የተቀረጸውንም ምሳሌ ለእኛ አናደርግም  አንሰግድም  አናመልክምም ደግሞም መልክ አላያችሁምና ተጠንቀቁ ተብለናልና ስለዚህ ይህንን አምላካችንን የምናመልከው መልክ አይተን  ቅርጽና ምስል አበጅተን  ሥዕሎችንም ስለን  በቤታችንም አምጥተን በመስገድና በማምለክ አይደለም እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ የምናመልከው በእውነትና በመንፈስ ነው ስለዚህ ወገኖቼ እነዚህ የቅዱስ ወንጌል መምህራን ናቸው የተባሉት ታድያ ከየት አምጥተው ነው ለሁለቱ ፍጡራን ለማርያምና ለመስቀል የፈጣሪ ምሥጋና ይገባቸዋልና እንስገድላቸው በክብራቸው ተመርጠዋልና ሲሉ ያዘዙን ? በቅዱስ ወንጌሉ ላይ ስናይ ለእነዚህ ፍጡራን የፈጣሪ ምስጋና ስጡ ስገዱ የሚል ቃል አላነበብንም አማልክት አይኑርህ  አትስገድላቸው  አታምልካቸውም የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ  አታምልክ  መልክ አላየህም ፣ ምስልን ለአንተ አታድርግ  እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ በእውነትና በመንፈስ አምልክ ነው የሚለን ቃሉ ስለዚህ ችግሩ ያለው በመጽሐፍቅዱሳችን ቃል መሠረት  የቅዱስ ወንጌል መምህራን  የተባሉት ጋር ነው በመሆኑም እነዚህ የቅዱስ ወንጌል መምህራን የተባሉት ትክክለኛ ያልሆኑና ያልተጻፈ የሚያነቡ ስለሆኑ እንደ ወንጌሉ ቃል እንደ መጽሐፍቅዱሱም እውነት የተሳሳቱ እና አሳሳች መምህራን ናቸው  እንጂ የቅዱስ ወንጌል መምህራን አይደሉም ስለዚህ እኛም  ትዕዛዛቸውን አንቀበልም ሌሎችም እንዳይቀበሉ በእንዲህ መልኩ እንናገራለን ፣ እናስተምራለን  እናስጠነቅቃለን ሐዋርያው ጳውሎስም ለዚህ ነው በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌል ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን እላለሁ  ያለን  ገላትያ 1  6 _ 9  ወገኖቼ ሆይ ልዩ ወንጌል በገላትያ ክርስቲያኖች ዘመን ብቻ ሳይሆን ዛሬም የቅዱስ ወንጌል መምህራን አዘዙን በተባለው መንገድ የሚታመንና የሚደረግ  ሁሉ  አሁንም ልዩ ወንጌል ነውና እኛም  እንደ ጳውሎስ እንዲህ ያለውን አስተምህሮ እንዲሁ የተረገመ ይሁን እንላለን የተጠራንበትም ሆነ የዳንበት ወንጌል የክርስቶስ የጸጋው ወንጌል በመሆኑ ፊታችንን የምናዞርበት የተለየ ወንጌል የለንም  እንደገናም  መዳን በሌላ በማንም ስለሌለ የምንድነው በኢየሱስ ብቻ ነው ስግደት አምልኮም የሚቀርበው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለእግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ ከእግዚአብሔር ውጪ ለሌላ አንሰግድም ሌላም አናመልክም የሐዋርያት ሥራ 4  12  ፊልጵስዩስ 2  9 _ 11  1 የጴጥሮስ መልእክት 4 : 11  የማቴዎስ ወንጌል 4  10 እና 11 ወደ ግጥሜና የመነባንቤ ሃሳብ ስመልሳችሁ ደግሞ የግጥሜ  ጥቂቱ ሃሳብ የግዕዝ ቃላቶች የተቀላቀሉበት በመሆኑ እንደሚከተለው ልተረጉመው እወዳለሁ እስመ ተዐረዩ እስመ ተዐረዩ  በክብሮሙ አሉ ግነዩ ግነዩ ያልኩት ግነዩ ማለት አመስግኑ ማለት ሲሆን ገነየ አመሰገነ ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ በመሆኑ እስመ ተዐረዩ እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ አሉ ግነዩ ግነዩ ማለት እነዚህ የፈጣሪ ምሥጋና ይገባቸዋልና እንስገድላቸው የተባሉት ማርያምና መስቀል የወንጌል መምህራኑ እንዳዘዙትም ሆነ ደራሲው እንዳለው      " ተመርጠዋልና  ተመርጠዋልና  በክብራቸው ! አመስግኑ አመስግኑ አሉ "የሚለውን ሃሳብ ስለሚይዝልኝ ነው ይህንን ለግጥሜ እንደ ዋና አርዕስት አድርጌ  የግጥሜ ወይም የመነባንቤ የመጀመርያና የመነሻ ሃሳብ እንዲሆን የወሰድኩት ቢሆንም መጽሐፍቅዱሳችን ግን አሁንም    ሁሉ ኃጢአትን ከመስራቱ የተነሳ የእግዚአብሔር ክብር የጎደለው ነውና በክብሩ የተመረጠም ሆነ አልፎ ሄዶ የፈጣሪ ምሥጋናን የተቀበለ  የፈጣሪም ምሥጋና ሊሰጠው ሊሰገድለት የተገባ ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ የለምና  በማለት የመስተብቊዕ ዘመስቀልን ሃሳብ በእንዲህ መልኩ አፍርሶታልና የመጽሐፍቅዱሱ ሃሳብ የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ የእግዚአብሔር ቃል ያለንን ብቻ ሰምተንና ይዘን እርሱን እግዚአብሔርን እንከተል ለማለት ይህቺ መልዕክት በግጥም መልክና የታሪኩን ይዘትም ጠብቆ በሚያብራራ መጽሐፍቅዱሳዊ የቃል ገለጻ ተዘጋጅታ ወደ እናንተ ደርሳለች   አነሳስቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስፈጸመን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው አሜን 


Image result for turning to a different Gospel




«Do not turn to a different gospel» 



«ወደ ልዩ ወንጌል አትመለሱ»



Image result for turning to a different Gospel


Image result for turning to a different Gospel












ወይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ 


የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ 


ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry 


ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ