Wednesday 11 September 2019

እንኩዋን አደረሳችሁ 2012 የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት እንቁጣጣሽ የክፍል አንድ ዝግጅትወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም ወይረውዩ አድባረ በድው በቸርነትሕ ዓመትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ መዝሙር 64 ( 65 ) ፥ 9 - 13 የተወደዳችሁ ወገኖች ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ኤርትራውያን እንኩዋን ከዘመን ዘመን አሸጋገራችሁ አዲሱ ዓመት የበረከት የተድላና የደስታ ዓመት ይሁንላችሁ በማለት ምኞቴን እየገለጽኩ ዘመን የሚለወጥበት የመስከረም ወር ዘር ዘርተው ተክል ተክለው የሚኖሩ ሐረስተ ምድር በክረምት የዘሩትን ዘር አሽቶ አፍርቶ ምድርም በልምላሜ ተጊጣ እንስሳትም ለምለሙን ሣር ግጠው ጽሩውን ውኃ ተጎንጭተው ጠግበው አምረው የሚታዩበት የልምላሜ የፍሬ ወር ነው። “ምድርን ጐበኘሃት አጠጣሃትም፥ ብልጥግናዋንም እጅግ አበዛህ፤ የእግዚአብሔርን ወንዝ ውኃን የተመላ ነው፤ ምግባቸውን አዘጋጀህ እንዲሁ ታሰናዳለህና ትልምዋን ታረካለህ፥ ቦይዋንም ታስተካክላለህ፤ በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ፥ ቡቃያዋንም ትባርካለህ ይለናልና ስለዚህ ዓመታቱን በቸርነቱ የለወጠ የበረከት እጁንም ሳያጥፍ ፍጥረትን ሁሉ የመገበ የሠራዊቱ ጌታ እግዚአብሔር ስሙ የተባረከ ይሁን ከዚህ በመቀጠል ይህንን የተለቀቀ የእንቁጣጣሽን በዓል አስመልክቶ የተዘጋጀ የክፍል አንድ መልዕክት ተከታተሉ ተባረኩ

No comments:

Post a Comment