Friday 15 February 2019

Grassmayr Glocke Berg Tabor schwingend

Grassmayr Glocke Berg Tabor schwingend

የትምህርት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ሦስት )

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 13 ) እርሱም ሁሉንም እክዳለሁ ማርያምን ግን አልክድም አለ!!! የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ለእናንተ ይሁን በተአምረ ማርያም 110 ቁጥር 7 ላይ ጥብርያዶስ ስለሚባል ስለ አንድ ነጋዴ ይናገራል :: ይህንንም የምታገኙት በተአምረ ማርያም 123ኛው እትም ላይ ነው :: ይህ ጥብርያዶስ ሃብታም የነበረ ነጋዴ ነበርና ወንድና ሴት ባሮች ነበሩት :: ይሁን እንጂ ሃብታም ቢሆንም በሃብቱ ደኸየ ታድያ ሰይጣን በድህነቱ መጥቶ ሥላሴን ክርስቶስን ማርያምን ካድ አለው:: እርሱም ሁሉንም እክዳለሁ ማርያምን ግን አልክድም አለ:: በዚህ ሁኔታ የሚሞትበት ጊዜ መጥቶ ማርያምም እንደ ልማድዋ መጣችለትና ልጅዋ ወዳጅዋን ይህን ሰው የማትምርልኝ ከሆነ ጡቶቼን እቆርጣለሁ ፊቴንም እቆራርጣለሁ አለችው :: እርሱም ስለዚህ ነገርዋ ማረላት ይለናል :: በመሆኑም ታድያ ይሄ መጽሐፍ አቅሉን የሳተ የሰይጣን መጽሐፍ መሆኑን የምናውቅባቸው መንገዶች ብዙ ናቸው :: አንደኛ ማርያም ማርልኝ አለበለዚያ ጡቴን እቆርጣቸዋለሁ የምትለው በሰማይ የክርስቶስን ጽኑ ፍርድ በማስፈራራት ልጅዋን ልታስለውጥ ብላ ነው ይለናል መጽሐፉ :: ሌላው ደግሞ አሁንም መጽሐፉ ማርያምን ጡትዋን የምትቆርጥበትን ቢላዋ ፣ ሰይፍም ይሁን መቀስ ይዛለች እያለን ነው:: ታድያ በሰማይ ጡትም ሆነ ጡት የሚቆረጥበት ቢላዋ ሰይፍም ሆነ መቀስ አለን ? ይህ ደግሞ ከትንሣኤ በሁዋላ ስለሆነ ፍጥረታዊ ሰውነት የለምና ማርያምን ጡት ነበራት ስንል ልንናገር አንደፍርም :: ከዚህም ሌላ ይህም ሰው ክርስቶስንና ሥላሴን ክዶ ማርያምን አልክድም ስላለ በማርያም ኢየሱስን አስፈራሪነት ምህረት አገኘ ልንል አንችልም :: ኢየሱስ እንዲህ በቀላሉ ፍርዱንም ሆነ ሃሳቡን የሚለውጥ ጌታ አይደለም ትክክለኛዋ የኢየሱስ እናት ማርያምም ሰዎች ሁሉ ለኢየሱስ እንዲታዘዙና የዘላለም ሕይወት ባለቤቶች እንዲሆኑ የሚላችሁን አድርጉ ትላለች እንጂ በሰማይ መቀስ ይዛ ይህንን ሰው ካልማርክልኝ ጡቴን እቆርጣቸዋለሁ የሚል ቃል በማውጣት ኢየሱስን አላስፈራራችም ፣ አታስፈራራውምም ፣ አስፈራርታም ፍርዱን አላስለወጠችውም ፣ ወደፊትም አታስለውጠውም ይልቁንም እርስዋ ራስዋ በክርስቶስ ኢየሱስ አምና የዳነች አማኝ በመሆንዋ ይህንን የጨለማ ሃሳብ ጨርሶውንም አታስበውም :: የተወደዳችሁ ወገኖች በዛሬው ትምህርታችን እንግዲህ ይህንን የተአምረ ማርያም የትረካ ሃሳብ አንስተን ኦርቶዶክሳውያኑ ወገኖቻችን በመጽሐፍቅዱስ ላይ የተጻፈላትን ማርያምን ከማመን ይልቅ በተአምረ ማርያም ላይ የተጻፈላትን ማርያም በማመናቸው ምክንያት የሚቸገሩበትን ወደ ሁለት የሚደርሱ ነጥቦች በየተራ ተመልክተናል:: 1ኛ ) ማርያምን መካድ የሚፈልግ ሰው ማንም ባይኖርም ኦርቶዶክሳውያኑ ግን ማርያምን አንክድም የምንለው ትልቁ ምክንያታችን ያለ ወላዲተ አምላክ አማላጅነት ዓለም አይድንም ብለን ስለምናምን ነው ብለው ይረዳሉ ደግሞም ይናገራሉ 2ኛ ) ያለ እመቤታችን ማርያም ሥላሴ አይታወቅም ይላሉ ታድያ እኛም እነዚህን ሁለት ነጥቦች አንስተን በመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ዳኝተነዋል የተለቀቀውን ቪድዮ በመስማት ትምህርቱን ተከታተሉ ታድያ አሁንም ትምህርቱ ያላለቀ በመሆኑ ተከታዩን በሚቀጥለው አቀርባለሁ እስከዚያው የጌታ ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን የምላችሁ ወንድማችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ ነኝ ተባረኩልኝ

Tuesday 12 February 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ ቸርነቱን በሕያዋንና በሙታን ላይ አልተወምና በእግዚአብሔር የተባረከ ይሁንየመልዕክት ርዕስ ፦ ቸርነቱን በሕያዋንና በሙታን ላይ አልተወምና በእግዚአብሔር የተባረከ ይሁን መጽሐፈ ሩት 1 : 19 - 22 ፤ መጽሐፈ ሩት 2 : 20 የተወደዳችሁ ወገኖችና የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ተንከራታች የሆነችዋ ኑኃሚን ፣ እግዚአብሔር አዋርዶኛልና ባዶዬን መለሰኝ ስለዚህ ማራ በሉኝ እንጂ ኑኃሚን አትበሉኝ ስትል ስሟን ሳይቀር መለወጥ የፈለገችው ኑኃሚን ፣ እንደገና ተመልሳ « በጎነቱን ለሕያዋንም ሆነ ለሙታን ማድረግን ያልተወ እግዚአብሔር ይባርከው » በማለት የበጎነት አምላክ የሆነውን እግዚአብሔርን አንስታ ቦዔዝን የባረከችበትን ምስጢር ዛሬ ተመልክተናል ከዚህ የተነሳ ኑኃሚን በእግዚአብሔር ቸርነት ታግዛ ከእንዲህ ዓይነቱ የተስፋ መቁረጥ ሕይወት ነጻ የወጣችበትን የሚጠቁሙ ተዛማጅ ቃሎችን እንደሚከተለው አቅርቤያለሁና ተከታተሉ በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ ቃሌም ወደ እግዚአብሔር ነው፥ እርሱም አደመጠኝ በመከራዬ ቀን እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤ እጆቼ በሌሊት በፊቱ ናቸው፥ አላረፍሁምም፥ ነፍሴም መጽናናትን አልቻለችም እግዚአብሔርን አሰብሁት ደስ አለኝም፤ ተናገርሁ፥ ነፍሴም ፈዘዘች ዓይኖቼ እንዲተጉ ያዝሃቸው፤ ደነገጥሁ አልተናገርሁም የዱሮውን ዘመን አሰብሁ፤ የዘላለሙን ዓመታት አሰብሁ፤ አጠናጠንሁም በሌሊት ከልቤ ጋር ተጫወትሁ፥ ነፍሴንም አነቃቃኋት እግዚአብሔር ለዘላለም ይጥላልን? እንግዲህስ ቸርነቱን አይጨምርምን? ለዘላለምስ ምሕረቱ ለልጅ ልጅ ተቈረጠችን? የተናገረውስ ቃል አልቆአልን? እግዚአብሔርስ ሞገሱን ረሳን? በቍጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን? ይህ ድካሜ ነው አልሁ፥ የልዑል ቀኝ እንደ ተለወጠ የእግዚአብሔርን ሥራ አስታወስሁ፤ የቀደመውን ተአምራትህን አስታወሳለሁና በምግባርህም ሁሉ እናገራለሁ፥ በሥራህም እጫወታለሁ አቤቱ፥ መንገድህ በመቅደስ ውስጥ ነው፤ እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማን ነው? ተኣምራትን የምታደርግ አምላክ አንተ ነህ፤ ለሕዝብህ ኃይልን አስታወቅሃቸው ( መዝሙረ ዳዊት  77 : 1 - 14 )   እንደ ኃጢአታችን አላደረገብንም፥ እንደ በደላችንም አልከፈለንም ( መዝሙረ ዳዊት 103 : 10 ) ሁለታችሁን ከማጣ ተብሎ በእናቱ አማካኝነት ወደ አጎቱ ቤት የተላከ በአጎቱም በላባ ቤት ደሞዙ የተለዋወጠና የተነጠቀ ያዕቆብ ከመከራው ብዛት የተነሳ ሥፍራ ሳይለውጥ በዛው በአጎቱ ቤት እንዳለ እግዚአብሔር በሕይወቱ ጣልቃ ገብቶ ቸርነትን አደረገለት ስለዚህም የላባ ልጆች ይህን አሉት ያዕቆብም የሚከተለውን ሃሳብ ሰነዘረ ( ዘፍጥረት 31 : 5 - 14 ፤ 42 ) ከወንድሙም ጋር ተገናኝቶ እንዲህ ሲል ተናገረ ( ዘፍጥረት 33 : 11 ) ኢየሱስ መልሶ፦ የእግዚአብሔርን ስጦታና፦ ውኃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን መሆኑንስ ብታውቂ፥ አንቺ ትለምኚው ነበርሽ የሕይወትም ውኃ ይሰጥሽ ነበር አላት ( የዮሐንስ ወንጌል  4 : 10 ) የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ ( 2ኛ ቆሮንቶስ   8 : 9 ) እኛ ደግሞ አስቀድመን የማናስተውል ነበርንና፤ የማንታዘዝ፥ የምንስት፥ ለምኞትና ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎች የምንገዛ፥ በክፋትና በምቀኝነት የምንኖር፥ የምንጣላ፥ እርስ በርሳችን የምንጠላላ ነበርን ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው ቃሉ የታመነ ነው ( ቲቶ  3 : 3 - 8 ) እነሆ፥ ለዳዊት ጻድቅ ቍጥቋጥ የማስነሣበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፥ እርሱም እንደ ንጉሥ ይነግሣል፥ ይከናወንለታልም፥ በምድርም ፍርድንና ጽድቅን ያደርጋል በዘመኑም ይሁዳ ይድናል እስራኤልም ተዘልሎ ይቀመጣል፥ የሚጠራበትም ስም፦ እግዚአብሔር ጽድቃችን ተብሎ ነው ስለዚህ፥ እነሆ፦ የእስራኤልን ልጆች ከግብጽ ምድር ያወጣ ሕያው እግዚእግዚአብሔርን! ዳግመኛ የማይባልበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር ነገር ግን፦ የእስራኤልን ቤት ዘር ከሰሜን አገርና ካሰደድኋቸውም አገር ሁሉ ያወጣና የመራ ሕያው እግዚአብሔርን ይባላል በምድራቸውም ይቀመጣሉ ( ትንቢተ ኤርምያስ  23 : 5 - 6 ) ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ  

Saturday 9 February 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ክፍል ሁለት )

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ክፍል ሁለት )

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ክፍል ሁለት )

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ክፍል ሁለት )

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ክፍል ሁለት )

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተፈተነና ዝም ያላለ ራዕይ ወደ ፍጻሜው ይቸኩላል ( ክፍል ክፍል ሁለት )

Monday 4 February 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ ያልተያዘና ያልተነካካ ነገር ይሰጥሃልና አንተም አትነካካ ( ክፍል አንድ ) የመልዕክት ርዕስ ፦ ያልተያዘና ያልተነካካ ነገር ይሰጥሃልና አንተም አትነካካ ( ክፍል አንድ ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ዛሬ ዘፍጥረት ምዕራፍ 24 ን በሙሉ የትምህርታችን ዋና ሃሳብ በማድረግ ተመልክተነዋል :: የርብቃ ቤተሰቦች ርብቃን ሚስት አድርገው ሲሰጡ እንዲህ ነበር ያሉት :: ላባና ባቱኤልም መለሱ እንዲህም አሉ፦ ነገሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቶአል ክፉም በጎም ልንመልስልህ አንችልም ርብቃ እንኋት በፊትህ ናት ይዘሃት ሂድ፥ እግዚአብሔር እንደ ተናገረ ለጌታህም ልጅ ሚስት ትሁን የአብርሃምም ሎሌ ነገራቸውን በሰማ ጊዜ ወደ ምድር ወድቆ ለእግዚአብሔር ሰገደ ሎሌውም የብርና የወርቅ ጌጥ ልብስም አወጣ፥ ለርብቃም ሰጣት የከበረ ስጦታንም ለወንድምዋና ለእናትዋ አቀረበ ይለናል ዘፍጥረት ምዕራፍ 24 ፥ 50 - 53 ውድ ወገኖቼ ያልተያዘና ያልተነካካ ሕይወት ከእግዚአብሔር ለመሆኑ የርብቃ ቤተሰቦች የሆኑት ላባና ባቱኤልም ሆኑ ልጃቸው ርብቃ እንዲሁም የአብርሃም ሎሌ ጽኑ ምስክሮች ናቸው :: ስለዚህ ዛሬም በእኛ ዘመን ሥራ ፣ ሕይወት ፣ እጮኝነት ፣ ትዳር አገልግሎትና የመሣሠሉት ሁሉ ከእግዚአብሔር ሲሆኑ ያልተነካኩ የሰውንም ሆነ የእያንዳንዳችንን ነገር ነገር ጣልቃ ያላስገቡ ይሆኑና ከእግዚአብሔር ብቻ ሆነው ለእኛ ይሰጣሉ ታድያ በዚያ ውስጥ በረከት እንጂ ልቅሶም ሆነ ሃዘን የለበትም ለዚህም ነው የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም ያለን መጽሐፈ ምሳሌ 10 ፥ 22 ትምህርቱ ዘፍጥረት ምዕራፍ 24 ን በሙሉ መሠረት አድርጎ የተነሳ ስለሆነ አብርሃምን ፣ የአብርሃምን ሎሌ ፣ ርብቃንና ቤተሰብዋን እንዲሁም የይስሐቅንም ሕይወት ያካተተ ነው ትምህርቱን ለመረዳት የክፍሉን ሃሳብ እንደሚገባ ማጥናትና ማንበብ ያስፈልጋል ለተጨማሪ መረጃ እንዲሆናችሁ ቪዲዮውን መላልሳችሁ ስሙ ጌታ በነገር ሁሉ ይባርካችሁ የክፍል ሁለት መልዕክት ይቀጥላል ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊ የተሃድሶ አገልግሎት

Sunday 3 February 2019

Aba WoldeTensae Ayalenahe የሃዲስ ኪዳን ታቦት አሁን አድን የታቦቱ ምስጢር በቆራጡ የወንጌሉ ሐዋርያና አርበኛ አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ በዛሬው ስማቸው የሁላችን አባት በሆኑት በአቡነ በርናባስ ሲገለጥ እኚህ አባት በዚህ አስደናቂ መልዕክታቸው ስደትንና መገፋትን ከመጥላት የተነሣ እውነትን ይዞ ፣ ፈርቶና ተደብቆ ያለውን መምህር ልዑለ ቃል አካሉን ከተደበቀበት መቅደስ ውስጥ በስሙ በመጥራትና ወደ መድረኩም በማውጣት ፣ የእሁድ ውዳሴ ማርያም የሚለውን ቃል አንስተው በግዕዝ በማንበብ ፣ እርሱ ደግሞ አማርኛውን እንዲተረጉም አድርገውታል :: መምህር ልዑለ ቃልም በሕዝብ ፊት መጠራቱ ምንም እንኩዋ ያስደሰተው ባይመስልም የግድ እየተናነቀውም ቢሆን እውነቱን ይፋ አውጥቶና ዝርግፍ አድርጎ ተርጉሞታል :: ሃሳቡንም ፈራ ተባ እያለም ቢሆን እንዲህ ሲል ገልጾታል :: በወርቅ የተለበጠው ታቦት በአካላዊ ቃል ይመሰልልናል :: እኛን ለማዳን ሰው የሆነ በጎላ በተረዳ ሰው ከሆነ በኋላ እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ነው :: ድንግል በድንግልና ጸንታ ሳለች እመቤታችን ወለደችው በማለት እውነቱን አፍረጥርጦ ተናገረ :: ታድያ ከዚህ እውነት አንጻር መምህር ልዑለ ቃል ከዚህ ከተገለጠለት የወንጌል እውነት ራሱን ማሸሹም ሆነ መደበቁ ምን የሚሉት ሞኝነት ነው እንላለን :: ይህ ብቻ አይደለም ራሱን ወንጌል ያልተገለጠለትና ያልበራለት በማስመሰል ፣ የወንጌሉንም እውነት ሽምጥጥ አድርጎ በማካድ ፣ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክተኞችና የወንጌሉ አገልጋዮች የሆነውን እኛን ደግሞ አሁን ላይ ተነስቶ በብዙ ማሳደዱ በእጅጉ አስገርሞኛል :: ይሄ ብቻ አይደለም መምህር ልዑለ ቃል ተአምረ ማርያምን የጣልያን ባንዳ የጻፈው ነው ሲል የተቸበት የቪዲዮ ማስረጃ በእጃችን አለ :: ስለ መምህር ልዑለቃል ከተፈለገ በእውነት ላይ እንዲቆም ከምንፈልግ ውጪ ልንወነጅለው አንፈልግም እንጂ በወንጌል እውነት ላይ የቆመበትን ሌላ ብዙ የብዙ ብዙ ማስረጃዎች ማቅረብ እንችላለን :: ለማንኛውም ግን ለዚህ እውነት ያነሳሱትንና ያበረታቱትን አቡነ በርናባስን ፣ እግዚአብሔር ይባርክዎት ፣ ዕድሜና ዘመንም ይጨመርልዎት ለማለት እወዳለሁ :: ከዚያ መልስ ብፁዕ አባታችን አቡነ በርናባስ ርቱዕ በሆነና በመንፈስቅዱስም በተቃኘው አንደበታቸው የጌትነቱንና የአዳኝነቱን ፣ ከእግዚአብሔር ጋር መገናኛ ማዕከላችን የብሉይ ኪዳኑ ታቦት ሳይሆን ኢየሱስ መሆኑን ፣ ወደ አብ መንግሥት የሚወስደን በራችንም ሆነ መንገዳችን አሁንም ይኸው ኢየሱስ መሆኑን ትርትር አድርገው በሚገባ አስተምረዋል :: ለተጨማሪ መረጃ ቪዲዮውን መስማቱ አማራጭ የለውምና ቪዲዮውን ሰምታችሁ ተባረኩበት :: ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ አገልግሎት

Friday 1 February 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ አታልቅሺ ( የሉቃስ ወንጌል  7 : 13 ፤ 11 - 17 ) የምንባቡ ኃይለ ቃል ፦ ጌታም ባያት ጊዜ አዘነላትና አታልቅሽ አላት የሉቃስ ወንጌል  7 : 13 ፤ 11 - 17 የመልዕክት ርዕስ ፦ አታልቅሺ የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን በዛሬው መልዕክት በእርግጠኝነት እንደምትባረኩበት አምናለሁ :: ጌታ አታልቅሺ ፣ አታልቅስ ፣ አታልቅሱ ያለን ፤ ወደፊትም ይሄ ሁኔታ በሚደርስብን ጊዜ ሁሉ የሚለን ቀጥሎ ለእኛ ለልጆቹ ያለውንና ያሰበውን መልካም ነገር ስለሚያደርግ ነው ስለዚህ ጌታችን እንዲሁ እንደ ሰው በአፉ ይህንን ለማለት ብቻ ወይንም እንዲሁ ማለት ስላለበት አታልቅሺ ፣ አታልቅስ ፣ አታልቅሱ ያለን አይደለም ፣ ወደፊትም አይለንም :: ታድያ ይህቺንም መበለት በልጅዋ ሞት አዝኖላት አታልቅሺ ሲላት ለማለት ብቻ ያለ ሳይሆን ቀጣዩን የልጅዋን ነገር ከቃሬዛ ላይ የማስነሳትና መልሶም ለእርስዋ የማስረከብን ተግባር ሊያከናውንላት ወዶ ነው ደግሞም አከናወነላት :: ስለዚህ ወገኖቼ እንዲሁ እንደዚህች መበለት እኛም በአስከፊው ጉዳዮቻችን ዙርያ አልቅሰን ከሆነ አታልቅሱ ይበለን :: አታልቅሱ ያለን ጌታ ቀጣዩን ነገር በሕይወታችን ያለመከልከል ያደርጋል :: ውድ ወገኖቼ ሆይ በዚህ ውስጥ ታድያ እኛም እንደዚህች መበለት በዚህ ደግ ጌታ ተጽናንተን ከሆነ ማጽናናቱን ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ጊዜም ተግሣጹንም ጭምር መቀበል አስፈላጊያችን እንደሆነ ማመን አለብን:: ለዚህም ነው ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም እንደ ልጆችም ከእናንተ ጋር፦ ልጄ ሆይ፥ የጌታን ቅጣት አታቅልል፥ በሚገሥጽህም ጊዜ አትድከም፤ ጌታ የሚወደውን ይቀጣዋልና፥ የሚቀበለውንም ልጅ ሁሉ ይገርፈዋል ብሎ የሚነጋገረውን ምክር ረስታችኋል ያለን :: ለበለጠ መረጃ ቪዲዮውን ደግማችሁ ስሙት ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ አገልግሎት