Thursday 8 November 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 5 ) አስፈሪው የእግዚአብሔር ቁጣ በልዝብ ምላስም ሆነ በስጦታችን ልናበርደው የማንችለው ነው ( ምሳሌ 15 ፥ 1 ፣ ምሳሌ 21 ፥ 14 ) በፊንሐስ አማካኝነት፦ዘኊልቁ 25 ፥ 7 _ 13 ሀ ) መቅሰፍት ከእስራኤል የተከለከለበት ለ ) የእግዚአብሔር ቁጣ ከእስራኤል የተመለሰበት ሐ ) ለእስራኤል ልጆች ማስተስረይ የመጣበት ነው አስፈሪውና ጽኑዕ የእግዚአብሔር ቁጣ ከሕዝቡ እንዲከለከል እግዚአብሔርም ቁጣውን ከሕዝቡ እንዲመልስ በእግዚአብሔር ቅንዓት በመካከል የሚቀና ፊንሐስ ያስፈልጋል ዘኊልቁ 25 ፥ 11 ሀ ) እንደ ዔሊ እርሱ እግዚአብሔር ነው ደስ ያሰኘውን ያድርግ የማይል ( መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 3 ፥ 18 ) ለ ) ንቂ ቁሚ የሚል ኢሳይያስ 51 ፥ 17 ፤ መሣፍንት 5 ፥ 12 ፣ የሐዋርያት ሥራ 2 ፥40 - 42 ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል ( ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5 : 14 ) ሐ ) ደግመሽ አትጠቺው የሚል ኢሳይያስ 51 ፥ 22 ፤ የዮሐንስ ወንጌል 8 : 1 - 11 መ ) ጠጉርሽን ቁረጪ ጣይውም የሚል ኤርምያስ 7 ፥ 29 ፣ ራዕይ 3 : 1 - 6 ፣ 15 - 22 ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ ይለናል 1ኛ ነገሥት 13 ፥ 18 ፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5 : 6 ፤ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4 :2 ፤ ሮሜ ፤ 2ኛ ጴጥሮስ 3 : 16 - 18 አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment