Monday 5 November 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 4 ) ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ስለሆንን እግዚአብሔርን የሚወድ ማንነት የለንም ኤፌሶን 2 : 3 የእግዚአብሔር ቁጣና የሰው ቁጣ ልዩነታቸው ሀ ) የእግዚአብሔር ቁጣ ፦ የእግዚአብሔር ቁጣ እንደ ሰው ቁጣ ቶሎ የሚነሣና የሚበርድ አይደለም እንደገናም እግዚአብሔር በባሕርዩ ቁጣ የለበትም ነገር ግን ቅዱስና ጻድቅ ስለሆነ በኃጢአት ምክንያት ይቆጣል ቁጣውም በፍርዱ ይታያል ትንቢተ ኢሳይያስ 59 : 1- 4 ፤ ትንቢተ ኢሳይያስ 53 በሙሉ ዘኁልቁ 25 : 7 - 13 ፤ ትንቢተ ዘካርያስ 8 : 14 - 16 የዮሐንስ ወንጌል 3 : 36 ፤ ሮሜ 1: 18 ፤ ሮሜ 2 :5 ፤ ኤፌሶን 5 : 6 ለ ) የሰው ቁጣ ከፍርሃትና ከኩራት ከስንፍናም የሚመጣ በመሆኑ ቶሎ የሚነሣና የሚበርድም ነው ከዚህም ባሻገር በቃሉ እና በመንፈሱ እውነት ካልታረመና ካልተገታ የሥጋ ሥራ ስለሆነ አሳዛኝ ውጤትን ያመጣል ዘፍጥረት 27 : 41 - 45 ፤ ዘፍጥረት 30 : 1- 3 ፤ ዘፍጥረት 49 :6 እና 7 ፤ ምሣሌ 27 : 4 ሐ ) ልዝብ መልስ ወይም ስጦታ የሰውን ቁጣ ሊያበርድ ይችላል ምሣሌ 15 : 1 ፤ ምሣሌ 21 : 14 መ ) የእግዚአብሔር ቁጣ ግን የሰው ቁጣ ስላልሆነ በልዝብ መልስም ሆነ ስጦታ ልናበርደው አንችልም 1ኛ ሳሙኤል 15 : 13 - 16 ፤ትንቢተ ኤርምያስ : 12 : 2 የማቴዎስ ወንጌል 15 : 8 ፤ የማርቆስ ወንጌል 7 : 6 ፤ ቲቶ 1 : 16 ትንቢተ ኢሳይያስ 1 : 11 - 16 ፤ ሆሴዕ 6 : 6 ሠ ) ለእግዚአብሔር የሚገኝ እውነተኝነት መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 19 : 18 አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

No comments:

Post a Comment