Friday 27 January 2017

የመልዕክት ርዕስ ፦ የእግዚአብሔርን ቃል በሰዎች ሕይወት ውስጥ ማጽናት ( እርግጠኛ ማድረግ ) ዕብራውያን 2 ፥ 3...የመልዕክት ርዕስ ፦ የእግዚአብሔርን ቃል በሰዎች ሕይወት ውስጥ ማጽናት ( እርግጠኛ ማድረግ )ዕብራውያን 2 ፥ 3 እና 4 የተወደዳችሁ ቅዱሳን ይህ መልዕክት ለሁላችንም በጣም አስፈላጊና ወቅታዊ የሆነ መልዕክት በመሆኑ በብዙ ልታደምጡት ይገባል ስል ላሳስባችሁ እወዳለሁ ከቪዲዮው መልዕክት እንደምትሰሙት በአጭሩ ከጌታ የሰማነውን የእግዚአብሔርን ቃል ማጽናት በምንጀምርበት ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል በሰሙና ሊሰሙ ባሉ ፣ በሚሰሙም አማኞች ሕይወት ውስጥ ቃሉ እውነት ይሆናል እውነትም ሆኖ ይቀራል ከዚህም የተነሳ ቃሉን የሰሙ አማኝ ክርስቲያኖች የሕይወት አካሄድ እና የኑሮ ሥርዓት የአመለካከትም ለውጥ ያደርጋሉ ከጌታ የሰማነውን ቃል ማጽናት በማንችልበት ጊዜ ደግሞ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል እውነት አይሆንም ከዚህ የተነሳም ሰዎች ከክፉ መንገዳቸው አይመለሱም እንደውም እኛ ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለእነርሱም ጭምር ይሆናል ብለን የጀመርነውን የእግዚአብሔር ነገር አቋም ኖሮንና በአቋማችንም ጸንተን ቃሉን በራሳችን ሕይወትም ሆነ በሰሚዎች ሕይወት ካለማጽናታችን የተነሳ ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለሰሚዎቻችንም ጭምር ነገሩ ይበልጥ መሰናከያና ኃጢአት ይሆንባቸዋል እንደገናም እርግጠኝነትና የእግዚአብሔርንም ቃል ማጽናት ከሌለ ሰዎች የኪዳኑን ደም እንደ ርኩስ ነገር እስከ መቁጠር ይደርሳሉ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋሉ ስለዚህ እኛ በእውነት የጌታ አገልጋዮች ከሆንን ከጌታ የሰማነውን የእግዚአብሔርን ቃል በሰዎች ሕይወት ውስጥ ማጽናትና ማረጋገጥ አለብን ይህን በምናደርግበት ጊዜ ጌታም ከእኛ ጋር ሆኖ ይሰራል በሚከተሉትም ምልክቶችና ተአምራቶች ቃሉን ያጸናል በማለት ነበር የተነጋገርነው ታድያ ይህቺን አጭር መልዕክት የጻፍኩት ከዚህ በመቀጠል ለምትሰሙት ቪዲዮ እንደ መንደርደርያ ይሆናችኋል ብዬ ስላሰብኩ ነው ተባረኩልኝ በጌታ ፍቅር እወዳችኋለሁ እጸልይላችኋለሁ የቪዲዮውን መልዕክት ብትችሉ ያልሰሙ እንዲሰሙ ሼር አድርጉት ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment