Thursday 19 January 2017

የመልዕክት ርዕስ ፦ ያልተለመደ ነገር ያደርጋልና የእግዚአብሔርን ነገር ተረኛ እግዚአብሔርንም ወረፈኛ አታድርገው (...አንኳር የሆኑ የመልዕክቱ ዋና ዋና ሃሳቦች እግዚአብሔር ተገለጡ የሚለን በአክአብና በመንግሥቱም የሚያስፈልገን በኤልያስ ዘመን እንደመጣው ዝናብ ዝናብን አምጥቶ ተደናቂ ባርያዎች መሆናችንን ሊያስመሰክርልን ወይም ሊያረጋግጥልን ሳይሆን እንደዚሁ እንደ ኤልያስ አሁንም ፈርሶ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠውያ እንድናበጅ ሊያደርገንና ጉልበትም ሊሆነን ነው ኤልያስ ተገለጥ ዝናብ እሰጣለሁ ስለተባለ በአክአብ መንግሥትና ሕዝብም ሳይቀር ስለተፈለገ እንዲሁ በቀላሉ ሄዶ ከበዓል ነቢያትና ከመሥዋዕቶቻቸው መልስ መሠውያን ያቀረበ አልሆነም ይህንን ያደረገ ቢሆንማ እግዚአብሔርን ተረኛና ተራውም የደረሰ ወረፈኛ ባደረገው ነበር ነገር ግን ኤልያስ አምላኩን ለወረፋ የተዘጋጀ ከበዓልም ነቢያት አገልግሎት ለጥቆ የሚሠራ ተረኛ አላደረገውም ይህንንም የምናውቀው ከኤልያስ ከንግጝሩ፣ ከሰጣቸው መልሶቹና ከድርጊቱ ተነስተን ነው ይህንንም ለማወቅ እነዚህን ጥቅሶች ያንብቡአቸው 1ኛ ነገሥት 18 ፥ 15 ፣ 16 _ 29 ፣ 30 _ 46 ይህ ኤልያስ ታድያ ፈርሶ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠውያ ሲያበጅ በሌላኛው ገጽታ ወይም በተዘዋዋሪ የበዓልን ነቢያት መሠውያቸውንም ሆነ መሥዋዕታቸውን ሙሉ ለሙሉ እያፈረሰውና ዋጋም እያሳጣው መሆኑን ሁላችንም በይበልጥ የምንገነዘበው ጉዳይ ሊሆን ይገባል እርሱ ገና ሕያው እግዚአብሔርን ለእርሱ እገለጣለሁ ሲል የበዓል ነቢያት መሠውያቸውም ይሁን መስዋዕታቸው እንዲሁም ትንግርታቸውና ሟርታቸውም ጭምር ፈርሷል አሁንም እስከ ለዘለዓለሙ የፈረሰ ይሁን ሙሉ ትምህርቱን ለማግኘት ቪዲዮውን ይከታተሉ ጌታ እግዚአብሔር ዘመንዎን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን የ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry አገልጋይና የአገልግሎቱ ባለአደራ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ ተባረኩ

No comments:

Post a Comment