Tuesday 9 February 2016

የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉምከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ

የመልእክት ርዕስ



የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራጅማሬን ማወቅ


ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉምከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16  9 )




ክፍል አንድ









Image result for samson and delilah
የመልእክት ርዕስ



የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራጅማሬን ማወቅ


ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉምከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16  9 )



ክፍል አንድ



የተወደዳችሁ ወገኖች በቅድሚያየጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ዛሬበዚህ መልዕክት ወደ እናንተ መጥቻለሁ  ይህንን መልዕክትአንብባችሁ እንድትጠቀሙበትናለሌሎችም ሼር እንድታደርጉትበጌታ ፍቅር ለማሳሰብ እወዳለሁተባረኩልኝ ይህንን መልዕክትበደሊላና በሶምሶን ታሪክጀምሬዋለሁ እንደምትመለከቱትናከላይም በመግቢያዬ ላይእንደገለጽኩት ደሊላ ሶምሶንንልታዋርደው ጀመረች ኃይልምከእርሱ ሄደ ይለናል ይህ እንግዲህደሊላ በትክክል ሥራዋንየጀመረችበት ጊዜ ነው ለማለትእንችላለን ታድያ ይህንን የጅማሬጊዜ ነው ሶምሶን በውል ያላወቀውደሊላ ከሶምሶን ጋር በቆየችባቸውጊዜያት ለሶምሶን ደሊላትክክለኛውን ሥራ የጀመረችበትጊዜ መስሎታል አይደለም ለሶምሶንለሁላችንም ቢሆን ደሊላ ከሶምሶንጋር በተገናኘችባቸው ጊዜያቶችሁሉ ከድርጊቶችዋናከሁኔታዎችዋም የተነሳ በሰላምአብራ ስለምትወጣ ስለምትገባከአንደበትዋ ልስላሴና አነጋገርከምታሳየውም አቀራረብናየአነጋገር ዘዬ ሥራዋን በትክክልየጀመረች ብቻ ሳይሆን በአግባብሥራዋን በመስራት ላይ ያለችናየሚገባትንም ሥራ በትክክልእየተወጣች ያለች ሴት መሆንዋንምበቅርብ ርቀት ለምናያትተጠግተንም ላልተረዳናትናላላስተዋልናት ሁሉ ሊመስለንይችላል ብዬ እገምታለሁየእግዚአብሔር ቅባት በላዩ ላይያለ ሶምሶን የደሊላን የሥራ ጅማሬያላወቀ  በቅርብ ርቀት ያለንሰዎችማ ባናውቅ የሚገርምአይሆንም ነገር ግን ደሊላ ሶምሶንንልታዋርደው የጀመረችበት የሥራጅማሬ ዋናውና  አንገብጋቢውቀዳሚውም የሥራ ጅማሬ ነውበዚህ ውስጥ ልንረዳው የሚገባአንድ እውነት የተጀመሩጅማሬዎች ሁሉ ትክክለኛ የሥራጅማሬዎች ናቸው ማለትእንዳልሆኑ ሁላችንም ልናውቀውየሚገባ እውነት እንደሆነ አበክሬመናገር እፈልጋለሁ ይህንካልተረዳን የተጀመሩ ጀማሬዎች ሁሉ ትክክለኛ የሥራ ጅማሬዎች  ሳይሆኑ ቀርተው ፍጻሜያቸውየተበላሹ እንደሚሆኑ ውለንአድረን በዓይኖቻችን ልናያቸውከእኛ ሩቅ አይሆኑም ስለዚህ በዚህነገር መጠንቀቅ ከሁላችንየሚጠበቅ ጉዳይ ሊሆን ይገባልእላለሁ የብዙዎች የሥራ ጅማሬበተለይ በዚህ ዘመን የደሊላዓይነት የሥራ ጅማሬ በመሆኑአይታወቅም የተጀመሩ ጅማሬዎችሁሉ ካላስተዋልናቸውና ሃሌሉያብለን ከገባንባቸው ሃሌሉያ ብለንእንደገባን ሃሌሉያ ብለንለመውጣት የማንችልባቸውአሳሳቢ ነገሮች ውስጥ ይከቱናልደሊላ ከሶምሶን ጋርበጀመረችባቸው የፍቅርየወዳጅነትና የጓደኝነት ጊዜያቶች ጊዜ ለደሊላም ባይሆን ለሶምሶንግን የሃሌሉያ ጊዜ ነበር ለዚህምነው በመሣፍንት 14  1 _ 4   በተጻፈው ቃል ላይ  የሶምሶንድምጽ ከቤተሰቡ ይልቅ ከፍ ብሎመሰማትን የወደደው በአጠቃላይሶምሶን ለቤተሰቡ ያለው ደሊላተመችታኛለችና እርስዋን አጋቡኝነው ይሁን እንጂ እግዚአብሔርምበፍልስጥኤማውያን ላይ ምክንያትይፈልግ ነበርና ነገሩ ከእርሱ ሆነአባትና እናቱ ግን አላወቁም በዚያንጊዜ ፍልስጥኤማውያን በእስራኤልላይ ገዦች ነበሩ ይለናል ሌላውየሶምሶን የሃሌሉያ ጊዜ ወደከተማው በመግባቱ ምክንያትበጠላት መከበቡን እና ጠላቶቹምእንደሸመቁበት ሊገደልምእንደተፈለገ ያላወቀው ሶምሶንጋለሞታዋን ሴት አይቶ ወደእርስዋ በመግባት እስከ እኩለሌሊት መተኛቱ ነው እነዚህንናከዚያም በኋላ ያለው የደሊላያልታወቀው ሽንገላዋ ለሶምሶንየሃሌሉያ ጊዜ  የደሊላንም ፍቅሯንጭምር የማጣጣምያ ጊዜያትየመሰሉ ነበሩ ነገር ግን ሃሌሉያብሎ የደሊላ የፍቅር እቅፍ ውስጥበመግባት መኝታ አግኝቶ እስከእኩለ ሌሊት የተኛው ሶምሶንየነቃና አንዳንድ ነገሮችን ያደረገእንኳ ቢመስል ከእቅፏ ግን ወጥቶለማምለጥ ያልቻለ በመሆኑእዚያው በተኛበት ነው ለጠላትየተገኘው ፍቅሯን አጣጣምኩትተመችታኛለች  እና እርሷን አጋቡኝሲል  ደሊላን ለሚስትነት አጭቶየገባበትን ፍቅር   ለሞትናለውርደት ሆኖ  አገኘው ከዚያውከደሊላ እቅፍ ሳይወጣም የሚደክምበትን ጉዳይ ለደሊላተናግሮና የልቡን አጫውቶም ደከመ ጠላቶች ፍልስጥኤማውያንመጥተው ጸጉሩን ላጩትልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉምከእርሱ ሄደ በመቀጠልምትክክለኛውና ዋነኛውበፍልስጥኤማውያን በቀዳሚነትየሚጠበቀውም የደሊላ የሥራ ጊዜ ተጀመረ ሶምሶን የነቃው እንግዲህየደሊላ የሥራ  ጊዜ ተጀምሮሊጠናቀቅ ጥቂት ሰዓታት ሲቀሩነው ማለትም ሶምሶን የነቃውሶምሶን ሆይ ፍልስጥኤማውያንመጡብህ እያለች ደሊላልታዋርደው በጀመረች ጊዜ ነውይህ ጊዜ ሶምሶን ሆይፍልስጥኤማውያን መጡብህየሚለው ተደጋጋሚ የሆኑ የደሊላየሙከራ ቃላቶች እውን የሆኑበትጊዜ ነው ወገኖቼ አንዳንድ የሙከራቃላቶች ለቀልድ ያህል የተነገሩየመሠሉ የጫወታ ዘይቤዎች ሲሆኑጊዜውን ጠብቀውና ጫወታመሆናቸውም ቀርቶ ለእኛለሞታችን የተዘጋጁ ወጥመዶችሆነው ሲገለጡ ከወዲሁካልነቃንባቸው በሕይወታችንየሚያመጡት እጅግ አሳዛኝ የሆነየታሪክ ጠባሳ ነው ስለዚህ ይህከመሆኑ በፊት በተደጋጋሚ ወደሕይወታችን ለሚመጡ ጫወታመሰል የሙከራ ቀልዶች ቆይተውየጠላት ቁምነገሮችና ታርጌቶችይሆናልና እዚያ ጋር ሳይደርሱ በሕይወታችንም ላይ ሳያደሩከወዲሁ ልናስብበትልንቀጫቸውና ፍጻሜም ላይሳይደርሱ በአጭሩ ልናስቀራቸውይገባል ታድያ ሶምሶን ሆይፍልስጥኤማውያን መጡብህየሚለው የወዳጅነት ጭውውትመሰል የሙከራ ቀልዶች የሙከራቀልድ መሆናቸው አብቅቶበሶምሶን ላይ እውንና የተግባርመገለጫዎች የሆኑበት ጊዜ በመሆኑበእርግጥም ፍልስጥኤማውያንበሶምሶን ላይ መምጣት ችለውነበር መጽሐፉ አሁንምእንደሚነግረን እርስዋም፦ ሶምሶንሆይ፥ ፍልስጥኤማውያን መጡብህአለችው ከእንቅልፉም ነቅቶ፦እወጣለሁ እንደ ወትሮውም ጊዜአደርጋለሁ አለ ነገር ግንእግዚአብሔር ከእርሱ እንደተለየው አላወቀምፍልስጥኤማውያንም ይዘውዓይኖቹን አወጡት፤ ወደ ጋዛምአምጥተው በናስ ሰንሰለት አሰሩት፤በግዞትም ሆኖ እህል ይፈጭ ነበርይለናል መሣፍንት 17  20 _ 22 ስለዚህ በማናኛውም አቅጣጫእና የሥራ ዘርፍ ተጀመሩያልናቸው የሥራ ጅማሬዎች ተከታትለን ካላየናቸውባልጠበቅነው ሁኔታ ተፈጽመውእንደ ሶምሶን ታሪካችንን አሳዛኝሊያደርጉት ይችላሉና ከወዲሁሥራዎቻችንን ሁሉ ጥንቃቄየተሞላበት ልናደርገው ይገባልየተጀመሩ የሚመስሉ ደግሞየተጀመሩ ናቸው ብለን ብዙ ርቀትከተጓዝን በኋላ እኛ በጠበቅነውመንገድ ሳይሆን ሌላ ጅማሬንበሕይወታችን አምጥተው መውጫን ያሳጡናል ፣ ለውርደትና ለሞትም ይዳርጉናል ስለዚህ   በትክክለኛ ሁኔታየተጀመሩ ከሆኑ በትክክለኛ ሁኔታየተጀመሩ መሆናቸውን ከወዺሁቆም ብለንና ከጒዞአችንም ተገተንበትክክል የተጀመሩ መሆናቸውንልናይ  ልናጤናቸውም ይገባልመልእክቱ ቀጣይ ክፍል ሁለትአለው ተባረኩ


       

Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministryአገልጋይና ባለ ራዕይ

ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ


No comments:

Post a Comment