Monday, 31 December 2018

የኢየሱስ ደቀመዝሙር መሆን ክፍል አንድ ትምህርት የትምህርት ርዕስ ፦ የኢየሱስ ደቀመዝሙር መሆን ( ክፍል አንድ ) የተወደዳችሁ ቅዱሳን ወገኖችና የእግዚአብሔር ሕዝቦች በሙሉ ተባረኩ እንደሰማችሁትና እንደተከታተላችሁት ጌታ አጃቢዎች እንድንሆን ሳይሆን ትክክለኛ የራሱ ደቀመዛሙርት እንድንሆን ስለፈለገ ይህንን መሠረታዊ ትምህርት በትምህርቱ የመነሻ ክፍለጊዜያችን ላይ ሰጥቶናል :: ዓለምን እንደኖህ በጽድቅ የምንኮንን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንድንሆን ራሳችንን ለጸጋው ባለቤት ለእግዚአብሔር በማስገዛት ጸጋውን ተቀብለን ወደዚህ ሕይወት ልንመጣ እንደምንችል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር በመንፈሱ አማካኝነት በጽኑ ተናግሮናል :: ያገለገለንን የእግዚአብሔር ሰው መምህር ጌታቸው ምትኩን ጌታ እግዚአብሔር ይባርከው ለማለት እፈልጋለሁ ትምህርቱ እንግዲህ ሰኞ ሰኞ ሁልጊዜ በዚሁ ሰዓት ይቀጥላል :: ይህንንም ትምህርት ለሰዎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ :: ሰዎችን መጋበዝ አትርሱ :: ጌታ እግዚአብሔር የሳምንት ሰው ይበለን ቸር እንሰንብት ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከተሃድሶ አገልግሎት

Thursday, 27 December 2018

የመልዕክት ርዕስ ፦ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ!! ከዚህ በመቀጠል የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ምክንያት በማድረግ አሁንም በድጋሜ መልዕክትን ወደ እናንተ ይዤ ቀርቤያለሁና ተከታተሉ የመልዕክት ርዕስ ፦ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና የዕለቱ የምንባብ ክፍል ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል፦ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ ( የማቴዎስ ወንጌል 2: 1 - 2 ) 1ኛ ) እነዚህ ሰዎች ሊሰግዱ መጥተው የቀሩ አልሆኑም ፣ ንጉሥ ሄሮድስም አላስቀራቸውም ፣ ኢየሱስ ጋር መጥተው ሰገዱለት ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት፥ ወድቀውም ሰገዱለት፥ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤም አቀረቡለት ( የማቴዎስ ወንጌል 2 : 11 ) 2ኛ ) ኢየሱስ ከተወለደ ጀምሮ ንጉሥ ነው ደግሞም የሚሰገድለት ነው :: ከሞት ተነስቶና ሞትን አሸንፎ ብቻ አይደለም የተሰገደለት በታንኳይቱም የነበሩት፦ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብለው ሰገዱለት ( የማቴዎስ ወንጌል 14 : 33 ) እነሆም፥ ኢየሱስ አገኛቸውና፦ ደስ ይበላችሁ አላቸው። እነርሱም ቀርበው እግሩን ይዘው ሰገዱለት ( የማቴዎስ ወንጌል 28 : 9 ) እነርሱም፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ ( የሉቃስ ወንጌል 24 : 52 ) በታላቅም ድምፅ፦ የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ በሰማይና በምድርም ከምድርም በታች በባሕርም ላይ ያለ ፍጥረት ሁሉ በእነርሱም ውስጥ ያለ ሁሉ፦ በረከትና ክብር ምስጋናም ኃይልም ከዘላለም እስከ ዘላለም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው፥ ለበጉም ይሁን ሲሉ ሰማሁ አራቱም እንስሶች፦ አሜን አሉ፥ ሽማግሌዎቹም ወድቀው ሰገዱ ( ራዕይ 5 : 11 - 14 ) 3ኛ ) ኢየሱስን አንጠራጠረው ፣ ንጉሣችንና አዳኛችንም ነውና አንካደው ባዩትም ጊዜ ሰገዱለት፤ የተጠራጠሩ ግን ነበሩ ( የማቴዎስ ወንጌል 28 : 17 ) ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት ( የማርቆስ ወንጌል 15 : 19 ) ብንጸና፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ እንነግሣለን፤ ብንክደው፥ እርሱ ደግሞ ይክደናል 2ኛ ጢሞቴዎስ 2 : 12 ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ

Thursday, 20 December 2018

በመምህር ጌታቸው የተዘጋጀ ትምህርት ነበረ በኮኔክሽን ምክንያት ቢቁዋረጥም ጌታ በመንፈሱ ያካፈለን መልዕክት ነበረ ...የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን መምህር ጌታቸው ምትኩ የኢየሱስ ደቀመዝሙር መሆን በሚል ርዕስ ተከታታይ ትምህርት ለመስጠት በሰዓቱ ተገኝቶ ነበር ነገር ግን በኮኔክሽን ችግር ምክንያት በዕለቱ ሊያስተላልፍልን ይዞት የመጣውን ትምህርት ማስተላለፍ አልቻለም በሚቀጥለው ጊዜ ጌታ ረድቶን በሚኖረን ፕሮግራም ያለምንም ችግር ለተከታታይ ሳምንታት ሳይቋረጥ እናስተላልፋለን ብለን እናምናለን ወንድማችን እንደምታውቁት ለማስተማር ከኢትዮጵያ ነውና የሚገባው የሃገራችንን የኔት ወርክ ሁኔታ ደግሞ ታውቁታላችሁና በጣም አስቸጋሪ ነው ለወደፊቱም ያለምንም ችግር የተዘጋጁበትን ትምርቶች እንደሚገባ እንዲያስተላልፉ ከኢትዮጵያ ለሚገቡ አገልጋዮችም ሆነ እዚሁ ላለነው ለእኛም ጭምር አብዝታችሁ ጸልዩልን ለማለት እወዳለሁ ይሁን እንጂ ጌታ መልዕክት ስለነበረው በሚደንቅ ሁኔታ ቃሉን በመንፈስቅዱስ አማካኝነት አስተላልፎልናል መልዕክቱ የሚጠቅማችሁ ስለሆነ ደጋግማች በማስተዋል ስሙት ጌታ እግዚአብሔር ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ

Wednesday, 19 December 2018

Ethiopia:{ እጅግ አሳዛኝ መረጃ } አረጋዊው ሊቀ ጳጳስ ተደበደቡ! ግን ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን እስኪገሎቸው ነው...ይህቺ ናት ርትዕቷና ቀጥተኛዋ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ተብላ የሚፎከርላት እንግዲህ :: መጨረሻዋ ይሄ ሆነ :: ጉድ አይሰማም አይባልምና አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት የማይከበሩባት ፣ ጉሮሮአቸው ታንቆ የሚደበደቡባት ፣ መንፈሳዊ መሪዎች የማይከበሩባት እና የማይደመጡባት ፣ ሊያውም የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የሆኑት አረጋዊ አባትና የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ የተደበደቡባት ቤት ሆነች :: ወገኖቼ የእስራኤል መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ፣ አናቂ ቁጥር 1 ሽፍቶች መነኮሳትን እስር ቤት ባይወስድ ፣ በቤተመቅደሱ ውስጥም የነበረውን ድብድብ ባያስቆም ፣ ጉሮሮአቸው የታነቀው ምስኪኑ አረጋዊው ሊቀ ጳጳስ ለሕልፈተ ሕይወት በተዳረጉ ነበር :: ወገኖቼ እስቲ አንድ ጊዜ ይህንን ሁኔታ ቆም ብላችሁ አስቡት የራስ ሀገር ባልሆነ በኢየሩሳሌም ከአንድ ትልቅ ገዳምና የኃይማኖት ተቋም ይሄ ድርጊት ሊፈጸም ይገባልን ? የሦስት ሺህ ዓመት ክርስትና አለኝ የምትለዋ ይህቺ ቤተክርስቲያንስ በዚህ አሳፋሪ ጉዳይ ስሟ በዓለም ዙርያ ሊናኝና ሊነሳስ ይገባ ነበር ? ታድያ ለዚህ እኮ ነው እኛም አፋችንን ሞልተን አሁን ላይ ላለችው ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ቃል ተሃድሶ ያስፈልጋታል የምንለው :: በሆሴዕ 4 ፥ 6 - 8 በተጻፈው ቃል መሠረት ከምዕመኖችዋ በፊት ያሉት ካህናትዎችዋ በደሙ የተገኘውን የኃጢአት ሥርየት ለማግኘት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በነፍስ ወከፍ የግል አዳኛቸው አድርገው ዛሬ ነገ ሳይሉ እና ሳይሞቱ በምድር ላይ አሁኑኑ ድህነትን ተቀብለው ቢገኙ ፣ የዳነ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ስምና በአምላኩም መንፈስ የታጠበ ፣ የተቀደሰና የጸደቀ ስለሆነ ዓመጸኛ ተሳዳቢ ሴሰኛ ነጣቂ ተደባዳቢ ገዳይና የመሣሠሉትን አይሆኑም በ2ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 9 - 11 የተጻፈውን ቃል በማስተዋል እናንብበው :: ቀራጩ ዘኬዎስ ኢየሱስ በምድር በነበረበት ጊዜ በቀረጥ ሰብሳቢነቱ አሁን ከዘረዘርኳቸው ተርታዎች የተመደበ ሰው ነበር :: ነገር ግን ኢየሱስን ይዞ ወደ ቤቱ በመግባት ዘኬዎስ ግን ቆሞ ይለናል ቃሉ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ ካለኝ ሁሉ እኩሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ ማንንም በሐሰት ከስሼ እንደሆነ አራት እጥፍ እመልሳለሁ ሲል ልባዊ ኑዛዜውን እንዳቀረበና ኢየሱስም አሁን ለቤቱ መዳን እንደሆነለት አውጆ የአብርሃም ልጅ ነህ እንዳለው እንመለከታለን የሉቃስ ወንጌል 19 ፥ 1 - 10 :: ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያደድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል እንደሚል ቃሉ ሮሜ 4 ፥ 5 የሚያስደንቀው እውነት ኢየሱስ ስለበደላችን የሞተ እኛንም ስለማጽደቅ የተነሣ ነውና በእርሱ በማመናችን ምክንያት ብቻ እምነታችንን ጽድቅ አድርጎ ይቆጥረዋል ሮሜ 4 ፥ 22 - 25 :: ለዚህም ነው ዘኬዎስን እውነተኛ ንስሐ በመግባቱ ብቻ ተቀብሎ መዳንን የሰጠው :: ወገኖቼ ሆይ ጽድቃችን ወይም ሥራችንማ ይኸው አረጋዊ ጳጳስ ሳይቀር እስከ መደብደብ ደርሶ በእግዚአብሔር ፊት አላቆመንም :: ይኸው ታየ ኦኮ በቃ ! ስለዚህ ትምክህታችን ጽድቃችን ቅድስናችንና ቤዛችን የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው 1ኛ ቆሮንቶስ 1 ፥ 30 እና 31 ን እንመልከት :: መልዕክቴን ስጠቀልለው አሁን ላይ ያለሽው ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የሚበጅሽ አንድና አንድ ነገር ቢኖር የእግዚአብሔር ቃል ነውና ወደ እግዚአብሔር ቃል ፊትሽን መልሺ ስል በወንድማዊና አባታዊ ምክሬን ልሰጥሽም ሆነ ላስገነዝብሽ እወዳለሁ:: በኢሳይያስ መጽሐፍ እንደተጻፈው በዘመኑም ፍጻሜ የእግዚአብሔር ቤት ተራራ በተራሮች ራስ ላይ ጸንቶ ይቆማል፥ ከኮረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል፥ አሕዛብም ሁሉ ወደ እርሱ ይሰበሰባሉ በዘመኑም ፍጻሜ የእግዚአብሔር ቤት ተራራ በተራሮች ራስ ላይ ጸንቶ ይቆማል፥ ከኮረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል፥ አሕዛብም ሁሉ ወደ እርሱ ይሰበሰባሉ በአሕዛብም መካከል ይፈርዳል፥ በብዙ አሕዛብም ላይ ይበይናል ሰይፋቸውንም ማረሻ ጦራቸውንም ማጭድ ለማድረግ ይቀጠቅጣሉ ሕዝብም በሕዝብ ላይ ሰይፍ አያነሣም፥ ሰልፍም ከእንግዲህ ወዲህ አይማሩም እናንተ የያዕቆብ ቤት ሆይ፥ ኑ፥ በእግዚአብሔር ብርሃን እንሂድ በማለት ይናገራል ትንቢተ ኢሳይያስ 2 ፥ 2 - 5 ይመልከቱ በዚህ ጉዳይ ላይ ወደፊት ከወንድሞቼ ጋር በመነጋገር አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ መሪነትን አገልግሎትንና ክህነትን ሌሎችንም ጉዳዮች መሠረት ያደረገ ሰፋ ያለ ትምህርት ይዘን በቪዲዮ ልንቀርብ እንችላለን :: እስከዚያው ግን ይህቺን መልዕክት በማንበብ እንድትጠቀሙ ለእናንተ ለወገኖቼ ትቻለሁ :: ሌላው መናገር የምፈልገው ወንድምህ ሲታማ ለእኔ ብለህ ስማ ነውና ይሄ ውሽንፍር ወደ ወንጌላውያኑም ቤተክርስቲያን ከሞላ ጎደል ጎራ ያለ በመሆኑ ይፋ ሆኖ ባይገለጥም በአንዳንድ ደካማና ያልበሰሉ ፓስተሮችም ሆነ ነቢያት እየታየ ያለ ክስተት ሆኗል ስለዚህ በአጠቃላይ የክርስቶስ ስም በእኛ ምክንያት እንዳይሰደብ ሁላችንም ልናስብበት ይገባል የሚለውን ምክር ልሰጥ እፈልጋለሁ :: ጌታ እግዚአብሔር ማስተዋልን ይስጠን :: ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

Ethiopia:{ እጅግ አሳዛኝ መረጃ } አረጋዊው ሊቀ ጳጳስ ተደበደቡ! ግን ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን እስኪገሎቸው ነው...

December 18, 2018 በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 12 ) አለማፈርስ ያለው ማንን በማመን ነው ? ማርያምን ወይስ ኢየሱስን ? ወንድሞች ሆይ አወቃችሁን እምነቱን በእናቱና በእግዚአብሔር ላይ ያደረገ ሁሉ አያፍርም የሚለውንና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች ክብርት እመቤቴ ሆይ ከአንቺ ዘንድ ሽቶ የወደደውን ሁሉ ያላገኘ ማነው? በአንቺ አምኖ ያፈረ ማነው ? አንቺን ለምኖ ወደ ገሃነም ያወረድሽው ማነው ? ወደ ሠርግ ቤት ማለት ወደ መንግሥተ ሰማይ አገባሽው እንጂ የሚለውን በ2007 እትም ተአምር 41 : 25 እና በተአምር 43 : 23 - 25 ማግኘትም እንችላለን :: የተአምረ ማርያም መጽሐፍ በተለያየ ዓመተ ምሕረት የተጻፈ በመሆኑ እንደየ ዓመተ ምሕረቶቹ ምዕራፎቹና ቁጥሮቹ ይለያያሉ ተባረኩ በባለፈው ትምህርታችን ላይ የተአምረ ማርያም ጸሐፊ ርኢክሙኑ ኦ አኃው "እስመ ኩሉ ዘረሰየ ትውክልቶ ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ ወላዲቱ ኢይትኀፈር " ወደ አማርኛው ሲተረጐም :--- ወንድሞች ሆይ አወቃችሁን እምነቱን በእናቱና በእግዚአብሔር ላይ ያደረገ ሁሉ አያፍርምና ብሎን ነበር ( ተአምር 31 : 25 ) እምነታችን የመጣው የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ስለሆነ የማናፍረው እምነታችንን በእናቱና በእግዚአብሔር ላይ አድርገን ሳይሆን በትንቢተ ኢሳይያስ  28 ፥ 16 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በጽዮን ድንጋይን ለመሠረት አስቀምጣለሁ፤ የተፈተነውን፥ የከበረውን፥ መሠረቱ የጸናውን የማዕዘን ድንጋይ የሚያምን አያፍርም ይላልና የማዕዘኑን ድንጋይ የሆነውን ኢየሱስን አምነን ነው ዛሬ ደግሞ በተአምር 33 ፥ 23 - 25 ላይ ኦ እግዝእትየ ቅድስት ድንግል በ፪ ማርያም መኑ ዘኀሠሠ እምኔኪ ወኢረከበ ኮሎ ዘፈቀደ ወመኑ ዘተወከለ ኪያኪ ወተኀፍረ ወመኑ ዘጸውአ ኀቤኪ ወሰደድኪዮ አፍኣ ዘእንበለ ዘአባእኪዮ ውስተ ቤተ መርዓ ይለናል ወደ አማርኛው ስተረጉመው በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች ክብርት እመቤቴ ሆይ ከአንቺ ዘንድ ሽቶ የወደደውን ሁሉ ያላገኘ ማነው? በአንቺ አምኖ ያፈረ ማነው ? አንቺን ለምኖ ወደ ገሃነም ያወረድሽው ማነው ? ወደ ሠርግ ቤት ማለት ወደ መንግሥተ ሰማይ አገባሽው እንጂ በማለት ይህንን ቃለ ተናገረ ይህ ማለት ታድያ ሰዎች ከማርያም እንዳይሄዱና እንዲታዘዙላት ፣ እንዲያመልኩዋት ፣ እንዲሰግዱላትና እንዲገዙላት ስለ ራሷም ታላቅነት ጭምር እንዲናገሩ ነው ይህ የስሕተት መጽሐፍ የሚያስተምረው በዚህም ምክንያት እንግዲህ የተአምረ ማርያም ጸሐፊ ደፍሮ ማርያም ማለት መንግስተ ሰማያት መርታ የምታገባ ማለት ነው አለን ( የዘወትር መቅ፡ቁጥር፡ 5 ) እመቤታችንን የቤተክርስቲያን ልጆች አክብሩዋት ለእናንተ ለኃጥአን መድኃኒት ስለሆነች ሳትጠራጠሩ በፍጹም ልባችሁ እመኑባት እርስዋ መድኃኒታችሁ ናትና አለን ( የዘወትር መቅ፡ቁ፡ 34 ) የካቲት 16ቀን አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ ያሉበት የጻድቃን ማረፊያቸው ቦታ ያሳዩዋት ዘንድ ወደ ሰማይ አሳረጉዋት ከአዳም ጀምሮ እስከዚያው ድረስ ያረፉ ያባቶች ነፍሳት ሁሉ ተቀበሉዋት ከአጽማችን አንችን አጥንት ከሥጋችን አንቺን ሥጋ ለፈጠረልን ለእግ/ር ምስጋና ይግባው እያሉም ሰገዱላት ባንቺ ደህንነትን አገኘን የአምላካችን ልጅ ካንቺ ተወለደ ከጥፋት የሕይወት ወደብ የሆንሽን እያሉም ሰገዱላት አለን (12ኛ ተአምር ቁ፡12 - 13) እመቤታችንን የዓለም ሁሉ መድኃኒት አድርጎ እንደፈጠራት ልብ አድርጋችሁ እነሆ እወቁ አለን (12ኛ ተአምር ቁ፡ 62) ልመናንና አምልኮንም በተመለከተ ደግሞ አንቺ ከሰማያውያን መላእክት ልዕልት እንደሆንሽ ከመሬታውያን ጻድቃንም የከበርሽ እንደሆንሽ ያውቁ ዘንድ ይደረግልኛል ብሎ አምኖ አንቺን በእኔ ስም የለመነ ሰው ቢኖር ከሰማዕታት አንዱም ቢሆን ከቅዱሳንም ወገን ቢሆን የፈለገው ይደረግለታል (18ኛ ተአምር ቁ፡30_31) እንደኔ ያላችሁ ወንድሞቼ ሆይ ከእንግዲህ ወዲህ 16ቱን ሕግጋት ለመፈጸም የእግ/ር ባሮች ለመሆን አንሻ እሱ በቀትር ግዜ በመስቀል ላይ እመቤታችሁ እናታችሁ እነሆ እያለ የቃል ኪዳን እመቤት እሷን ሰጥቶናል ስለዚህ የእናታችን የድንግል ማርያም ባሮች ለመሆን ፈጽመን እንሽቀዳደም ብዬ እነግራችሁዋለሁ። (12ኛ ተአምር ቁ፡ 52_53) ከነዚህ ሃሳቦቹ የተነሳ ይሄ የተአምረ ማርያም ጸሐፊ እግዚአብሔር የለም ኢየሱስም ለእኛ አልሞተልንም እያለን ነው መጽሐፍ ቅዱሳችን እንደሚነግረን ግን 1ኛ ) አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ ( 1ኛ ጢሞቴዎስ 2 : 5 ) 2ኛ ) ወደ እግዚአብሔር የቀረብነው ፣ ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ ? ያልነው በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ እንደሆነ ግልጽ አድርጎ ነግሮናል ክርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንዲያቀርበን እርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞች አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት ሞቶአልና፤ በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ በእርሱም ደግሞ ሄዶ በወኅኒ ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ፥ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቈየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም ( 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት  3 : 18 - 20 ) ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ ? የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው ፤ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ( 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች  15 : 55 - 57 ) 3ኛ ) በዚህም ምክንያት የምንንበረከከውም ሆነ የምንገዛው ለእግዚአብሔር አብ ክብር እየሰጠን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በመንበርከክ ብቻ ነው በመዝሙር 95 : 6 ላይ ኑ፥ እንስገድ ለእርሱም እንገዛ፤ በእርሱ ባደረገን በእግዚአብሔር ፊት እንበርከክ ይለናል በመዝሙር 100 : 4 ላይ ደግሞ ወደ ደጆቹ በመገዛት፥ ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፤ አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ በማለት ይነግረናል እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው ይለናልና ( ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች  2 : 6 - 11 ) ታድያ ከዚህ ከተባረከው የእግዚአብሔር እውነት አንጻር የተአምረ ማርያምን መጽሐፍም ሆነ ጸሐፊውን ፦—————————— በማቴዎስ ወንጌል 4 : 10 በተጻፈው ቃል መሠረት ያን ጊዜ ኢየሱስ፦ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና በማለት ገስጾ አባሮታልና እኛም እንዲሁ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ስንል እናባርረዋለን ደግሞም እናስወግደዋለን 4ኛ ) መዳን በኢየሱስ ብቻ ነው ስለዚህ መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና ( የሐዋርያት ሥራ  4 : 12 ) እንደገናም ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም ብሎናል ( የዮሐንስ ወንጌል 14 ፥ 6 ) በዕብራውያን 7 ፥ 24 ላይ ደግሞ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው ፤ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል ይለናል 5ኛ ) ትዕዛዛትንም በተመለከተ እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ የማቴዎስ ወንጌል 5 : 18 እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንዲቱን የሚሽር ለሰውም እንዲሁ የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል የማቴዎስ ወንጌል 5 : 19 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም የዮሐንስ ወንጌል 14 : 24 ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ

Thursday, 13 December 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 11 ) ማንን ነው ማመን ያለብን ? በማን ስንታመንና ማንንስ ስናምን ነው የማናፍረው ? ጉደኛውና ተረተኛው የተምረ ማርያም መጽሐፍ ርኢክሙኑ ኦ አኃው "እስመ ኩሉ ዘረሰየ ትውክልቶ ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ ወላዲቱ ኢይትኀፈር " ወደ አማርኛው ሲተረጐም :--- ወንድሞች ሆይ አወቃችሁን እምነቱን በእናቱና በእግዚአብሔር ላይ ያደረገ ሁሉ አያፍርምና ይለናል ( ተአምር 31 : 25 ) 1ኛ ) ማንን ነው ማመን ያለብን ? ለሚለው ጥያቄ ሀ ) መጽሐፍቅዱሳችን በእግዚአብሔር እመኑ ነው የሚለን ማልደውም ተነሡ፥ ወደ ቴቁሔም ምድረ በዳ ወጡ፤ ሲወጡም ኢዮሣፍጥ ቆመና፦ ይሁዳና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሆይ፥ ስሙኝ በአምላካችሁ በእግዚአብሔር እመኑ፥ ትጸኑማላችሁ፤ በነቢያቱም እመኑ፥ ነገሩም ይሰላላችኋል አለ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 20 : 20 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ በእግዚአብሔር እመኑ እውነት እላችኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል የማርቆስ ወንጌል  11 : 22 - 23 ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና ፤ ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ የዮሐንስ ወንጌል  14 : 1 - 3 ወንድሞች ሆይ አወቃችሁን እምነቱን በእናቱና በእግዚአብሔር ላይ ያደረገ ሁሉ አያፍርምና ግን አላለንም ይህንን ያለን የተአምረ ማርያም መጽሐፍ ነው ለ ) እምነታችን የመጣው ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ስለሆነ እንዲሁ ዝም ብለን እንደ ደራሽ ውሃ ያመነው ወይም የምናምነው እምነት የለም ስለዚህ ፦———————— እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው ይለናል ሮሜ 10 : 17 ሐ ) የአብርሃም እምነት በእግዚአብሔር ቃል የሆነ እምነት ነበር እነሆም፥ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጣለት፦ ይህ አይወርስህም፤ ነገር ግን ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል ወደ ሜዳም አወጣውና፦ ወደ ሰማይ ተመልከት፥ ከዋክብትንም ልትቈጥራቸው ትችል እንደ ሆነ ቍጠር አለው። ዘርህም እንደዚሁ ይሆናል አለው አብራምም በእግዚአብሔር አመነ፥ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ኦሪት ዘፍጥረት  15 : 4 - 6 ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት ነገር ግን፦ ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው ሮሜ   4 : 22 - 25 2ኛ )በማን ስንታመንና ማንንስ ስናምን ነው የማናፍረው ? ከዚህ ከተቆጠረልን ከእምነት የሆነ ጽድቅ የተነሳ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ነው የተባልነው :: ያም ያመነው ፣ ያላመንበት ብንኖር ደግሞ በእርሱ ብናምን የማናፍርበት ፣ የተመረጠና የከበረ የማዕዘን ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ነው ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በጽዮን ድንጋይን ለመሠረት አስቀምጣለሁ፤ የተፈተነውን፥ የከበረውን፥ መሠረቱ የጸናውን የማዕዘን ድንጋይ የሚያምን አያፍርም ትንቢተ ኢሳይያስ  28 :16 በመጽሐፍ፦ እነሆ፥ የተመረጠና የከበረን የማዕዘን ራስ ድንጋይ በጽዮን አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ ተጽፎአልና እንግዲህ ክብሩ ለእናንተ ለምታምኑት ነው፤ ለማያምኑ ግን አናጢዎች የጣሉት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ የዕንቅፋትም ድንጋይ የማሰናከያም ዓለት ሆነ የማያምኑ ስለ ሆኑ በቃሉ ይሰናከሉበታልና፤ ለዚህ ደግሞ የተመደቡ ናቸው 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት  2 : 6 - 8 እንግዲህ ምን እንላለን? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው እስራኤል ግን የጽድቅን ሕግ እየተከተሉ ወደ ሕግ አልደረሱም ይህስ ስለ ምንድር ነው? በሥራ እንጂ በእምነት ጽድቅን ስላልተከተሉ ነው፤ እነሆ፥ በጽዮን የእንቅፋት ድንጋይና የማሰናከያ ዓለት አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ እንደ ተጻፈ በእንቅፋት ድንጋይ ተሰናከሉ ሮሜ 9 : 30 - 33 ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና ሮሜ 10 : 8 - 11 ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

Thursday, 6 December 2018

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 10 ) ለሁሉም ሰው ለማርያምም ጭምር የኢየሱስ ሞት አስደናቂ ነው ይሁን እንጂ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ይገኝበታል በተባለው መጽሐፈ ዚቅ ፦ « ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል » የሚል ሃሳብ ተጽፎ ብናገኝም 1ኛ ) የማርያም ሞት ግን አይደለም ለእኛ ፣ ለራስዋ ለማርያም እንኩዋ ያስፈራት እንጂ ያስደነቃት አልነበረም ለምን ስንል ፦ የሞት ጣር ያዘኝ፤ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድ ደረሰብኝ ( መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 22 : 5 - 6 ) የሞት ጣር ያዘኝ፥ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድም ደረሰብኝ ( መዝሙረ ዳዊት 18 : 4 - 5 ) ልቤ በላዬ ተናወጠብኝ፥ የሞት ድንጋጤም ወደቀብኝ ( መዝሙረ ዳዊት 55 : 4 ) የሞት ጣር ያዘኝ፥ የሲኦልም ሕማም አገኘኝ፤ ጭንቀትንና መከራን አገኘሁ ( መዝሙረ ዳዊት 116 : 3 ) ፊቴ ከልቅሶ የተነሣ ቀላ የሞት ጥላ በዓይኖቼ ቆብ ላይ አለ ( መጽሐፈ ኢዮብ 16 : 16 ) የጥዋት ብርሃን ለእነርሱ ሁሉ እንደ ሞት ጥላ ነው የሞትን ጥላ ድንጋጤ ያውቃሉና (መጽሐፈ ኢዮብ 24 : 17 ) 2ኛ ) በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ራሱ በሥጋው ወራት ፦ ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት ይለናል ዕብራውያን 5 : 7 ከዚያ በፊት ግን ፦———————————— ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም፦ አባት ሆይ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 41 - 42 ) ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 43 - 44 ) ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው ስለ ምን ትተኛላችሁ ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 45 - 46 ) 3ኛ ) ኢየሱስ በሥጋና በደም እንዲሁ በመካፈሉ የመጣ ለውጥ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ ይለናል ( ዕብራውያን 2 : 14 - 15 ) 4ኛ ) ይህ እንዲሆን ታድያ ኢየሱስ የተናገረው ፣ አባቱም እግዚአብሔር ያደረገው ወይም የሠራው ሥራ ነበረ እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች ይሰጣል፤ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል ( የማቴዎስ ወንጌል 20 : 18 ) እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች አልፎ ይሰጣል፥ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል፥ ለአሕዛብም አሳልፈው ይሰጡታል ( የማርቆስ ወንጌል 10 : 33 ) እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና ( የሐዋርያት ሥራ 2 : 24 ) ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ ( የዮሐንስ ራእይ 1 : 18 ) 5ኛ )ለሁሉም ሰው ለማርያምም ጭምር የኢየሱስ ሞት አስደናቂ መሆኑ በነቢዩም በኢሳይያስ፦ የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር፥ የባሕር መንገድ፥ በዮርዳኖስ ማዶ፥ የአሕዛብ ገሊላ፤ በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፥ በሞት አገርና ጥላ ለተቀመጡትም ብርሃን ወጣላቸው የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ ( የማቴዎስ ወንጌል 4 : 14 - 16 ) ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል ( የሉቃስ ወንጌል 1 : 79 ) እናንተንም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁና ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ፥ በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ ( ቆላስይስ 1 21 -22 ) የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ( 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ 15 : 56 ) ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን ( ሮሜ 6 : 7 -8 ) በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና ( ሮሜ 8 : 2 ) ቃሉ የታመነ ነው እንዲህ የሚለው፦ ከእርሱ ጋር ከሞትን፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንኖራለን ( 2ኛ ጢሞቴዎስ2 : 11 ) አዎን፥ ሙታንን በሚያነሣ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን፥ እኛ ራሳችን የሞትን ፍርድ በውስጣችን ሰምተን ነበር እርሱም ይህን ከሚያህል ሞት አዳነን፥ ያድነንማል ( 2ኛ ቆሮንቶስ 1 : 9 -10 ) ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው ? ( 2ኛ ቆሮንቶስ 2 : 16 ) ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ ተሻረው ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም ? የኵነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ፥ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና ( 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ 3 : 7 ) እኛ ወንድሞችን የምንወድ ስለ ሆንን ከሞት ወደ ሕይወት እንደ ተሻገርን እናውቃለን፤ ወንድሙን የማይወድ በሞት ይኖራል ( 1ኛ ዮሐንስ መልእክት 3 : 14 ) ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት

በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥ...በዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ተሰግስገው የገቡ ፣ እግዚአብሔርን የተኩ ፣ የአማልክት አምልኮዎች ( ክፍል ሰባት ) ( ቊጥር 10 ) ለሁሉም ሰው ለማርያምም ጭምር የኢየሱስ ሞት አስደናቂ ነው ይሁን እንጂ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ይገኝበታል በተባለው መጽሐፈ ዚቅ ፦ « ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል » የሚል ሃሳብ ተጽፎ ብናገኝም 1ኛ ) የማርያም ሞት ግን አይደለም ለእኛ ፣ ለራስዋ ለማርያም እንኩዋ ያስፈራት እንጂ ያስደነቃት አልነበረም ለምን ስንል ፦ የሞት ጣር ያዘኝ፤ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድ ደረሰብኝ ( መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 22 : 5 - 6 ) የሞት ጣር ያዘኝ፥ የዓመፅ ፈሳሽም አስፈራኝ የሲኦል ጣር ከበበኝ፤ የሞት ወጥመድም ደረሰብኝ ( መዝሙረ ዳዊት 18 : 4 - 5 ) ልቤ በላዬ ተናወጠብኝ፥ የሞት ድንጋጤም ወደቀብኝ ( መዝሙረ ዳዊት 55 : 4 ) የሞት ጣር ያዘኝ፥ የሲኦልም ሕማም አገኘኝ፤ ጭንቀትንና መከራን አገኘሁ ( መዝሙረ ዳዊት 116 : 3 ) ፊቴ ከልቅሶ የተነሣ ቀላ የሞት ጥላ በዓይኖቼ ቆብ ላይ አለ ( መጽሐፈ ኢዮብ 16 : 16 ) የጥዋት ብርሃን ለእነርሱ ሁሉ እንደ ሞት ጥላ ነው የሞትን ጥላ ድንጋጤ ያውቃሉና (መጽሐፈ ኢዮብ 24 : 17 ) 2ኛ ) በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ራሱ በሥጋው ወራት ፦ ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት ይለናል ዕብራውያን 5 : 7 ከዚያ በፊት ግን ፦———————————— ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም፦ አባት ሆይ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 41 - 42 ) ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 43 - 44 ) ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው ስለ ምን ትተኛላችሁ ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው ( የሉቃስ ወንጌል 22 : 45 - 46 ) 3ኛ ) ኢየሱስ በሥጋና በደም እንዲሁ በመካፈሉ የመጣ ለውጥ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ ይለናል ( ዕብራውያን 2 : 14 - 15 ) 4ኛ ) ይህ እንዲሆን ታድያ ኢየሱስ የተናገረው ፣ አባቱም እግዚአብሔር ያደረገው ወይም የሠራው ሥራ ነበረ እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች ይሰጣል፤ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል ( የማቴዎስ ወንጌል 20 : 18 ) እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች አልፎ ይሰጣል፥ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል፥ ለአሕዛብም አሳልፈው ይሰጡታል ( የማርቆስ ወንጌል 10 : 33 ) እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና ( የሐዋርያት ሥራ 2 : 24 ) ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ ( የዮሐንስ ራእይ 1 : 18 ) 5ኛ )ለሁሉም ሰው ለማርያምም ጭምር የኢየሱስ ሞት አስደናቂ መሆኑ በነቢዩም በኢሳይያስ፦ የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር፥ የባሕር መንገድ፥ በዮርዳኖስ ማዶ፥ የአሕዛብ ገሊላ፤ በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፥ በሞት አገርና ጥላ ለተቀመጡትም ብርሃን ወጣላቸው የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ ( የማቴዎስ ወንጌል 4 : 14 - 16 ) ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል ( የሉቃስ ወንጌል 1 : 79 ) እናንተንም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁና ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ፥ በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ ( ቆላስይስ 1 21 -22 ) የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ( 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ 15 : 56 ) ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን ( ሮሜ 6 : 7 -8 ) በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና ( ሮሜ 8 : 2 ) ቃሉ የታመነ ነው እንዲህ የሚለው፦ ከእርሱ ጋር ከሞትን፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንኖራለን ( 2ኛ ጢሞቴዎስ2 : 11 ) አዎን፥ ሙታንን በሚያነሣ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን፥ እኛ ራሳችን የሞትን ፍርድ በውስጣችን ሰምተን ነበር እርሱም ይህን ከሚያህል ሞት አዳነን፥ ያድነንማል ( 2ኛ ቆሮንቶስ 1 : 9 -10 ) ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው ? ( 2ኛ ቆሮንቶስ 2 : 16 ) ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ ተሻረው ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም ? የኵነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ፥ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና ( 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ 3 : 7 ) እኛ ወንድሞችን የምንወድ ስለ ሆንን ከሞት ወደ ሕይወት እንደ ተሻገርን እናውቃለን፤ ወንድሙን የማይወድ በሞት ይኖራል ( 1ኛ ዮሐንስ መልእክት 3 : 14 ) ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ዮናስ ጌታነህ ከጸአተ ግብጽ ኦርቶዶክሳዊና ሐዋርያዊ የተሃድሶ አገልግሎት