Saturday, 30 September 2017
መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉበት ምስጢር ( ክፍል አስራ ስምንት ) ቊጥር ፩መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉበት ምስጢር ( ክፍል አስራ ስምንት ) ቊጥር ፩ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን በዚህ አሁን በማቀርበው ትምህርት መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉበትን እውነት እንመለከታለንና ተከታተሉ መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች መሆናቸው ታስቦአል ተመዛዝኖአል ዘፍጥረት 6 ፥ 2 ፣ ዘፍጥረት 6 ፥ 4 ፣ ኢዮብ 1 ፥ 6 ፤ 2 ፥ 1 እና ኢዮብ 38 ፥ 7 ፣ ዳንኤል 3 ፥ 25 ፣ መዝሙር 29 ፥ 1 ፣ መዝሙር 89 ፥ 7 ን ይመልከቱ የኢዮብ መጽሐፍ እንደሚያመለክተን መላዕክት በእግዚአብሔር የተፈጠሩ እንኳ ቢሆኑ የተገኙት ከዘላለም በፊት ነው ኢዮብ 1 ፥ 6 ፤ ኢዮብ 38 ፥ 7 እንደገናም ሰይጣን ዲያብሎስ ከእነርሱ ጋር ነበር ይህ ማለት ግን እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለን የምናስበው አይደለም ሌላው የምንመለከተው በ King James Bible ( ኪንግ ጀምስ ባይብል ) በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ 6 ብዙ ሕዝቦች ሴቶችን አገቡ ልጆችን ወለዱ ( አፈሩ ) ማለትም ጃይንት የሆኑ ልጆችን አፈሩ ኃያል ጠንካራ የሆኑ ወንዶችን ዝነኞች የሆኑ ወንዶችን አፈሩ ይለናል መደበኛው መጽሐፍቅዱሳችንም በቃሉ እንዲህ ይላል እንዲህም ሆነ ሰዎች በምድር ላይ መብዛት በጀመሩ ጊዜ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ እግዚአብሔርም ፦ መንፈሴ በሰው ላይ ለዘላለም አይኖርም እርሱ ሥጋ ነውና ዘመኖቹ መቶ ሃያ ዓመት ይሆናሉ አለ ይለናል ዘፍጥረት 6 ፥ 1 _ 3 እንመልከት ታድያ ይህ ዓረፍተ ነገር መላዕክትን አያመለክትም ማለትም ትክክለኛ የሆኑትን ቅዱሳን መላዕክትንም ይሁን ትክክለኛ ያልሆኑትን የሚያመለክት አይደለም ይህንንም ስናረጋግጥ መንፈስ የሆኑ መላዕክትና የሰው የሆኑ ሴቶች ልጆች ተጋብተው ዘር ማፍራት አይችሉም በሐዲስ ኪዳን መላዕክት ማግባትም ሆነ መጋባት እንደማይችሉ የእግዚአብሔር ቃል በግልጽ ይናገራል የማቴዎስ ወንጌል 22 ፥ 29 እና 30 መጋባት የሚችሉት ወንዶችና ሴቶች ልጆች ናቸው ዘፍጥረት 1 ፥ 28 ፤ ዘፍጥረት 2 ፥ 18 ፣ 21 _ 24 ፤ ዘፍጥረት 3 ፥ 15 እና 16 ን ይመልከቱ ስለዚህ የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ የሚለውን በዘፍጥረት 6 ፥ 1 _ 3 የተጻፈውን ቃል የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉት መላዕክት ናቸው ብለን በመደምደም የሰውን ሴቶች ልጆች ያገቡት እነዚሁ የእግዚአብሔር ልጆች መላዕክት ናቸው ስንል ባልተገባ መልኩ ቃሉን ልንተረጒምና ለቃሉም ፍቺ ልንሰጥ መጽሐፉንም በዚህ መልኩ ልናብራራ አይገባም እንደገናም እውነተኛ ወንዶችና ሴቶች ልጆች የሚሆኑት ሰዎች ናቸው እንዴት ? ስንል ኃጢአታቸውን ሲናዘዙና ኢየሱስን ብቸኛ የሕይወታቸው አዳኝና ጌታ አድርገው ሲቀበሉ ፣ በመንፈስቅዱስም ሲጠመቁ ነው በአብዛኛው መጽሐፍቅዱስ የሚያስተላልፍልን የተለወጡ ሰዎች የእግዚአብሔር የቤተሰብ ክፍል መሆናቸውን ነው ዮሐንስ ወንጌል 1 ፥ 12 ፤ ሮሜ 8 ፥ 12 _ 19 ፤ 2ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 18 ፤ ገላትያ 4 ፥ 4 _ 6 ፤ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 3 ፥ 1 እና 2 ፤ ኤፌሶን 2 ፥ 19 እውነተኞቹም መላዕክት የሚያስገነዝቡን የእግዚአብሔር ልጆች መሆናቸውን ነው እነርሱ ከመጀመርያ ከመነሻቸው ሲፈጠሩ አንድ ዓይነትና ወጥ የሆነ መንፈሳዊነት ነው ያላቸው ፍጥረታቸውም መሠረት ያለው ነው ሰዎች ግን በሌላ መልኩ ከሥጋ ነው የተወለዱት ስለሆነም በመላዕክቱና በሰዎች መካከል የሥነ አፈጣጠር ልዩነት አለ ሰዎች በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ የተፈጠሩ ሲሆኑ ዘፍጥረት 1 ፥ 26 _ 28 ስለ መላእክትም፦ መላእክቱን መናፍስት አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል የሚያደርግ ይላል ወደ ዕብራውያንየተላከ ምዕራፍ 1 ቊጥር 7 ከዚህም ሌላ በመካከላቸው በጣም ትልቅና የተራራቀ ክሂሎት ነው ያለው ይሁን እንጂ በጌታ ወንጌል የተለወጡ ቅዱሳን ሰዎች በእርግጠኝነት ለወደፊቱ ከሞት በሚነሡ ጊዜ የፈራጅነት ሃላፊነት ይሰጣቸዋል 1ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 2 እና 3 የዛሬው የትምህርት ፍሬ ሃሳብ ይህ ነው ለተጨማሪ መረጃ ቪዲዮውን ይከታተሉ በመጨረሻም ልገልጽ የምፈልገው በኮኔክሽን ችግር ምክንያት ቪዲዮው ለሁለተኛ ጊዜ ቀጥሎ ቀርቦላችኋል ስለሆነም ተከፋፍሎ የቀረበ እንኳ ቢሆንም ትምህርቱ አንድ ወጥና ተከታታይነት ያለው በመሆኑ የተለቀቁትን ሁለቱንም ቪዲዮዎች አድምጡአቸው ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉበት ምስጢር ( ክፍል አስራ ስምንት ) ቊጥር ፩መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉበት ምስጢር ( ክፍል አስራ ስምንት ) ቊጥር ፩ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን በዚህ አሁን በማቀርበው ትምህርት መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉበትን እውነት እንመለከታለንና ተከታተሉ መላዕክት የእግዚአብሔር ልጆች መሆናቸው ታስቦአል ተመዛዝኖአል ዘፍጥረት 6 ፥ 2 ፣ ዘፍጥረት 6 ፥ 4 ፣ ኢዮብ 1 ፥ 6 ፤ 2 ፥ 1 እና ኢዮብ 38 ፥ 7 ፣ ዳንኤል 3 ፥ 25 ፣ መዝሙር 29 ፥ 1 ፣ መዝሙር 89 ፥ 7 ን ይመልከቱ የኢዮብ መጽሐፍ እንደሚያመለክተን መላዕክት በእግዚአብሔር የተፈጠሩ እንኳ ቢሆኑ የተገኙት ከዘላለም በፊት ነው ኢዮብ 1 ፥ 6 ፤ ኢዮብ 38 ፥ 7 እንደገናም ሰይጣን ዲያብሎስ ከእነርሱ ጋር ነበር ይህ ማለት ግን እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለን የምናስበው አይደለም ሌላው የምንመለከተው በ King James Bible ( ኪንግ ጀምስ ባይብል ) በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ 6 ብዙ ሕዝቦች ሴቶችን አገቡ ልጆችን ወለዱ ( አፈሩ ) ማለትም ጃይንት የሆኑ ልጆችን አፈሩ ኃያል ጠንካራ የሆኑ ወንዶችን ዝነኞች የሆኑ ወንዶችን አፈሩ ይለናል መደበኛው መጽሐፍቅዱሳችንም በቃሉ እንዲህ ይላል እንዲህም ሆነ ሰዎች በምድር ላይ መብዛት በጀመሩ ጊዜ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ እግዚአብሔርም ፦ መንፈሴ በሰው ላይ ለዘላለም አይኖርም እርሱ ሥጋ ነውና ዘመኖቹ መቶ ሃያ ዓመት ይሆናሉ አለ ይለናል ዘፍጥረት 6 ፥ 1 _ 3 እንመልከት ታድያ ይህ ዓረፍተ ነገር መላዕክትን አያመለክትም ማለትም ትክክለኛ የሆኑትን ቅዱሳን መላዕክትንም ይሁን ትክክለኛ ያልሆኑትን የሚያመለክት አይደለም ይህንንም ስናረጋግጥ መንፈስ የሆኑ መላዕክትና የሰው የሆኑ ሴቶች ልጆች ተጋብተው ዘር ማፍራት አይችሉም በሐዲስ ኪዳን መላዕክት ማግባትም ሆነ መጋባት እንደማይችሉ የእግዚአብሔር ቃል በግልጽ ይናገራል የማቴዎስ ወንጌል 22 ፥ 29 እና 30 መጋባት የሚችሉት ወንዶችና ሴቶች ልጆች ናቸው ዘፍጥረት 1 ፥ 28 ፤ ዘፍጥረት 2 ፥ 18 ፣ 21 _ 24 ፤ ዘፍጥረት 3 ፥ 15 እና 16 ን ይመልከቱ ስለዚህ የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ የሚለውን በዘፍጥረት 6 ፥ 1 _ 3 የተጻፈውን ቃል የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉት መላዕክት ናቸው ብለን በመደምደም የሰውን ሴቶች ልጆች ያገቡት እነዚሁ የእግዚአብሔር ልጆች መላዕክት ናቸው ስንል ባልተገባ መልኩ ቃሉን ልንተረጒምና ለቃሉም ፍቺ ልንሰጥ መጽሐፉንም በዚህ መልኩ ልናብራራ አይገባም እንደገናም እውነተኛ ወንዶችና ሴቶች ልጆች የሚሆኑት ሰዎች ናቸው እንዴት ? ስንል ኃጢአታቸውን ሲናዘዙና ኢየሱስን ብቸኛ የሕይወታቸው አዳኝና ጌታ አድርገው ሲቀበሉ ፣ በመንፈስቅዱስም ሲጠመቁ ነው በአብዛኛው መጽሐፍቅዱስ የሚያስተላልፍልን የተለወጡ ሰዎች የእግዚአብሔር የቤተሰብ ክፍል መሆናቸውን ነው ዮሐንስ ወንጌል 1 ፥ 12 ፤ ሮሜ 8 ፥ 12 _ 19 ፤ 2ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 18 ፤ ገላትያ 4 ፥ 4 _ 6 ፤ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 3 ፥ 1 እና 2 ፤ ኤፌሶን 2 ፥ 19 እውነተኞቹም መላዕክት የሚያስገነዝቡን የእግዚአብሔር ልጆች መሆናቸውን ነው እነርሱ ከመጀመርያ ከመነሻቸው ሲፈጠሩ አንድ ዓይነትና ወጥ የሆነ መንፈሳዊነት ነው ያላቸው ፍጥረታቸውም መሠረት ያለው ነው ሰዎች ግን በሌላ መልኩ ከሥጋ ነው የተወለዱት ስለሆነም በመላዕክቱና በሰዎች መካከል የሥነ አፈጣጠር ልዩነት አለ ሰዎች በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ የተፈጠሩ ሲሆኑ ዘፍጥረት 1 ፥ 26 _ 28 ስለ መላእክትም፦ መላእክቱን መናፍስት አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል የሚያደርግ ይላል ወደ ዕብራውያንየተላከ ምዕራፍ 1 ቊጥር 7 ከዚህም ሌላ በመካከላቸው በጣም ትልቅና የተራራቀ ክሂሎት ነው ያለው ይሁን እንጂ በጌታ ወንጌል የተለወጡ ቅዱሳን ሰዎች በእርግጠኝነት ለወደፊቱ ከሞት በሚነሡ ጊዜ የፈራጅነት ሃላፊነት ይሰጣቸዋል 1ኛ ቆሮንቶስ 6 ፥ 2 እና 3 የዛሬው የትምህርት ፍሬ ሃሳብ ይህ ነው ለተጨማሪ መረጃ ቪዲዮውን ይከታተሉ በመጨረሻም ልገልጽ የምፈልገው በኮኔክሽን ችግር ምክንያት ቪዲዮው ለሁለተኛ ጊዜ ቀጥሎ ቀርቦላችኋል ስለሆነም ተከፋፍሎ የቀረበ እንኳ ቢሆንም ትምህርቱ አንድ ወጥና ተከታታይነት ያለው በመሆኑ የተለቀቁትን ሁለቱንም ቪዲዮዎች አድምጡአቸው ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Tuesday, 26 September 2017
አዳም የእግዚአብሔር ልጅ የተባለበት ምስጢር ( ክፍል አስራ ሰባት ) አዳም የእግዚአብሔር ልጅ የተባለበት ምስጢር ( ክፍል አስራ ሰባት ) የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን በዛሬው ዕለት የምንማማረው አዳም የእግዚአብሔር ልጅ የተባለበትን ምስጢር ነው ኢየሱስ ክርስቶስ የአባት የእግዚአብሔር ልጅ ሲሆን ከድንግል ማርያም በመወለዱ ምክንያት ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል ተባለ በ2ኛ ዮሐንስ መልዕክት ቊጥር 3 ን እና በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ቊጥር 35 የተጻፈውን የእግዚአብሔር ቃል እንመልከት በሉቃስ ወንጌል 20 ፥ 36 ላይ ደግሞ ክርስቲያኖች የእግዚአብሔር ልጆች ተብለዋል በምን ምክንያት እኛ የእግዚአብሔር ልጆች ሆንን ስንል ደግሞ ትልቊ የእግዚአብሔር ልጅ ያሰኘን የትንሣኤ ልጆች ስለሆንን ነው ከዚህ በመቀጠል ግን አዳም የእግዚአብሔር ልጅ የተባለበትን እውነት እንመለከታለን አዳም የእግዚአብሔር ልጅ የተባለው በምን ዓይነት መንገድ ነው ? ስንል አዳምን ስናየው በግልጽነት የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም አዳም በምድር ላይ አባት እና እናት አልነበረውም ነገር ግን በእግዚአብሔር ተፈጥሮአል ስለዚህ አዳም በመመሣሠል ላይ የተመሠረተ ልጅነት አለው ወይ ? ስንል መልሱ ፦ በመጀመርያው ሴንቸሪ የልጅ ሃሳብ ክርስቲያኖች በጻፉት መሠረት ከዛሬው የተለየ ነው በአንድ ወቅት በነበረው ክንዋኔ ወይንም ድርጊት ልጅ ሲተረጎም ከእግዚአብሔር የመጣ እና በእርሱ መልክ የተፈጠረ ማለት ነው ዘፍጥረት 1 ፥ 26 እና 27 ን ይመልከቱ ሌላኛው ተጨማሪ መልስ ደግሞ ዘፍጥረት 5 ፥ 1 _ 3 ላይ የተጻፈ ነው ይህ የአዳም የዘር ግንድ ነው መጽሐፍም የአዳም የትውልድ መጽሐፍ ይህ ነው ይለናልና የአዳም የዘር ግንድ ነው ያልነው ከዚህ የተነሳ ነው ዘፍጥረት 5 ፥ 1 This is the book of the genealogy of Adam . In the day that God created man , he med him in the likeness of God ( English Bible Benson Commentary ) በዚያ ቀን እግዚአብሔር ሰውን ፈጠረ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው ባረካቸው በፈጠራቸውም ቀን የሰው ልጅ ብሎ ጠራቸው አዳም 130 ዓመት ኖረ በእርሱ አምሳል የተፈጠረ የእርሱ ልጅ እየሆነ ሄደ ይለናል በዚሁ በዘፍጥረት 5 ፥ 1 _ 32 መሠረት እንግዲህ አዳም የዘር ግንድ አባት ወይም መሪ ዓይነት ነው Ge 5:1-32. Genealogy of the Patriarchs ይህ ማለት አዳም የሰው ዘር መጀመርያ ወይም የሰው ዘር ማለትም የሕዝብ መጀመርያ ነው ማለታችን ነው ሌላው በዘፍጥረት 11 ፥ 4 ላይ የተጠቀሰውን ሃሳብ በማገናዘብ ይኸው ቃል የትውልድ መጽሐፍን የሚያመለክት ነው book of the generations—(See Ge 11:4). Adam:- used here either as the name of the first man or the human race generally ( English Bible Benson Commentary ) በዘፍጥረት 5 ፥ 2 ላይ ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን አዳም ብሎ ጠራቸው ይለናል ለሁለቱም አንድ ዓይነት ስም ነው የሰጣቸው አንደኛው በስነ ፍጥረት ሲሆን ከዚያ በኋላ ደግሞ በጋብቻ ነው Genesis 5:2. He called their name Adam — He gave this name both to the man and the woman. Being at first one by nature, and afterward one by marriage, it was fit they should both have the same name in token of their union.( English Bible Benson Commentary ) By giving them both one name he notes the inseparable conjunction of Man and Wife . ሌላኛው ትርጉም ደግሞ በዘፍጥረት 5 ፥ 2 መሠረት ስማቸውን በፈጠረበት አዳም ብሎ ጠራቸው ማለት ሰው ብሎ ጠራቸው ማለት ነው እግዚአብሔር የሰጣቸው ስም ሰው ወይንም የሰው ልጅ የሚል ነው ይህ የትውልድ መጽሐፍ መቅዘፍያው ወይንም መሽከርከርያው አዳም ነው ዘፍጥረት 5 ፥ 1 መቅዘፍያ ወይንም መሽከርከርያን በተመለከተ ዘፍጥረት 2 ፥ 4 ን ከዘፍጥረት 5 ፥ 1 ጋራ በንጽጽር መመልከቱ ጠቃሚነት አለው የትውልድ መጽሐፉ በተጠናቀቀ ሁኔታ የተሠራው የነበረውና የተገኘው ከአንድ ይዞታ ወይንም ከብዙ ነው ለምሳሌ ዘዳግም 24 ፥ 1 ፣ 3 የፍቺ ደረሰኝን ያሳያል ይህ ነገር ታድያ የፍቺ ደረሰኝን አሰጣጥ ጉዳይን የሚመለከት ቢሆንም የአንድ ቤተሰብን የመሠረት ሁኔታና የመነሻ ሃሳብንም ጭምር የሚያመለክት ነው The heading in Genesis 5:1 runs thus: "This is the book (sepher) of the generations (tholedoth) of Adam." On tholedoth, see Genesis 2:4. Sepher is a writing complete in itself, whether it consist of one sheet or several, as for instance the "bill of divorcement" in Deuteronomy 24:1, Deuteronomy 24:3. The addition of the clause, "in the day that God created man," etc., is analogous to Genesis 2:4; the creation being mentioned again as the starting point, because all the development and history of humanity was rooted there (English Bible Benson Commentary ) ሌላው በዘፍጥረት 5 ፥ 2 መሠረት ስማቸውን በፈጠረበት ቀን አዳም ብሎ ጠራቸው ማለት አዳም ከእግዚአብሔር የወጣ ነው እንደገናም ስሙ በእግዚአብሔር የወጣለት ነው እርሱ ቀዳሚና መጀመርያም ነው ሔዋን የመጣችው ከእርሱ በኋላ ነው ጋብቻውም የመጣው ከእርሱና ለእርሱ ነው ዘፍጥረት 2 ፥ 18 _ 25 ስለዚህ ሔዋንም በጋብቻ አንድ የምትሆነው ከእርሱ ከአዳም ጋር ነው ይህ ማለት አዳም የሚለው ስም Man and Wife ሲሆን ይህ ስም የተሰጠው በፍቅር አንድ ለመሆንና ለመገናኘት ነው ይህ ስም የተገኘው ወይም የተወረሰው ከአረብ ቃል ነው Signifying " to Join "መገናኘት ማለት ተካፋይ መሆን ማለት ነው ውድ ወገኖቼ አሁንም በዘፍጥረት 1 ፥ 26 እና 27 የተጻፈውን ሃሳብ መሠረት አድርገን ስናብራራ በአንድ ወቅት በነበረው ክንዋኔ አዳም ከእግዚአብሔር የመጣና በእርሱ መልክ የተፈጠረ ሆኖ በቀላሉ ሲተረጎም ልጅ የሚለውን ስያሜ ያሰጠው ቢሆንም በግሪኩ ትርጉም ግን ልጅ ብሎ አልተጠቀመም ሁሉም የዘር ግንድ የሚሄደው ወደ ተመሠረተበት ነውና በዚያን ጊዜ ልጅ የሚለው ቃል በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ቊጥር 23 ላይ ኢየሱስ አገልግሎቱን ሲጀምር ዕድሜው 30 ዓመት ያህል ነበር ሕዝቡ እንደመሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ ስለሚለን ቃሉ ኢየሱስ በትክክለኛ የዘር ግንድ ወይንም በትውልድ መጽሐፍ የተቆጠረ የዮሴፍ ልጅ ሳይሆን ለምናልባቱ ማለትም በአይሁድ ልማድ ያለወንድ ዘር ጸንሳ የተገኘች አመንዝራ ተብላ ትወገራለችና ማርያምን ከአይሁድ የድንጋይ መወገር ለመጠበቅ ሲባል የዮሴፍ ልጅ ነው ተባለ ኢየሱስ ግን ያለወንድ ዘር ከመንፈስቅዱስ የተጸነሰ በመሆኑ በሥጋ ከድንግል ማርያም የተወለደ ቢሆንም የዮሴፍ ልጅ ሳይሆን የእግዚአብሔር ልጅ ነው ድንግል ማርያምንም መልአኩ መልዕክትን ይዞላት ሲመጣ የተናገረው መንፈስቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል የሚል በመሆኑ ድንግል ማርያም የወለደችልን የዮሴፍን ልጅ ሳይሆን የእግዚአብሔርን ልጅ ነው አይሁድ ግን በልማዳቸው መሠረት ሕዝቡ እንደመሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ ተብሎም በቃሉ ስለተጻፈ እስከ ዛሬ ድረስ ሞትን ድል ነስቶና ሥራችንን ሁሉ ሰርቶ በአብ ቀኝ የተቀመጠልንን የናዝሬቱ ኢየሱስን የዚያ የጠራቢው የዮሴፍ ልጅ ነው ይሉታል እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናቸውን ያብራላቸው የማርቆስ ወንጌል 6 ፥ 1 _ 6 ፤ የማቴዎስ ወንጌል 27 ፥ 62 _ 66 ፤ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 28 የኢየሱስን መነሣትና የመነሳቱንም ውጤት የሚናገር በመሆኑ ምዕራፉን በሙሉ አንብቡት በመሆኑም ኢየሱስ ለምናልባቱ የዮሴፍ ልጅ ነው የተባለ እንኳ ቢሆንም በሉቃስ ወንጌል 3 ፥ 22 ላይ በተጻፈው የእግዚአብሔር ሃሳብ መሠረት ግን መንፈስቅዱስ በአካል መልክ እንደ ርግብ በእርሱ ላይ ሲወርድ እግዚአብሔር አብ ደግሞ የምወድህ ልጄ አንተ ነህ በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምጽ ከሰማይ አምጥቷል ክብር ለእርሱ ለአምላካችን ይሁንለት ከዚህ የተነሣ በሉቃስ ወንጌል 3 ፥ 23 _ 28 ያለው የኢየሱስ ክርስቶስ የዘር ግንድ የሚያልቀው በኢየሱስ ነው የሚጀምረው በአዳም የእግዚአብሔር ልጅነት ነው ኢየሱስ ለእኛ ራሱን ሲያረጋግጥ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ትርጉሙም በቀላሉ እርሱ ጻድቅ እንደነበረ በእርሱ ያመኑና ጻድቃን የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከአዳም ፍጥረት ጀምሮ ያሉት ናቸው አለበለዚያ ሉቃስ አዳም የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብሎ አያረጋግጥልንም ነበር ሕጉም ዳዊት የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብሎ አያረጋግጥልንም ነበር ኢየሱስ የተወደደና የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ አስደሳች ልጅ እንደ መሆኑ መጠን በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ የዳነው ፣ የእግዚአብሔር ልጅም የሆነው አዳምና የአዳም ዘር በሙሉ እንዲሁ እንዲሆን ይፈለጋል እንደገናም የሉቃስ የዘር ግንድ አሁንም በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ ስለዳነው ስለ አዳምና ስለ ዘሩ ሲናገር በመለኮታዊ የመፍጠር መፍለቅያ ሃሳብ የሚመራው ወደ ኢየሱስ ነው የሉቃስ ወንጌል 3 ፥ 38 ጌታ እግዚአብሔር የምናነበውን ይህንን ቃል ይባርክልን ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Friday, 22 September 2017
ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ( ክፍል አስራ ስድስት ) ቊጥር ፫ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ( ክፍል አስራ ስድስት ) ቊጥር ፫ የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሰላም ለእናንተ ይሁን በዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው በሚለው የክፍል አስራ ስድስትና የቊጥር ፫ ትምህርታችን ላይ ለኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅነት ብዙ አስረጂ የሆኑ ጥቅሶች ቀርበዋል እኔ ግን በዋናነት በዚህ ጽሑፌ ላይ ላሰፍረው የፈለኩት መናፍስት ሳይቀሩ ለእግዚአብሔር ልጅ እውቅና በመስጠት ኢየሱስ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ ካንተ ጋር ምን አለን ? ጊዜው ሳይደርስ ልታሰቃየን መጣህን ? እያሉ የጮሁበትን እውነት ነው ለማሳየት የፈለኩት የማቴዎስ ወንጌል 8 ፥ 29 እንመልከት ከዚሁ ጋር በተያያዥነት የሚቀርብ ሌላም የመጽሐፍቅዱስ እውነት አለ አጋንንትም ደግሞ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉ እየጮሁም ከብዙዎች ይወጡ ነበር ገሰጻቸውም ክርስቶስም እንደሆነ አውቀውት ነበርና እንዲናገሩ አልፈቀደላቸውም ይለናል የሉቃስ ወንጌል 4 ፥ 41 በሌላም ክፍል ላይ በዚያን ጊዜም በምኩራባቸው ርኩስ መንፈስ ያለው ሰው ነበረ እርሱም የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለን ? ልታጠፋን መጣህን ? ማን እንደሆንህ አውቄያለሁ የእግዚአብሄር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ ይለናል ኢየሱስም ለዚሁ ክፉ መንፈስ አሁንም መልስ ሲሰጥ ዝም በል ከእርሱም ውጣ አለው ብሎ ነው የእግዚአብሔር ቃል የሚነግረን የማርቆስ ወንጌል 1 : 24 ን ይመልከቱ ታድያ የናዝሬቱ ኢየሱስ በተደጋጋሚ ትክክለኛ መሲህነቱን ፣ ክርስቶስነቱን ፣ የእግዚአብሔር ልጅነቱንና ቅዱስነቱን አንስተው ጊዜው ሳይደርስ ሳይቀር እንዳያጠፋቸው በብዙ ልመና የተማጸኑትን የእጋንንትን ምስክርነት ባለመቀበል ዝም ብለው ብቻ እንዲወጡ የተናገረበትን ሃሳብ ስንመለከት ምን እናስባለን ? ኢየሱስ ይህን እውነታዊነት ሲያይ ትክክል የሆነውን ምስክርነት ያልተቀበለበት ምክንያት ምንድርነው እንላለን ? መልሱ ለእኔ እንደሚገባኝና መጽሐፍቅዱሴም እንደሚያስተምረኝ ጌታችን ኢየሱስ ይህንን ምስክርነት መስማት የሚፈልገው ከአጋንንት ሳይሆን ከዳኑና ከዚሁ ከአጋንንት እስራት ከተፈቱ ከሰዎች ልጆች ነው ለዚህም ነው በብዙ ሰንሰለት ታስሮ በመቃብርና በተራራ ይጮህ የነበረውን ይህንን ሰው ከዚሁ ከሌጌዎን የአጋንንት እስራት ከፈታው በኋላ ወደ ቤትህ በቤተሰቦችህ ዘንድ ሄደህ ጌታ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገልህ እንዴትስ እንደማረህ አውራላቸው ያለው ይህም ሰው ሄዶ ኢየሱስ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገለት በቤቱና በቤተሰቦቹ ዘንድ ብቻ ሳይሆን አሥር ከተማ በሚባል ሀገር ይሰብክ እንደነበርና ሁሉም ይደነቁ እንደነበር የክፍሉ ሃሳብ ያስተምረናል የማርቆስ ወንጌል 5 ፥ 1 _ 20 ከዚሁ ጋር በማርቆስ ወንጌል 16 ፥ 9 ላይ ከሳምንቱ በመጀመርያው ቀን ማልዶ በተነሳ ጊዜ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግደላዊት ማርያም ታየ ስለሚለን በሉቃስ ወንጌል 8 ፥ 2 ላይ ደግሞ አሥራ ሁለቱም ከእርሱ ጋር ነበሩ ከክፉዎች መናፍስትና ከደዌም ተፈውሰው የነበሩ አንዳንድ ሴቶች እነርሱም ሰባት አጋንንት የወጡላት መግደላዊት የምትባል ማርያም የሄሮድስ አዛዥ የኩዛ ሚስት ዮሐናም ሶስናም ብዙዎች ሌሎችም ሆነው በገንዘባቸው ያገለግሉት ነበር ስለሚለን በተያያዥነት ልንመለከተው እንችላለን ውድ ወገኖቼ ሆይ መጽሐፍ ሲናገር ወበእንተ ዝንቱ አስተርአየ ወልደ እግዚአብሔር ከመ ይስአር ግብሮ ለጋኔን ይለናል ወደ አማርኛው ስመልሰው ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ የሚለውን ትርጉም የሚሰጠን ነው 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 3 ፥ 8 ን ይመልከቱ የዲያብሎስ ሥራ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ የፈረሰው በዚሁ በእግዚአብሔር ልጅ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው ታድያ ጌታችን ኢየሱስ ሥራውን ያፈረሰበት ብቻ ሳይሆን አለቅነቱን የሻረበት ሥልጣኑንም ገፎ ድል በመንሳት ጭምር በግልጥነት እያሳየ ያዞረው ነው እነዚህ ጥቅሶች የተናገርኩትን ሃሳብ በግልጥ የሚያብራሩ ስለሆኑ አስተውለው ይመልከቷቸው ኤፌሶን 2 ፥ 1 እና 2 ፤ ቆላስያስ 2 ፥ 14 እና 15 ፤ ዕብራውያን 2 ፥ 14 እና 15 ከዚህ የተነሳ አሁን የአምላካችን ማዳንና የክርስቶስም ሥልጣን ሆኖአል በቀንና በሌሊት የሚከሰንም የወንድሞች ከሳሽ ተጥሏል እኛም ከበጉ ደምና ከምሥክራችን ቃል የተነሳ ድል ነስተነዋል ራዕይ 12 ፥ 7 _ 12 እንመልከት በመሆኑም ታድያ መጽሐፍቅዱሳችን ይህንን እውነት በግልጥነት እያስቀመጠልን ሰዎች ግን ዛሬም በዘመናችን ከአጋንንት እስራት ለመፈታትና ከደዌያቸውም ለመፈወስ ሲሉ መቊጠርያና በትረ መስቀል ወደያዙ ባሕታውያንና አጥማቂ ነን ባይ ሰዎች እየሄዱ በበትረ መስቀሉ ግንባራቸው እስኪቆስል ድረስ ይጠፈጠፋሉ እንደገናም ይህ አልበቃ ብሎአቸው አጋንንቱ ከውስጣቸው እንዲወጣ ተብሎ ወፋፍርና ድቡልቡል በሆኑ የእንጨት መቁጠርያዎች ጀርባቸው እስኪመለጥ ድረስ ይደበደባሉ እንደገናም በማለዳ ከቧንቧ በተቀዳ የበርሜል ቀዝቃዛ ውሃ ይነከራሉ ነገር ግን ከስቃዩ ብዛት የተነሳ የድረሱልኝ ያክል ከሚጮህና ከሚሰቃይ ሰው በስተቀር በዚያ ፈውስም ሆነ ድህነት የለም አጋንንት የሚወጣውም ሆነ ደዌ የሚፈወሰው ከላይ ባብራራሁት ቃል መሠረት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ብቻ ነው ጌታችን ኢየሱስ አጋንንትን እንዲያስወጡና ሕሙማንን እንዲፈውሱ ለሐዋርያቱ ትዕዛዝ ሰጥቶአቸዋል ይሄ ትዕዛዝ ታድያ ለእኛም ይሄ እምነት ላለንና አሜን ብለን ትዕዛዙን በመቀበል ልንተገብረው ለወደድን ሁሉ ይሰራል የማቴዎስ ወንጌል 10 ፥ 8 ከዚህም ሌላ እባቡንና ጊንጡን ይረግጡ ዘንድ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ የሚጎዳችሁ ምንም የለም ብሎአቸዋል የሉቃስ ወንጌል 10 ፥ 17 _ 20 ይህንን ያደረጉት ግን ሐዋርያቱ እንዲሁ ከሜዳ ተነስተው ሳይሆን አምነው ነው ለዚህም ነው በማርቆስ ወንጌል 16 ፥ 17 እና 18 ፥ ላይ ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ እባቦችን ይይዛሉ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ ያለን ስለዚህ አጋንንትን ለማስወጣትም ሆነ ድውያንን እጅ ጭኖ ለመፈወስ በመጀመርያ በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ የዳነ ትክክለኛ አማኝና ዳግምም የተወለደ ክርስቲያን መሆን ያስፈልጋል በክርስቶስ ኢየሱስ ብቸኛ አዳኝነት ያላመነና ዳግምም ያልተወለደ ሰው ይህንን ነገር ለማድረግ አይችልም ከዚህ የተነሳም ነው እንግዲህ የአስቄዋ ልጆች ጉድ የሆኑት አጋንንቱ እናንተ እነማን ናችሁ ? አላቸው አቆሰላቸው ፣ ደበደባቸው ፣ አሸነፋቸው ታድያ አንዳንዴ የማን መሆናችንን ሳናውቅና ሚናችንንም ሳንለይ በምንሰጠው አገልግሎት የአስቄዋ ልጆች ዕጣ ፈንታ የእኛም ይሆናል የሐዋርያት ሥራ 19 ፥ 11 _ 20 ከዚህ የተነሳ ይህን የሚያደርጉ ባሕታውያን እና አንዳንድ አጥማቂ ነን ባይ ሰዎች ዛሬ ላይ ባይመስላቸው ውሎ አድሮ እንደ አስቄዋ ልጆች ያለ ጉዳት ማጋጠሙ አይቀርምና ራሳቸውም ተጎድተው ሕዝባችንንም እንዳይጎዱ ሊያስቡበት ሊጠነቀቁም ይገባል እላለሁ ሕዝባችንንም ማሳሳት የለባቸውም ብዬ ጽኑ የሆነውን ምክሬንም ላስተላልፍላቸው እወዳለሁ የቤተክርስቲያኒቱ አመራርና የሲኖዶስ አባላትም ለዚሁ ጉዳይ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በእንዲህ ዓይነት ተግባር ተሰማርተው ፍጹም ርህራሄ በጎደለው የጭካኔ ድርጊት ፣ መጽሐፍቅዱሳችንም በማያዘው መንገድ አጋንንትን ካላስወጣን ፣ ደዌንም ካልፈወስን ሲሉ በመቊጠርያና በበትረ መስቀላቸው ሕዝቡን የሚቀጠቅጡትን ባሕታውያንና አጥማቂ ነን ባይ ሰዎችን ከወዲሁ በጊዜ ፣ ነገር ሳይበላሽ ፣ ሃይ ፣ ተዉ ፣ ተከልከሉ ሲል ሊገስጻቸው ፣ እገዳም ሊጥልባቸውና ሊያስቆማቸውም ይገባል እላለሁ ይሁን እንጂ ይህንን ሥራ በተገቢው መንገድ እናካሂዳለን ሲሉ የሚፈልጉት ከሆነም ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት በመላክ እንዲማሩና ትክክለኛውንም መጽሐፍቅዱሳዊ እውቀት አግኝተው እንዲያገለግሉ ቢደረግ ቤተክርስቲያኒቱ ይበልጥ መልክ ያላትና የተስተካከለች ትሆናለች ከጥፋትም ትድናለች ስል አስተያየቴን አክዬ በመጻፍ ለሚመለከተው ሁሉ አቤቱታዬን ለማቅረብ እወዳለሁ ጌታ እግዚአብሔር ለኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያናችን ትክክለኛ የተሃድሶ ዘመን ያምጣልን ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Monday, 18 September 2017
ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ( ክፍል አስራ ስድስት ) ቊጥር ፪ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ( ክፍል አስራ ስድስት ) ቊጥር ፪ የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው በሚለው በክፍል አስራ ስድስትና በቊጥር ፪ ትምህርታችን ላይ ዛሬም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነበትን ብዙ የሆኑ የመጽሐፍቅዱስ አስረጂ ጥቅሶችን አቅርቤያለሁ ነገር ግን ከዚህ የቊጥር ፪ ትምህርት ውስጥ ዋና ክፍል ነው ብዬ የጠቀስኩትን ሃሳብ በጥቂቱ ላቀርብላችሁ እወዳለሁ እናንተ ግን ሙሉውን የቪዲዮ መልዕክት ልትከታተሉ ትችላላችሁ ይሄ ዋና ሃሳብ የተባለው ግን አባት እግዚአብሔር ለኢየሱስ ክርስቶስ የልጅነት እውቅናን የሰጠበት እውነት ነው እርሱን ነው ላብራራው የፈለኩት ታድያ ይህ አባት እግዚአብሔር ለጌታችን ኢየሱስ የልጅነት እውቅናን የሰጠው መጽሐፉ በሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 33 ላይ እንደሚነግረን ይህን ተስፋ እግዚአብሔር በሁለተኛው መዝሙር ደግሞ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድኩህ ተብሎ እንደተጻፈ ኢየሱስን አስነስቶ ለእኛ ለልጆቻቸው ፈጽሞአልና ስለሚለን የኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን የተረጋገጠው ኢየሱስ በሥጋ በተገለጠበት ጊዜና ሕጻን ሆኖም ሳለ በእናቱ እቅፍ ውስጥ በነበረበት ጊዜ እግዚአብሔር አብም በሰማይ ሆኖ ለኢየሱስ ምስክርነት በሰጠበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን የሐዋርያት ሥራ 13 ፥ 33 መጽሐፍ በሁለተኛው መዝሙር ደግሞ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድኩህ ብሎ በጠቀሰልን በመዝሙር 2 ፥ 7 እና 8 በግዕዙ ቃል እግዚአብሔር ይቤለኒ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ሰአል እምኔየ እሁበከ አሕዛበ ለርስትከ ይለናልና ወደ አማርኛው ስተረጉመው እግዚአብሔር አለኝ ፦ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድኩህ ለምነኝ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ ይለናልና ኢየሱስ በቅድምና የእኛን ሥጋ ለብሶ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ከመሆኑ በፊት በዚሁ በተጠቀሰልን በመዝሙሩ ቃል መሠረት ይሄው ኢየሱስ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጁ ነው የዕብራውያን መጽሐፍም ይህንን ሃሳብ ሲያጠናክረው ከመላዕክትስ ፦ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ ደግሞም እኔ አባት እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል ያለው ከቶ ለማን ነው ? በማለት የኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅነቱ የብቻው መሆኑን በሚገርም ሁኔታ ገለጸልን ዕብራውያን 1 ፥ 5 ለዚህም ነው ዮሐንስ በወንጌሉ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና ያለን ዮሐንስ ወንጌል 3 ፥ 16 ን እንመልከት በመሆኑም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው የእግዚአብሔር አብ አንድያ የባሕርይ ልጁ ነው ክብር ለእርሱ ይሁንለት እንደገናም ኢየሱስ ክርስቶስ በዘላለማዊ ሕይወት የእግዚአብሔር ልጅ ነው እንዴት ? ስንል በዮሐንስ ወንጌል 1 ፥ 18 ላይ መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው ይለናልና ስለዚህ ኢየሱስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም በሥጋ ተወልዶ በቤተልሔም በግርግም ውስጥ በእናቱ እቅፍ ውስጥ እንደነበረ ሁሉ በቅድምናም በማይታየው በባሕርይ አባቱ በእግዚአብሔር እቅፍ ውስጥም የነበረ መሆኑን መጽሐፉ በሚገባ አብራርቶልናል ለዚህም ነው ያላየነውንና ልናየውም የማንችለውን እግዚአብሔርን በአባቱ እቅፍ ያለው አንድ ልጁ እርሱ ተረከው የሚለውን የቃሉን እውነት ያነበብነው በመሆኑም ይህንን መሠረት አድርጋ ጥንታዊትና ኦርቶዶክሳዊት ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን በ፫፻፲ወ፰ቱ ርቱዓነ ሃይማኖት በተወሰነ የኒቅያ ጉባኤ ጸሎተ ሃይማኖት በተሰኘው የእምነት መግለጫዋ ላይ ወነአምን በአሐዱ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ አብ ዋሕድ ዘህልው ምስሌሁ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም ብርሃን ዘእምብርሃን አምላክ ዘእም አምላክ ዘበአማን ዘተወልደ ወአኮ ዘተገብረ ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ ያለችው ወደ አማርኛው ስተረጉመው ዓለም ሳይፈጠር የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን እርሱም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ የሚሆን የተፈጠረ ያይደለ የተወለደ በመለኮቱ ከአብ ጋር አንድ የሆነ በማለት ይህንኑ የእምነት መግለጫዋን መሠረት አድርጋ ነገረችን « ድንቅና ይበል የሚያሰኝ የእምነት መግለጫ ነው !! » ታድያ ሌላ ነገር ሳንጨምርና ሳንቀንስ ይህንኑ የእምነት መግለጫ ብቻ ለእምነታችን መቆም ብንማር ዛሬ ሕዝባችን የት በደረሰ ታድያ ምን ያደርጋል አሁን ግን ሕዝባችን እንዲህ አይደለም እና ያለው እጅግ በጣም ያሳዝናል ልብንም ይሰብራል ወደ ትምህርቱም ስመለስ ከቃሉ ጋር በተገናዘበ መልኩ ይኸው የኦርቶዶክሱ የእምነት መግለጫው እንዳለን ኢየሱስ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው የእግዚአብሔር አንድያ የባሕርይ ልጁ ሆኖ ሳለ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ፣ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ ፣ የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ ነው የምናነበውን ቃል እግዚአብሔር ይባርክልን ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ
Thursday, 14 September 2017
ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ( ክፍል አስራ ስድስት ) ቊጥር ፩ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ( ክፍል አስራ ስድስት ) ቊጥር ፩ የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን በክፍል አስራ ስድስት ትምህርት ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በተከታታይ ከዚህ ክፍል ጀምሮ የምንማማረው ጉዳይ ይሆናል የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነውና የእግዚአብሔር ልጅ መሆን የእግዚአብሔር ባሕርይ ዓይነት መሆን ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ባሕርይ አለኝ ማለት እግዚአብሔርን በመሆኑ ለአይሁድ መሪዎች ስድብ ነው ስለሆነም የኢየሱስን ሞት ጠየቀ ይህንንም ለመረዳት የማቴዎስ ወንጌል 26 ፥ 65 እና 66 ን ከዘሌዋውያን 24 ፥ 15 ጋር ተያይዞ የቀረበውን ሃሳብ መመልከቱ በቂ ግንዛቤን እንድናገኝ ያደርገናል ኢየሱስ ግን የእግዚአብሔር አብ የባሕርዩ ምሳሌና የክብሩ መንጸባረቅ ነው ዕብራውያን 1 ፥ 3 እንደገናም የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ስለሆነ ኢየሱስ የተገለጠ እግዚአብሔር ነው ዮሐንስ ወንጌል 1 ፥ 1 ፣ 14 ) ትምህርቱ እንግዲህ ይህ ብቻ አይደለም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን የሚገልጹ ብዙ የመጽሐፍቅዱስ ክፍሎች ተጠቅሰው ተብራርተውበታል ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ
Tuesday, 12 September 2017
ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለተኛው አዳም ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 5 ) ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለተኛው አዳም ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 5 ) ሰላም ለእናንተ ይሁን ወገኖች በዚህ ትምህርት ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ የአዳም ልጅ የተባለበትን እውነት እንመለከታለን 1ኛ ) የሰው ልጅ ትርጉሙ የአዳም ልጅ ማለት ነው በዘፍጥረት 1 ፥ 26 ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጅ እንደሆነ ሁሉ በሂብሩ የትርጉም አፈታት ወይም አነጋገር ደግሞ የአዳም ልጅ ነው ምንጩ ያልተደባለቀውንና ዋነኛውን ለአዳም የተሰጠውን ተስፋ የወረስነው በአዲስ ፍጥረትነት ባለ የበላይነት ግዛት ነው ምክንያቱም አዳም በኃጢአት ስለወደቀ በካሳ ወይም በቅጣት መልክ የሚከፈል የሕይወት ክፍያ ነበር ከዚህ በመቀጠል ይህንን እውነት የሚጠቁሙ ጥቅሶች እንደሚከተለው አስቀምጣለሁ ፦ ( ሮሜ 5 ፥ 12 _ 21 ፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 15 ፥ 45 ፤ ዕብራውያን 2 ፥ 6 _ 9 ፤ መዝሙር 8 ፥ 4 _ 6 እንመልከት ) 2ኛ ) የሰው ልጅ ማለት በአማካኝ ምን እንደሆነ ትምህርቱ ይጠቁመናል ( ዘኁልቊ 23 ፥ 19 ፤ ኢዮብ 25 ፥ 6 ፤ ኢዮብ 35 ፥ 8 ፤ መዝሙር 8 ፥ 4 ፤ መዝሙር 79 ( 80 ) ፥ 17 ፤ መዝሙር 144 ፥ 3 ) 3ኛ ) ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔራዊ መልክና መጠን ሲኖር ሳለ በምድር ላይ ራሱንና የኑሮ ደረጃውን የገለጠባቸው መንገዶች ምክንያታዊ መሆናቸው የማቴዎስ ወንጌል 8 ፥ 20 ፤ የሉቃስ ወንጌል 9 ፥ 58 ፤ የማቴዎስ ወንጌል 11 ፥ 19 ፤ የሉቃስ ወንጌል 7 ፥ 34 ፤ የማቴዎስ ወንጌል 16 ፥ 13 ፣ 15 ፤ የሉቃስ ወንጌል 6 ፥ 22 ፤ የዮሐንስ ወንጌል 9 ፥ 35 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ትምህርቶቹ በእነዚህ ሃሳቦች ዙርያ የተጠቃለሉ ናቸው ተከታተሉት አጥኑት ጌታ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Thursday, 7 September 2017
ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 4 ) ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 4 ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዛሬው ትምህርት በቋሚነት የሚያጠነጥነው ኢየሱስ በሰማይ የሰው ልጅ ተብሎ ቀጥሏል ወደ ሰማይ የሚያስገባንንም ሥራ በምድር ሠርቷል በሚል ሃሳብ የቊጥር 3 እና የቊጥር 4 ትምህርት ሰኞና ዛሬ ሐሙስ በተያያዥነት ቀርቦላችኋል እንድትከታተሉት በጌታ ፍቅር ለማሳሰብ እወዳለሁ ጌታ ዘመናችሁን ይባርከው ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Monday, 4 September 2017
ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 3 ) ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 3 ) የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን የዛሬው ትምህርት በቋሚነት የሚያጠነጥነው ኢየሱስ በሰማይ የሰው ልጅ ተብሎ ቀጥሏል ወደ ሰማይ የሚያስገባንንም ሥራ በምድር ሠርቷል በሚል ሃሳብ የቊጥር 3 እና የቊጥር 4 ትምህርት ዛሬ እና በሚቀጥለው ሐሙስ የሚቀርብ ይሆናል እንድትከታተሉት በጌታ ፍቅር ለማሳሰብ እወዳለሁ ጌታ ዘመናችሁን ይባርከው ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Friday, 1 September 2017
ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 2 ) ኢየሱስ የሰው ልጅ ነው ( ክፍል አስራ አምስት ቊጥር 2 ) የተወደዳችሁ ወገኖችና የእግዚአብሔር ሕዝቦች ኢየሱስ የሰው ልጅ የሆነበትን ተከታታይና ቀጣይ ትምህርት በሰዓቱ በዚሁ የፌስቡክ ላይቭ እየገባችሁ ስለተከታተላችሁ ጌታ እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ በማለት ላመሰግናችሁ እወዳለሁ በመቀጠልም ወደ ዛሬው ትምህርት ሳልፍ ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣበትን መሠረታዊ ምክንያት ተናግሯል አንዱና ዋነኛው ምክንያትም በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 19 ፥ 10 ላይ በተጻፈው ሃሳብ መሠረት በግዕዙ ቃል እንዲህ ይላል ወይቤሎ ኢየሱስ ዮምሰ ሕይወት ኮነ ለዝንቱ ቤት እስመ አንተሂ ወልደ አብርሃም አንተ እስመ መጽአ ወልደ እጓለ እመሕያው ይኅሥሥ ወያድኅን ዘተሐጉለ ወደ አማርኛው ስተረጉመው ኢየሱስም እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነውና ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአልና በማለት ይነግረናል ስለዚህ ኢየሱስ የጠፋነውን የፈለገንና ያዳነን በሰውነቱም ጭምር በመሆኑ የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአል ተባለ እንደገናም ኢየሱስ የሰው ልጅ በመሆኑ በሰውነቱም የተሰቃየ ነበረ በማርቆስ ወንጌል 8 ፥ 31 ላይ የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል ከሽማግሌዎችም ከካህናት አለቆችም ከጻፎችም ሊጣል ሊገደልም ከሦስት ቀንም በኋላ ሊነሣ እንዲገባው ያስተምራቸው ጀመር ይለናል ከዚህም ሌላ የሰው ልጅ እንደተጻፈለት እንደሚሄድ ተናግሯል በማቴዎስ ወንጌል 26 ፥ 24 እና 25 ላይ የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደተጻፈ ይሄዳል ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አለ አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳም መልሶ መምህር ሆይ እኔ እሆንን ? አለ አንተ አልህ አለው ይለናል ሌላው የሰው ልጅ የሚለው ታይትል በሰውነት ውስጥ ያለውን የሐሴት ሕግ የሚያመለክተን ነው በማቴዎስ ወንጌል 25 ፥ 31 _ 33 ላይ የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላዕክቱ ሁሉ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ እረኛም በጐቹን ከፍየሎቹ እንደሚለይ እርስ በእርሳቸው ይለያቸዋል በጐችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል ይለናል የሰው ልጅ የተባለው ኢየሱስ የሰው ልጅ የሚለውን ታይትል በመያዙ መሲሃኒክ ስያሜ ( ማሳያ )ነው It is a messianic designation የሰው ልጅ የሚለው ታይትል መሲሁን የሚያሳይ ነው ትንቢተ ዳንኤል 7 ፥ 13 እና 14 ከዚህ ሃሳብ እንደምንረዳው ኢየሱስ ክርስቶስ በሥልጣኑና በበላይነት ግዛቱም የሰው ልጅ ነው የሰው ልጅ የሚለው ታይትሉ ዋና አጉልቶ የሚያሳየው የእርሱን የበላይነት ፣ ግዛቱን ፣ ሥልጣኑን ሲሆን እንደገናም እርስ በእርሱ የተጋጨና የተጻረረ የሚመስለው ያ ክብር የሚገኘው በመስቀሉ ሥር ባለ ትሕትና ነው ይህንንም በመስቀሉ ሥር ያለን ትሕትና ኢየሱስ ራሱን ባዶ በማድረግና ራሱን በማዋረድ ለሞትም ይኸውም ለመስቀል ሞት ሳይቀር የታዘዘ ሆኖ ገልጾታል በዚህም ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው ይለናል ፊልጵስዩስ 2 ፥ 1 _ 11 ታድያ እኛም ክርስቲያኖች ማለትም የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የአካሉ ብልትና አባላት የሆንን በሙሉ በዚህ ትሕትና ውስጥ ስንመጣ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የሆነው ሥልጣንና የበላይነት መግዛቱም ሳይቀር ይገለጥብናል በዚሁ በትንቢተ ዳንኤል 7 ፥ 13 እና 14 መሠረት ታይትሉ ወይም ርዕሱ የሚያጐላው ፣ በጣምም የሚያሳስበውና የሚያጋንነው እርሱ ሰው እንደሆነ ነው The title Emphasizes that He was Human ኢየሱስ የሰው ልጅ የተባለውን ታይትል ሲጠቀም አቅርቦ ሊያሳየን የፈለገው እውነት እርሱ ሙሉ ለሙሉ ሰው መሆኑን ነው ከዚህም ሌላ የእርሱን የበላይነት ፣ ግዛቱ ማለቅያ የሌለው ፣ የማያልፍና የዘላለም ግዛት ነው መንግሥቱም አንድና የማይጠፋ መንግሥት ነው His dominion is an everlasting dominion that will not pass away and his kingdom is one that will never be destroyed ትንቢተ ዳንኤል 2 ፥ 36 _ 45 ፣ መዝሙር ( 103 ) ፥ 19 ፣ የሉቃስ ወንጌል 1 ፥ 33 ስለዚህ ኢየሱስ የሰጠን አንዱ መንግሥት በክብሩና በመንግሥቱ የበላይ ነው ከዚህም ሌላ ሊቀካህናቱ ኢየሱስ መሲህ ለመሆኑ ባቀረበው የሙከራና የመፈተኛ ጥያቄ ይህንን ምላሽ ኢየሱስ በትንቢታዊ ቃል አስተላለፈ የማቴዎስ ወንጌል 26 ፥ 63 እና 64 ን ይመልከቱ በመሆኑም በዚህ የቃል ምላሽ መሠረት የሃይማኖት መምህሩ የተቆጣውና ልብሱንም እስከመቅደድ ድረስ ደርሶ ክርስቶስንም የከሰሰው ኢየሱስን የእግዚአብሔርን ስም በክፉ በማንሳት ከራሱ ከእግዚአብሔር ጋር የእኩልነት ሥልጣን መብት ጠይቋል በማለት ነው ታድያ ይህ ሊቀ ካህን ብቻ ሳይሆን እርሱን የመሠሉ ፈሪሳውያንና የሕግ መምህራኑም ጭምር ኢየሱስን የዛ የጠራቢው የዮሴፍ ልጅ ነው ብለው ስለሚያስቡ ግምታቸው ከዚህ የዘለለ አልነበረም የማርቆስ ወንጌል 6 ፥ 1 _ 6 ፣ የዮሐንስ ወንጌል 5 ፥ 1 _ 18 ፣ የዮሐንስ ወንጌል 8 ፥ 48 _ 59 ውድ ወገኖቼ ትምህርቱ በእነዚህ ሃሳቦች የተጠቀለለ ነው ቪዲዮውንም ደግማችሁ ስሙት ትባረኩበታላችሁ በሚቀጥለው የትምህርት ክፍለ ጊዜ እስክንገናኝ ሰላም ሁኑ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ God bless u all http://www.Facebook.com/yonas.asfaw.39 https://www.youtube.com/yF76GIi_rCQ yonasasfaw8@gmail.com
Subscribe to:
Posts (Atom)