Tuesday, 30 April 2019
Monday, 29 April 2019
Sunday, 28 April 2019
የመልዕክት ርዕስ ፦ ተነስቶአል እንጂ በዚህ የለም ( የሉቃስ ወንጌል 24 : 1 - 12 )«ዮም ፍሥሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን፤ እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን»   የተወደዳችሁ ወገኖች ሰላም ለእናንተ ይሁን እንኩዋን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ ክርስቶስ ተንስአ እሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍስሐ ወሰላም ወገኖቼ በዓሉን አስመልክቶ ተነስቶአል እንጂ በዚህ የለም በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መልዕክት ወደ እናንተ ይዤ ቀርቤያለሁ በዚህ መልዕክት ተጠቀሙ ተባረኩበት ለሌሎችም ሼር አድርጉት መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ
Thursday, 25 April 2019
Tuesday, 23 April 2019
Monday, 22 April 2019
Sunday, 21 April 2019
Saturday, 20 April 2019
በ1980 ዕትም መጽሐፍና በ2000 ዕትም ባሉ የአዋልድ መጻሕፍት መካከል ያሉ ልዩነቶች በ1980 ዕትም መጽሐፍና በ2000 ዕትም ባሉ የአዋልድ መጻሕፍት መካከል ያሉ ልዩነቶች የሁለቱ መጻሕፍት ልዩነት የሚጀምረው ከማውጫው ነው በ1980 ዕትም መጽሐፍ መጽሐፈ አስቴር ሁለት ጊዜ ታተመ በ2000 ዕትም መጽሐፈ አስቴር አንድ ጊዜ ብቻ ታተመ ( አንዱን ብቻ ወስዶአል ) በ1980 ዕትም መጽሐፍ ጸሎተ ምናሴ ፣ መዝሙረ ሠለስቱ ደቂቅና ተረፈ ዳንኤል ታትመው ፣ ተጽፈውና ተካተው ሲገኙ በ2000 ዕትም መጽሐፍ እነዚህ መጻሕፍት የሉም በ2000 ዕትም መጽሐፍ ተረፈ ባሮክ ተጽፎና ታትሞ ይገኛል በ1980 ዕትም መጽሐፍ ግን ተረፈ ባሮክ የለም ከዚህ በመነሳት ወደ ቆጠራው ሲገባ በሁለቱ መጻሕፍት መካከል የቁጥር ልዩነት መኖሩን ለመረዳት እንችላለን የትምህርቱ አቅራቢ: —— አባ ዮናስ ጌታነህ
Friday, 19 April 2019
Thursday, 18 April 2019
Wednesday, 17 April 2019
Tuesday, 16 April 2019
Monday, 15 April 2019
Sunday, 14 April 2019
Saturday, 13 April 2019
Friday, 12 April 2019
Thursday, 11 April 2019
Tuesday, 9 April 2019
Monday, 8 April 2019
Sunday, 7 April 2019
Saturday, 6 April 2019
የመምህር ምህረተ አብ አሰፋ የሐሰት ትምህርት በእግዚአብሔር ቃል ሲጋለጥ ለተከታታይ ሳምንት እውነተኛው ቃል ይነገራ...የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ቅዱሳን ወገኖች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን :: ከዚህ በመቀጠል መምህር ምህረተ አብ አሰፋ የተባለው ሰው በኦስሎ ከተማ በልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን ባገለገለበት ወቅት ኤካቦድ ክብር ከእስራኤል ለቀቀ በሚል ርዕስ ነበርና ያገለገለው ፣ በዚህ አገልግሎት ውስጥ በሴሎ የነበረውን የካህኑ የዔሊንና የልጆቹን አገልግሎት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጋር በማገናኘት ምንም እንኩዋ ታቦቱ ከእስራኤል የተማረከ ሆኖ ክብር ከእስራኤል የለቀቀ ቢሆንም ዛሬም ታቦቱ ፣ ደመራው ፣ ጥምቀቱ ፣ ገናው ሆያሆዬው ፣ ቡሄው ፣ ቅዳሴው ፣ ጸበሉ ፣ ጾሙ ፣ ስግደቱ ፣ ሕማማቱ ፣ ፋሲካው እና የመሣሠሉት ሁሉ በሌለበት የሚወለድ ልጅ ስሙ ኤካቦድ ነው ሲል ተናግሮአል :: ይህንንም ሃሳቡን ወደ ሕዝቡ በማምጣት የተናገረውን ነገር ሕዝቡም አምኖ የተቀበለው መሆኑን ለማረጋገጥ አይደለም ወይ አረ በማርያም ንገሩኝ ? ሲል የማርያም ወዳጅ ለመምሰል በማርያም ስም ሕዝቡን ተማጥኖአል :: ይህም በሕዝቡ ዘንድ የቤተክርስቲያን ተቆርቋሪ ለመምሰልና ተቀባይነትን ለማግኘት የሚደረግ ያላሰለሰ ጥረትና ብርቱ ትግል መሆኑን ከዚሁ ሰው አነጋገር ለመገንዘብ ችያለሁ :: አያይዞም ክብር አለ ? ጽላቱ አለ ? ቅዳሴው አለ ? ጸበሉ አለ ?መስቀል አለ ? ካህናት አሉ ? ዝማሬው አለ ? ማስቀደስ አለ ? ወዘተርፈ እያለ ከጠየቀ በኋላ ፣ ስለዚህ ስትመጡ ሁሉም ነገር ተሟልቶላችኋልና ኤካቦድ አይደላችሁም ሲል ሕዝቡን በባዶ ሜዳ እንዲሁ እልል ያሰኘበትን ስብከትና የቪዲዮ መረጃ በእጄ ስላገኘሁ ይህን ስብከት ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ቃል ስመለከተው ትክክል ባለመሆኑና ምላሽ የሚያስፈልገው መሆኑንም ስላመንኩበት ከመጀመርያ እና ከስብከቱ መነሻ ጀምሮ ከተናገራቸው ሃሳብ በመነሳት የሚከተሉትን መልሶች ለእናንተ ለአድማጮች አዘጋጅቻለሁ :: ቪዲዮዎቹ በየተራ ለተከታታይ ሳምንታት የሚለቀቁ ስለሆኑ እንድትከታተሉአቸው ስል ለማሳሰብ እወዳለሁ :: ለሌሎች ሼር ማድረግንም አትርሱ ተባረኩ :: እስከ ጊዜው ግን ለትውስታ ያክል ይህ ሰው ከተናገራቸው ጥቂቱን ሃሳብ ከዚህ አጭር የቪዲዮ ክሊፕ እንድትከታተሉና የየራሳችሁንም ትሕዝብት እንደ እግዚአብሔር ቃል እንድትወስዱ እጋብዛለሁ :: ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተማሪ ብላ የሾመቻቸው መምህራን የውላችሁ እንዲህ ናቸው :: ለዚህ ሕዝብ የሞተለትን ጌታ መስበክ ሲገባቸው የሚሰብኩት ከበሮንና ጸናጽልን ፣ ጸበልንና እመትን የመሳሰሉትን ነው :: ለእነዚህ የስሕተት አስተማሪዎች እነዚህ ነገሮች እስካሉና እስከተሟሉ ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ኤካቦድ አይደለችም :: ወገኖቼ ሆይ ስለዚህ እነዚህን የስሕተት አስተማሪዎች ስረዳቸው ኤካቦድ የሚለው ሃሳብ በራሱ ለእነዚሁ የስሕተት አስተማሪዎች ግልጽ አይደለም :: ምንም እንኩዋ ኦቶርዶክስ ቤተክርስቲያን በከበሮና በጸናጽል አያሸበሸበች ስትዘምር ብትገኝ ፣ ቅዳሴ ቢኖራት ፣ ማኅሌቱን ብትቆም ፣ ሰዓታቱንም ብታደርስ ክብርዋ ግን ከበሮና ጸናጽል ፣ ማኅሌቱና ሰዓታቱ አይደለም :: ክብርዋ ኢየሱስ ነው :: ስለዚህ ክብርዋ የሆነውን ኢየሱስን ነው ወደ ቤትዋ ልትመልስ የሚገባው :: ታድያ ይሄን እውነት በእርግጠኝነት እንድንቀበል መጽሐፍቅዱሳችን ነግሮን ሳለ ሕዝቡ ይህንን የመጽሐፍቅዱስ እውነት አምኖ እንዳይቀበልና እንዳይድን እነዚህ የስሕተት መምህራን ክብርህ ጸናጽል ፣ ከበሮ ቅዳሴና ሰዓታት እንዲሁም ካህናትና የመሳሰሉት ናቸው ሲሉ ይህንን ምስኪን ሕዝብ እንዲሁ በደረቁ እልል እያስባሉ ያታልሉታል :: ይህን ታድያ እንደ እንደ እግዚአብሔር ቃል ስመለከተው የጤንነት ነው አልለውም :: ስለዚህ እኔም በመጨረሻ የምለው ነገር ቢኖር ቢሆን ቢሆን እነዚህን የሐሰት መምህራን ጌታ ዓይናቸውን ያብራ ነው :: ካልሆነም ግን በስራቸው ያለውን ምስኪን ሕዝብ ከእጃቸው ያስመልጠው ዘንድ ምልጃዬም ሆነ ልመናዬ እንዲሁም ጩኸቴም ነው :: ወገኖቼ ሆይ ይሄ ልመናም ሆነ ጩኸት ታድያ የእኔ ብቻ ሳይሆን የእናንተም እንዲሆን እናገራለሁ :: ለማንኛውም ግን ከዚህ አጭር ክሊፕ መልስ ተያይዘው ያዘጋጀሁዋቸው ቪዲዮዎች ይለቀቃሉ እንድትከታተሉት አሁንም በድጋሜ አሳስባለሁ ለሕዝባችንም ይሁን ለእነዚህ የሐሰት መምህራን ጌታ ማዳኑን እንዲያደርግ አጥብቃችሁ ጸልዩላቸው በነገር ሁሉ ጌታ ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ
የመምህር ምህረተ አብ አሰፋ የሐሰት ትምህርት በእግዚአብሔር ቃል ሲጋለጥ ለተከታታይ ሳምንት እውነተኛው ቃል ይነገራ...የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ቅዱሳን ወገኖች በሙሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን :: ከዚህ በመቀጠል መምህር ምህረተ አብ አሰፋ የተባለው ሰው በኦስሎ ከተማ በልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን ባገለገለበት ወቅት ኤካቦድ ክብር ከእስራኤል ለቀቀ በሚል ርዕስ ነበርና ያገለገለው ፣ በዚህ አገልግሎት ውስጥ በሴሎ የነበረውን የካህኑ የዔሊንና የልጆቹን አገልግሎት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጋር በማገናኘት ምንም እንኩዋ ታቦቱ ከእስራኤል የተማረከ ሆኖ ክብር ከእስራኤል የለቀቀ ቢሆንም ዛሬም ታቦቱ ፣ ደመራው ፣ ጥምቀቱ ፣ ገናው ሆያሆዬው ፣ ቡሄው ፣ ቅዳሴው ፣ ጸበሉ ፣ ጾሙ ፣ ስግደቱ ፣ ሕማማቱ ፣ ፋሲካው እና የመሣሠሉት ሁሉ በሌለበት የሚወለድ ልጅ ስሙ ኤካቦድ ነው ሲል ተናግሮአል :: ይህንንም ሃሳቡን ወደ ሕዝቡ በማምጣት የተናገረውን ነገር ሕዝቡም አምኖ የተቀበለው መሆኑን ለማረጋገጥ አይደለም ወይ አረ በማርያም ንገሩኝ ? ሲል የማርያም ወዳጅ ለመምሰል በማርያም ስም ሕዝቡን ተማጥኖአል :: ይህም በሕዝቡ ዘንድ የቤተክርስቲያን ተቆርቋሪ ለመምሰልና ተቀባይነትን ለማግኘት የሚደረግ ያላሰለሰ ጥረትና ብርቱ ትግል መሆኑን ከዚሁ ሰው አነጋገር ለመገንዘብ ችያለሁ :: አያይዞም ክብር አለ ? ጽላቱ አለ ? ቅዳሴው አለ ? ጸበሉ አለ ?መስቀል አለ ? ካህናት አሉ ? ዝማሬው አለ ? ማስቀደስ አለ ? ወዘተርፈ እያለ ከጠየቀ በኋላ ፣ ስለዚህ ስትመጡ ሁሉም ነገር ተሟልቶላችኋልና ኤካቦድ አይደላችሁም ሲል ሕዝቡን በባዶ ሜዳ እንዲሁ እልል ያሰኘበትን ስብከትና የቪዲዮ መረጃ በእጄ ስላገኘሁ ይህን ስብከት ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ቃል ስመለከተው ትክክል ባለመሆኑና ምላሽ የሚያስፈልገው መሆኑንም ስላመንኩበት ከመጀመርያ እና ከስብከቱ መነሻ ጀምሮ ከተናገራቸው ሃሳብ በመነሳት የሚከተሉትን መልሶች ለእናንተ ለአድማጮች አዘጋጅቻለሁ :: ቪዲዮዎቹ በየተራ ለተከታታይ ሳምንታት የሚለቀቁ ስለሆኑ እንድትከታተሉአቸው ስል ለማሳሰብ እወዳለሁ :: ለሌሎች ሼር ማድረግንም አትርሱ ተባረኩ :: እስከ ጊዜው ግን ለትውስታ ያክል ይህ ሰው ከተናገራቸው ጥቂቱን ሃሳብ ከዚህ አጭር የቪዲዮ ክሊፕ እንድትከታተሉና የየራሳችሁንም ትሕዝብት እንደ እግዚአብሔር ቃል እንድትወስዱ እጋብዛለሁ :: ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተማሪ ብላ የሾመቻቸው መምህራን የውላችሁ እንዲህ ናቸው :: ለዚህ ሕዝብ የሞተለትን ጌታ መስበክ ሲገባቸው የሚሰብኩት ከበሮንና ጸናጽልን ፣ ጸበልንና እመትን የመሳሰሉትን ነው :: ለእነዚህ የስሕተት አስተማሪዎች እነዚህ ነገሮች እስካሉና እስከተሟሉ ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ኤካቦድ አይደለችም :: ወገኖቼ ሆይ ስለዚህ እነዚህን የስሕተት አስተማሪዎች ስረዳቸው ኤካቦድ የሚለው ሃሳብ በራሱ ለእነዚሁ የስሕተት አስተማሪዎች ግልጽ አይደለም :: ምንም እንኩዋ ኦቶርዶክስ ቤተክርስቲያን በከበሮና በጸናጽል አያሸበሸበች ስትዘምር ብትገኝ ፣ ቅዳሴ ቢኖራት ፣ ማኅሌቱን ብትቆም ፣ ሰዓታቱንም ብታደርስ ክብርዋ ግን ከበሮና ጸናጽል ፣ ማኅሌቱና ሰዓታቱ አይደለም :: ክብርዋ ኢየሱስ ነው :: ስለዚህ ክብርዋ የሆነውን ኢየሱስን ነው ወደ ቤትዋ ልትመልስ የሚገባው :: ታድያ ይሄን እውነት በእርግጠኝነት እንድንቀበል መጽሐፍቅዱሳችን ነግሮን ሳለ ሕዝቡ ይህንን የመጽሐፍቅዱስ እውነት አምኖ እንዳይቀበልና እንዳይድን እነዚህ የስሕተት መምህራን ክብርህ ጸናጽል ፣ ከበሮ ቅዳሴና ሰዓታት እንዲሁም ካህናትና የመሳሰሉት ናቸው ሲሉ ይህንን ምስኪን ሕዝብ እንዲሁ በደረቁ እልል እያስባሉ ያታልሉታል :: ይህን ታድያ እንደ እንደ እግዚአብሔር ቃል ስመለከተው የጤንነት ነው አልለውም :: ስለዚህ እኔም በመጨረሻ የምለው ነገር ቢኖር ቢሆን ቢሆን እነዚህን የሐሰት መምህራን ጌታ ዓይናቸውን ያብራ ነው :: ካልሆነም ግን በስራቸው ያለውን ምስኪን ሕዝብ ከእጃቸው ያስመልጠው ዘንድ ምልጃዬም ሆነ ልመናዬ እንዲሁም ጩኸቴም ነው :: ወገኖቼ ሆይ ይሄ ልመናም ሆነ ጩኸት ታድያ የእኔ ብቻ ሳይሆን የእናንተም እንዲሆን እናገራለሁ :: ለማንኛውም ግን ከዚህ አጭር ክሊፕ መልስ ተያይዘው ያዘጋጀሁዋቸው ቪዲዮዎች ይለቀቃሉ እንድትከታተሉት አሁንም በድጋሜ አሳስባለሁ ለሕዝባችንም ይሁን ለእነዚህ የሐሰት መምህራን ጌታ ማዳኑን እንዲያደርግ አጥብቃችሁ ጸልዩላቸው በነገር ሁሉ ጌታ ይባርካችሁ አባ ዮናስ ጌታነህ
Friday, 5 April 2019
Wednesday, 3 April 2019
Tuesday, 2 April 2019
Monday, 1 April 2019
Subscribe to:
Posts (Atom)