Friday, 27 January 2017
የመልዕክት ርዕስ ፦ የእግዚአብሔርን ቃል በሰዎች ሕይወት ውስጥ ማጽናት ( እርግጠኛ ማድረግ ) ዕብራውያን 2 ፥ 3...የመልዕክት ርዕስ ፦ የእግዚአብሔርን ቃል በሰዎች ሕይወት ውስጥ ማጽናት ( እርግጠኛ ማድረግ )ዕብራውያን 2 ፥ 3 እና 4 የተወደዳችሁ ቅዱሳን ይህ መልዕክት ለሁላችንም በጣም አስፈላጊና ወቅታዊ የሆነ መልዕክት በመሆኑ በብዙ ልታደምጡት ይገባል ስል ላሳስባችሁ እወዳለሁ ከቪዲዮው መልዕክት እንደምትሰሙት በአጭሩ ከጌታ የሰማነውን የእግዚአብሔርን ቃል ማጽናት በምንጀምርበት ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል በሰሙና ሊሰሙ ባሉ ፣ በሚሰሙም አማኞች ሕይወት ውስጥ ቃሉ እውነት ይሆናል እውነትም ሆኖ ይቀራል ከዚህም የተነሳ ቃሉን የሰሙ አማኝ ክርስቲያኖች የሕይወት አካሄድ እና የኑሮ ሥርዓት የአመለካከትም ለውጥ ያደርጋሉ ከጌታ የሰማነውን ቃል ማጽናት በማንችልበት ጊዜ ደግሞ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል እውነት አይሆንም ከዚህ የተነሳም ሰዎች ከክፉ መንገዳቸው አይመለሱም እንደውም እኛ ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለእነርሱም ጭምር ይሆናል ብለን የጀመርነውን የእግዚአብሔር ነገር አቋም ኖሮንና በአቋማችንም ጸንተን ቃሉን በራሳችን ሕይወትም ሆነ በሰሚዎች ሕይወት ካለማጽናታችን የተነሳ ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለሰሚዎቻችንም ጭምር ነገሩ ይበልጥ መሰናከያና ኃጢአት ይሆንባቸዋል እንደገናም እርግጠኝነትና የእግዚአብሔርንም ቃል ማጽናት ከሌለ ሰዎች የኪዳኑን ደም እንደ ርኩስ ነገር እስከ መቁጠር ይደርሳሉ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋሉ ስለዚህ እኛ በእውነት የጌታ አገልጋዮች ከሆንን ከጌታ የሰማነውን የእግዚአብሔርን ቃል በሰዎች ሕይወት ውስጥ ማጽናትና ማረጋገጥ አለብን ይህን በምናደርግበት ጊዜ ጌታም ከእኛ ጋር ሆኖ ይሰራል በሚከተሉትም ምልክቶችና ተአምራቶች ቃሉን ያጸናል በማለት ነበር የተነጋገርነው ታድያ ይህቺን አጭር መልዕክት የጻፍኩት ከዚህ በመቀጠል ለምትሰሙት ቪዲዮ እንደ መንደርደርያ ይሆናችኋል ብዬ ስላሰብኩ ነው ተባረኩልኝ በጌታ ፍቅር እወዳችኋለሁ እጸልይላችኋለሁ የቪዲዮውን መልዕክት ብትችሉ ያልሰሙ እንዲሰሙ ሼር አድርጉት ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ አሜን ከ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ
Thursday, 26 January 2017
Monday, 23 January 2017
Thursday, 19 January 2017
የመልዕክት ርዕስ ፦ ያልተለመደ ነገር ያደርጋልና የእግዚአብሔርን ነገር ተረኛ እግዚአብሔርንም ወረፈኛ አታድርገው (...አንኳር የሆኑ የመልዕክቱ ዋና ዋና ሃሳቦች እግዚአብሔር ተገለጡ የሚለን በአክአብና በመንግሥቱም የሚያስፈልገን በኤልያስ ዘመን እንደመጣው ዝናብ ዝናብን አምጥቶ ተደናቂ ባርያዎች መሆናችንን ሊያስመሰክርልን ወይም ሊያረጋግጥልን ሳይሆን እንደዚሁ እንደ ኤልያስ አሁንም ፈርሶ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠውያ እንድናበጅ ሊያደርገንና ጉልበትም ሊሆነን ነው ኤልያስ ተገለጥ ዝናብ እሰጣለሁ ስለተባለ በአክአብ መንግሥትና ሕዝብም ሳይቀር ስለተፈለገ እንዲሁ በቀላሉ ሄዶ ከበዓል ነቢያትና ከመሥዋዕቶቻቸው መልስ መሠውያን ያቀረበ አልሆነም ይህንን ያደረገ ቢሆንማ እግዚአብሔርን ተረኛና ተራውም የደረሰ ወረፈኛ ባደረገው ነበር ነገር ግን ኤልያስ አምላኩን ለወረፋ የተዘጋጀ ከበዓልም ነቢያት አገልግሎት ለጥቆ የሚሠራ ተረኛ አላደረገውም ይህንንም የምናውቀው ከኤልያስ ከንግጝሩ፣ ከሰጣቸው መልሶቹና ከድርጊቱ ተነስተን ነው ይህንንም ለማወቅ እነዚህን ጥቅሶች ያንብቡአቸው 1ኛ ነገሥት 18 ፥ 15 ፣ 16 _ 29 ፣ 30 _ 46 ይህ ኤልያስ ታድያ ፈርሶ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠውያ ሲያበጅ በሌላኛው ገጽታ ወይም በተዘዋዋሪ የበዓልን ነቢያት መሠውያቸውንም ሆነ መሥዋዕታቸውን ሙሉ ለሙሉ እያፈረሰውና ዋጋም እያሳጣው መሆኑን ሁላችንም በይበልጥ የምንገነዘበው ጉዳይ ሊሆን ይገባል እርሱ ገና ሕያው እግዚአብሔርን ለእርሱ እገለጣለሁ ሲል የበዓል ነቢያት መሠውያቸውም ይሁን መስዋዕታቸው እንዲሁም ትንግርታቸውና ሟርታቸውም ጭምር ፈርሷል አሁንም እስከ ለዘለዓለሙ የፈረሰ ይሁን ሙሉ ትምህርቱን ለማግኘት ቪዲዮውን ይከታተሉ ጌታ እግዚአብሔር ዘመንዎን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን የ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry አገልጋይና የአገልግሎቱ ባለአደራ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ ተባረኩ
Wednesday, 18 January 2017
Sunday, 15 January 2017
Friday, 13 January 2017
Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: የጾምና የጸሎት ጥሪ ለቅዱሳን ወገኖችሰላም ቅዱሳን ወገኖች የጌታ ጸጋና...
Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry: የጾምና የጸሎት ጥሪ ለቅዱሳን ወገኖች
ሰላም ቅዱሳን ወገኖች የጌታ ጸጋና...: የጾምና የጸሎት ጥሪ ለቅዱሳን ወገኖች ሰላም ቅዱሳን ወገኖች የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ይህ የ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry...
ሰላም ቅዱሳን ወገኖች የጌታ ጸጋና...: የጾምና የጸሎት ጥሪ ለቅዱሳን ወገኖች ሰላም ቅዱሳን ወገኖች የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ይህ የ Joshua Breakthrough Renewal Apostolic Ministry...