Wednesday 20 March 2019

የመልዕክት ርዕስ ፦ ተነሥቶ ነፋሱንና ባሕሩን ገሠጸ ታላቅ ጸጥታም ሆነ የማቴዎስ ወንጌል 8 ፥ 23 - 27የመልዕክት ርዕስ ፦ ተነሥቶ ነፋሱንና ባሕሩን ገሠጸ ታላቅ ጸጥታም ሆነ የማቴዎስ ወንጌል 8 ፥ 23 - 27 የመነሣትና የእምነትንም ሥራ የመሥራት ጊዜ ለዘመኗ ለቤተክርስቲያን ይሁን አንቅተውም፦ መምህር ሆይ፥ ስንጠፋ አይገድህምን? አሉት ( የማርቆስ ወንጌል  4 : 38 ) ወአንከሩ ሰብእ ወይቤሉ መኑ እንጋ ውእቱ ዝንቱ ዘይትኤዘዙ ሎቱ ባሕርኒ ወነፋሳትኒ ሰዎቹም ነፋሳትና ባሕር ስንኳ የሚታዘዙለት ይህ እንዴት ያለ ሰው ነው ?እያሉ ተደነቁ ፈርዖንም በቀረበ ጊዜ የእስራኤል ልጆች ዓይናቸውን አነሡ፥ እነሆም ግብፃውያን በኋላቸው ገሥግስው ነበር፤ የእስራኤልም ልጆች እጅግ ፈሩ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጮኹ ( ኦሪት ዘጸአት  14 :10 ) ሙሴንም፦ በግብፅ መቃብር ስላልኖረ በምድረ በዳ እንሞት ዘንድ አወጣኸንን? ከግብፅ ታወጣን ዘንድ ይህ ያደረግህብን ምንድር ነው? በምድረ በዳ ከምንሞት ብንገዛላቸው ይሻላልና፦ ተወን፥ ለግብፃውያን እንገዛ ብለን በግብፅ ሳለን ያልንህ ቃል ይህ አይደለምን? አሉት ( ኦሪት ዘጸአት  14 : 11 - 12 ) እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና ( የሐዋርያት ሥራ  10 : 38 ) እነዚህ ጥቅሶች የመልዕክቱን ዋናና አንኳር ሃሳቦችን የሚገልጡ ናቸው ተባረኩ የእግዚአብሔር ቃል አገልጋይ አባ ዮናስ ጌታነህ

No comments:

Post a Comment